ማህበረ ቅዱሳን፤ በአቡነ ጐርጐሪዎስ የዜማ መሳሪያዎች ትምህርትና ስልጠና ማዕከል ባለፈው ዓመት ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች፤ ዛሬ ከቀኑ 7፡30 ሰዓት ጀምሮ በማህበሩ ህንፃ ላይ በሚገኘው አዳራሽ እንደሚያስመርቅ አስታወቀ፡፡ማህበሩ ዘንድሮ ለ11ኛ ጊዜ የሚያስመርቃቸው 300 ተማሪዎችን እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ተመራቂዎቹ በስልጠና ቆይታቸው በበገና፣ በመሰንቆ፣ በልሳነ-ግዕዝ እና በከበሮ አመታት ትምህርት ማግኘታቸውን የጠቆመው ማህበሩ፤ የምረቃ ሥነስርዓቱ ሊቃነ ጳጳሳት፣ ሊቃውንተ ቤተ-ክርስቲያን፣ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተወካዮችና ታዋቂ ግለሰቦች በተገኙበት ይከናወናል ተብሏል፡፡