Saturday, 15 August 2015 16:20

የየአገሩ ምሳሌያዊ አባባል

Written by 
Rate this item
(16 votes)

ከተጠበሰ እንቁላል ጫጩት ማስፈልፈል አትችልም፡፡
የደች አባባል
 መደነቅ የጥበብ መጀመሪያ ነው፡፡
የግሪካውያን አባባል
እግዚአብሔር ምድር ላይ ቢኖር ኖሮ ሰዎች መስኮቱን ይሰብሩት ነበር፡፡
የአይሁዳውያን አባባል
ዝምታ ፈፅሞ ተፅፎ አያውቅም፡፡
የጣልያውያን አባባል
ፖለሪካ የበሰበሰ እንቁላል ነው፤ ከተሰበረ ይገማል።
የሩሳያውያን አባባል
ከተራመድክ መደነስ ትችላለህ፤ ከተናገርክ መዝፈን ትችላለህ፡፡
የዚምባቡዌ አባባል
እንደ ንፁህ ህሎሊና ለስላሳ ትራስ የለም፡፡
የፈረንሳውያን አባባል
ዝም ብለህ ተቀመጥ፤ ሰዎች እንደፈላስፋ ይቆጥሩሃል፡፡
የላቲን አባባል
የእግዚአብሔር እርሳስ ላጲስ የለውም፡፡
የሃይቲዎች አባባል
የማትናከስ ከሆነ ጥርስህን አታሳይ፡፡
የስፔናውያን አባባል
የጤናማነት መጀመሪያ በሽታውን ማወቅ ነው፡፡
የስፔናውያን አባባል
የስኳርን ጣዕም የምታደንቀው ሎሚን ስትቀምስ ብቻ ነው፡፡
የዩክሬናውያን አባባል
የቱንም ያህል ብትደክም ኮርማ ወተት አይሰጥህም፡፡
የዩክሬናውያን አባባል
ብቻውን የተጓዘ ያሻውን ማውራት ይችላል፡፡
የሩዋንዳውያን አባባል
ሚስትህን በአበባም እንኳ አትምታት፡፡
የሂንዱ አባባል
ማንም የራሱን አይብ ኮምጣጣ ነው አይልም፡፡
የአፍጋኒስታውያን አባባል
ሁሉም ሰው እንዲራመድብህ ከፈቀድክ ምንጣፍ ትሆናለህ፡፡
የቡልጋሪያውያን አባባል
የውሃውን ጥልቀት በሁለት እግሮቹ የሚለካ ጅል ብቻ ነው፡፡
የአፍሪካውያን አባባል
መንገዶች ሁሉ ወደሮም አያደርሱም፡፡
የስሎቬንያውያን አባባል
ድልድዩን ከሰበርክ ዋና መቻልህን እርግጠኛ ሁን፡፡
የስዋሂሊ አባባል

Read 2671 times