Saturday, 01 August 2015 14:36

“ባንቺ የመጣ” ፊልም ተመረቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በአይናዲስ በላይ ተደርሶ፣ በመስፍን በላይ ዳይሬክት የተደረገውና በኤምቢ ፊልም ፕሮዳክሽን የቀረበው “ባንቺ የመጣ” የተሰኘ ፊልም ባለፈው ሰኞ ምሽት በብሄራዊ ቴአትር ተመረቀ፡፡
“ፊልሙ በሀገራችን እየተስፋፋና ሴት እህቶቻችንን ለሞት ጭምር እየዳረገ ባለው አስገድዶ መድፈር ላይ ትኩረት አድርጎ የተሰራ ሲሆን በተለይ በዩኒቨርሲቲዎቻችን አካባቢ በሚታየው የሴት ተማሪዎቻችን ህይወት ላይ ያጠነጥናል” ተብሏል፡፡
የፊልሙ ዓይነት በድርጊት የተሞላ ሰስፔንስ ድራማ ሲሆን ፊልሙን ሰርቶ ለማጠናቀቅ 1 ዓመት ከ2 ወር እንደፈጀ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ፊልሙን ለመስራት 780 ሺ ብር እንደፈጀme ተገልጿል፡፡ በፊልሙ ላይ ሳምሶን ታደሰ (ቤቢ)፣ ካሣሁን ፍስሃ (ማንዴላ)፣ ሉሊት ገረመው እና ሌሎችም ተውነዋል፡፡

Read 1204 times