Saturday, 18 July 2015 12:00

ዕውቀትና ትጋት አሰፋ ጐሳዬ ቤተመጻህፍት መፃሕፍት ተለገሰ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የአቶ ካሣዬ ተክለአረጋይ ቤተሰቦች የተለያየ ቅፅ ኢንሳይክሎፒዲያ፣ የወንጀለኛ መቅጫ፣ የተጠቃለሉ ሕጐች፣ የሕግ መጽሔቶችና ጠቅላላ ዕውቀትን ጨምሮ 60 ያህል መፃሕፍትን ለዕውቀትና ትጋት አሰፋ ጎሳዬ የሕዝብ ቤተ-መፃሕፍት ሰሞኑን አበረከቱ፡፡
የሕግ ባለሙያ የነበሩት አቶ ካሣዬ ተክለአረጋይ በሕይወት ሳሉ ሲጠቀሙባቸው የነበሩ መፃሕፍትን ለቤተመፃሕፍቱ ያበረከቱት ልጃቸው አቶ ሰለሞን ካሣዬ ናቸው፡፡ የአቶ ሰለሞን ካሣዬ ባለቤት ወ/ሮ ምህረት ጌታቸው በወቅቱ እንደተናገሩት፤ “መጻህፍቱን እንድንሰጣቸው  የጠየቁ ግለሰቦች የነበሩ ቢሆንም መፃሕፍቱ የበለጠ ከአንባቢያን ጋር ሊገናኙ የሚችሉት በቤተ-መፃሕፍት ውስጥ ቢቀመጡ ነው በሚል እምነት አበርክተንላችኋል” ብለዋል፡፡

Read 3045 times