Saturday, 18 July 2015 11:59

የዓለማየሁ ገላጋይ “ወሪሳ” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(6 votes)

 በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ የሰሉ ሥነ ፅሁፋዊ ሂሶችን በማቅረብ የሚታወቀው ደራሲና ሃያሲ ዓለማየሁ ገላጋይ የጻፈው “ወሪሳ - የውድቀት ፈለጎች” የተሰኘ የረዥም ልብ ወለድ መፅሃፍ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡
አዲሱ ልብወለድ ለደራሲው 9ኛ መፅሃፉ ሲሆን በ49 ብር እየተሸጠ መሆኑ ታውቋል፡፡
ዓለማየሁ ከዚህ ቀደም “አጥቢያ”፣ “ቅበላ” እና “የብርሃን ፈለጎች” የተሰኙ ግሩም የረዥም ልብወለድ ስራዎችን ያሳተመ ሲሆን “ኩርቢት” የሚል የአጭር ልቦለድ መድበልም ለአንባቢያን አድርሷል፡፡ በደራሲ ስብሃት ገብረእግዚአብሄር ህይወትና ክህሎት ዙሪያ ያሰናዳው መፅሃፉም የሥነፅሁፍ  ምሁራንን ያነጋገረና ያሟገተ መሆኑ ይታወሳል፡፡ ደራሲው፤ “ፍትህ”፣ “አዲስ ታይምስ” እና“ፋክት” በተሰኙ የህትመት ውጤቶች ላይ ያቀርባቸው በነበሩ ማራኪና ኮርኳሪ መጣጥፎቹ የብዙዎችን ቀልብ ለመሳብ ችሏል፡፡

Read 3481 times