አምስት በአማርኛና አንድ በኦሮምኛ ቋንቋ የተፃፉ ስዕላዊ ባለቀለም የህጻናት መፃህፍት ተዘጋጅተው የታተሙ ሲሆን በነገው ዕለት ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ከደንበል ህንፃ ፊት ለፊት፣ ከዴሉክስ ፈርኒቸር ጀርባ በሚገኘው ኢግሉ አይስክሬም ቤት ይመረቃሉ፡፡
የመፃህፍቱን ታሪኮች በመድረስ አዜብ ወርቁ፣ ዳንኤል ወርቁ፣ ሰላማዊት ሙሉጌታና ሲሳይ ተስፋዬ የተሳተፉ ሲሆን የስዕል ስራዎቹን የሰሩት ሰዓሊ ደረጄ ደምሴ፣ አርክቴክት አሃዱ አባይነህና የህፃናት ስዕል ባለሙያው ይስሃቅ ሳህሌ እንደሆኑ የመፃህፍቱ አሳታሚ “ሚዳቆ ፐብሊሺንግ” ለአዲስ አድማስ በላከው ጋዜጣው መግለጫ ጠቁሟል፡፡ የመፃህፍቱ ዋጋ (እያንዳንዱ) 29 ብር ነው ተብሏል፡፡ “ሚዳቆ ፐብሊሺንግ” ዋነኛ ትኩረቱን በህፃናት መፃህፍት ላይ ያደረገ የህትመት ተቋም እንደሆነ ተገልጿል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና