Saturday, 18 July 2015 11:56

“ፍቅር እና አደራ …” ዛሬ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 “… ከገራገር ህይወቷ ላይ የሚከተላት ምሳሌ የፍስሃዋን በር የሚዘጋ ነገር አታጣም፡፡ በተፈጥሮ ያልሆነ በልጅ ሃሳብም ያልሆነ፣ በሴትነትም ያልሆነ የሚከተላት ጠልና ጥል እጇ ላይ ነጥሮ ይመጣል፤ አነጣጥሮ ይመታታል፡፡ በሩን ወደ ኋላ ዘጋችው። አይኖቿን ጨፍና አመታቱን አሰበች፡፡ ጠባሳዋን ቆጠረች፡፡ …”
(ከመፅሀፉ የተቀነጨበ)
በደራሲ ሊና ካሳሁን የተፃፉ ታሪኮችን ያካተተው “ፍቅር እና አደራ እና ሌሎችም” የተሰኘው መፅሃፍ ሰሞኑን ለአንባቢያን የቀረበ ሲሆን በዛሬው እለት ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ ከሬዲዮ ፋና ህንፃ ጀርባ በሚገኘው ወመዘክር አዳራሽ ይመረቃል፡፡
መፅሀፉ 11 ታሪኮችን የያዘ ሲሆን በ162 ገፆች እንደተቀነበበና በ40.50 ለገበያ መቅረቡ ታውቋል። የደራሲዋ ተከታይ ስራም “የእሳት እራት” የሚል ርዕስ ያለው እንደሚሆን ተጠቁሟል፡፡

Read 1487 times