በድቅድቁ የቀለመውን ፅልመት ሃዘን በከረቸመው ከንፈሮችዋ መሃል በማትጐለጐል ነበልባል የነገን ጭላንጭል ተስፋ እያየች ትዕግስት የሚሉት ተሰጥኦ እንደዛር ተከምሮባት ከባዱን ችላ ስለምትወዳቸው መስዋዕትነት የከፈለች በእውነት ጐበዝ ጀግና ነች…”
ከላይ የቀረበው ቅንጭብ የተወሰደው ደራሲ ዝናሽ ኤልያስ (ዲና) ከጻፈችውና “መስዋዕት” የሚል ርዕስ ከሰጠችው ረዥም ልብወለድ ሲሆን መጽሐፉ ሰሞኑን ለገበያ ቀርቧል፡፡ የታሪኩ ጭብጥ በአንዲት ሴት የህይወት ውጣ ውረድ ዙሪያ የሚያጠነጥን ነው ተብሏል፡፡
“መስዋዕት” በእውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተፃፈና በ214 ገፆች የተሰናዳ ሲሆን በ60 ብር ለሽያጭ እንደቀረበ ታውቋል፡፡
Saturday, 11 July 2015 13:03
“መ “መስዋዕት” ረዥም ልብወለድ ለገበያ ቀረበስዋዕት” ረዥም ልብወለድ ለገበያ ቀረበ
Written by Administrator
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና