በወጣቷ ገጣሚ ፅጌረዳ ጌታቸው የተፃፉ የእንግሊዝኛ ግጥሞች የየዘ “The Unspoken Outlook” የተሰኘ የግጥም መድበል በዛሬው ዕለት ከ10፡30 ጀምሮ ቦሌ ኤርፖርት መዳረሻ ጋ በሚገኘው ቲኬ ህንፃ፣ 8ኛ ፎቅ ላይ ይመረቃል፡፡ በምረቃው ሥነ -ሥርዓት ላይ የስነ ፅሁፍ ባለሙያ ሂሳዊ ዳሰሳ ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
በ84 ገፆች የተቀነበበው የግጥም መድበሉ፤ በ38 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ገጣሚዋ ዘንድሮ በሲቪል ኢንጂነሪንግ ከአምስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ እንደምትመረቅ ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና