Saturday, 13 June 2015 15:37

የገጣሚ ደምሰው መርሻ “ያልታየው ተውኔት” ረቡዕ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የገጣሚ ደምሰው መርሻ በሙዚቃ የተቀናበሩ የግጥም ሥራዎች “ያልታየው ተውኔት” በሚል ርዕስ በሲዲ የተዘጋጀ ሲሆን የፊታችን ረቡዕ ከ11 ሰዓት ጀምሮ በሂልተን ሆቴል ይመረቃል፡፡
17 ግጥሞችን ታዋቂው ሙዚቀኛ ጆርጋ መስፍን ያቀናበረለት ሲሆን 1 ግጥም ደግሞ በጥላሁን ጊዮርጊስ (ፒጁ) መቀናበሩን ገጣሚው ጠቅሶ፣ኤርምያስ ዳኜ የሁሉንም ሚክሲንግ እንደሰራለት ተናግሯል፡፡
የሲዲውን ሽፋን ሰዓሊ ዳንኤል ታዬ ሰርቶልኛል ብሏል- ገጣሚው፡፡   
በሒልተን ሆቴል በሚካሄደው የግጥም ሲዲ የምረቃ ሥነሥርዓት ላይ አንጋፋው ሃያሲ አብደላ እዝራ በግጥሞቹ ላይ ሒሳዊ ዳሰሳ የሚያቀርብ ሲሆን ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ፣ ገጣሚ ኤፍሬም ስዩም፣ አርቲስት ፈለቀ አበበና ሌሎችም ለታዳሚያን የግጥም ሥራዎችን ያቀርባሉ ተብሏል፡፡ ደምሰው መርሻ በተለያዩ የጥበብ መድረኮች ላይ ግጥሞቹን አዘውትሮ በማቅረብ የሚታወቅ ተወዳጅ ገጣሚ ሲሆን የ“ግጥም በጃዝ” ቡድንም አባል ነው፡፡

Read 2273 times