Saturday, 13 June 2015 15:24

የይስማዕከ ወርቁ “ሜሎስ” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(54 votes)

  ለደራሲው 10ኛው መጽሐፉ ነው
   “ዴርቶጋዳ” በተሰኘው የመጀመሪያ ልብ ወለድ መፅሃፉ ከፍተኛ ተነባቢነትና ዕውቅናን የተቀዳጀው ወጣቱ ደራሲ ይስማዕከ ወርቁ፤ “ሜሎስ” የተሰኘ አዲስ ልብ ወለድ መጽሐፍ ሰሞኑን ለንባብ ያበቃ ሲሆን 10ኛ መጽሃፉ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል፡፡ በ280 ገፆች የተቀነበበውን መጽሐፍ፤የዲዛይንና ህትመት ሥራ ያከናወነው ራሱ ደራሲው ያቋቋመው ዴርቶጋዳ ማተሚያ ድርጅት ነው፡፡ “ሜሎስ” በ60 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
ይስማዕከ ከዚህ ቀደም “የወንድ ምጥ”፣ “ዴርቶጋዳ”፣ “የቀንድ አውጣ ኑሮ”፣ “ራማቶሓራ”፣ “ተልሚድ”፣ “ተከርቸም”፣ “ዣንቶዣራ”፣ “ክቡር ድንጋይ” እና “ዮራቶራድ” የተባሉ መጽሐፍትን ያሳተመ ሲሆን  አብዛኞቹም በከፍተኛ ቅጂ በመሸጥ ለአሳታሚውም ሆነ ለጸሃፊው ዳጎስ ያለ ገቢ ማስገኘታቸው ይታወቃል፡፡ በተለይ “ዴርቶጋዳ” በጠቅላላው ወደ 200ሺ የሚጠጉ ቅጂዎች በመታተም በኢትዮጵያ የሥነጽሁፍ ህትመት ታሪክ አዲስ ሪከርድ ማስመዝገቡን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ አንዳንድ የሥነጽሁፍ ባለሙያዎችና ሃያሲያን፣ ደራሲው ከመጀመሪያው ሥራው በኋላ ያወጣቸው ተከታታይ  መጻህፍት እያሽቆለቆሉ መምጣታቸውን ቢናገሩም እስካሁን በሥራዎቹ ላይ የሰላ ሂስ የሰነዘረ ወይም ሂሳዊ ጽሁፍ ያቀረበ የለም፡፡

Read 19126 times