Sunday, 10 May 2015 15:17

“ሳንሱሲ” የተሰኘ ልብ-ወለድ መፅሃፍ እየተነበበ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ደራሲው ዘውዱ ደስታ የምንድስና ባለሙያ ሲሆን በዘርፋ በሃገራችን ውስጥ ትልልቅ ፕሮጀክቶች ላይ ሰርቷል፡፡ እየሰራም ይገኛል፡፡ደራሲው የህይወት ልምዱን ፤የንባብ ክህሎቱን ፤የብዙ ጊዜ ገጠመኞቹን ፤ትዝብቱንም ጭምር  ሳንሱሲ ውስጥ ከትቧል፡፡
ቀድሞ ሳንሱሲን እንዲያነቡ እድሉን ያገኙ ፀሀፊያን ከሶስት  በላይ አንኳር ጉዳችን  ደራሲው በመፅሀፋ እንዳስቀመጠና እንዲህም ሆኖ ግን ቁምነገሮቹ ተደጋጋፊና ተመጋጋቢ በመሆናቸው ለአንባቢያን የአይን መግለጫ ነው ብለዋል፡፡
ደራሲው ዘውዱ ደስታ ከአዲስ አበባ ምዕራብ  መዝለቂያ በሆነችው ሳናሱሲ ላይ መቼቱን አድርጎ የፈጠራቸው የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ገጸባህርያት ፤አንዳንዶቹ በልባችን ሙቀትና ቁመት ሲጎልምሱ አንዳንዶቹ ሰንፈው ሲፈርሱ በአጠቃላይ እንድንወዳቸው እንድንጨክንባቸው እና እንድንወያይባቸው ያደርጋል፡፡
ሳንሱሲ መጽሀፍን ማግኘት ለምትሹ አንባቢያን በተለያዩ መጽሃፍት መደብሮች ቀድሞ ይሸጥ ከነበረው  136 ብር  ደራሲው ዋጋውን አስተካክሎ በ96 ብር አቅርቦታል፡፡

Read 1427 times