በፀደይ ወቅት እናት መሬት እርጉዝ ናትና በቀስታ ተራመድ፡፡
ሰው ከተፈጥሮ ሲርቅ ልቡ ይደነድናል፡፡
ትንሿ አይጥ እንኳን የራሷ ንዴት አላት፡፡
የመጀመሪያው መምህራችን የራሳችን ልብ ነው፡፡
የሚንጫጩ ወፎች ጎጆ አይሰሩም፡፡
ሞክሮ መውደቅ ስንፍና አይደለም፡፡
ፍየል እንደሚሰጥህ ከገመትክ ግመል ጠይቅ።
በሰው አህያ ጉዞ አትጀምርም፡፡
ዳንስ የማያውቅን ዛፍ ነፋስ ያስተምረዋል፡፡
የማይናገር ሰውና የማይጮህ ውሻን ተጠንቀቅ፡፡
ጦጣ የምትሞት ዕለት ዛፎች ሁሉ ያንሸራትታሉ፡፡
እንቁላል ሻጭ ገበያ ውስጥ ጠብ አያነሳም፡፡
አላርፍ ያለ እግር የእባብ ጉድጓድ ውስጥ ዘው ይላል፡፡
ዝናብ በአንድ ጣራ ላይ ብቻ አይዘንብም፡፡
ጦርነት ዓይን የለውም፡፡
በአንበሳ የሚመራ የበግ ሰራዊት፣ በበግ የሚመራ የአንበሳ ሰራዊትን ማሸነፍ ይችላል።
የልመና ውሃ ጥም አያረካም፡፡
Published in
ባህል