Saturday, 07 February 2015 13:00

የመጀመርያው አገር አቀፍ የስፖርት ኤግዚቢሽንና ባዛር ተዘጋጅቷል

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(0 votes)

    በስፖርቱ በማርኬቲንግና በኢንቨስትመንት ያሉ እንቅስቃሴዎችን ለማነቃቃት በሚል ዓላማ 1ኛው ስፖርት ኤግዚቢሽን ባዛር  ተዘጋጀ፡፡ በጂኤምኤስ ፕሮሞሽንና በፈለቀ ደምሴ የኮምኒኬሽን ስራዎች የተዘጋጀው ኤግዚብሽንና ባዛር ከመጋቢት 5 እስከ 9 በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ይካሄዳል፡፡ በኤግዚቢሽንና ባዛሩ ላይ ለመሳተፍ በፌደራል ስፖርት ኮሚሽን ምዝገባ እየተከናወነ ሲሆንን ኮሚሽኑን ጨምሮ፤ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን፣ ፣ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴና፣ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ሌሎች ፌደሬሽኖችና የስፖርት ተቋማት በአጋርነት ይሰሩበታል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ በተዘጋጀው አገር አቀፍ የስፖርት ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ የስፖርት ክለቦች ማልያዎቻቸውን እንደሚያስተዋውቁ፣ የተለያዩ ስፖርታዊ ቁሳቁሶችንና ማሊያዎችን ለሽያጭ እንደሚያቀርቡ የየክለቦቻቸውን ታሪካዊ ዳራ በፎቶዎችና በቪዲዮ ምስሎች እንደሚያቀርቡበት ታውቋል፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ኢትዮጵያ ቡና፤ ደደቢት እና ንግድ ባንክ በዚሁ ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ በግንባር ቀደምነት ለመሳተፍ ከተመዘገቡት መካከል ይገኙበታል፡፡  በሌላ በኩል የስፖርት እቃ አምራች፣ አስመጪና አከፋፋይ ድርጅቶች በኤግዚብሽኑና ባዛር ላይ እንደሚሳተፉ ሲታወቅ ምርትና አገልግሎታቸውን የማስተዋወቅና የመሸጥ እድል እንደሚያገኙበት ይጠበቃል፡፡ ከስፖርቱ ጋር በተያያዘ የሚንቀሳቀሱ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በኤግዚቢሽንና ባዛሩ ላይ መሳተፋቸው በገራ ለመስራት ያሉ ጥረቶችን እንደሚያበረታታ ተገልጿል፡፡

Read 2016 times