Saturday, 10 January 2015 09:49

“አስታራቂ” እና “ልብ በ40 ዓመት” ኮንሰርቶች ዛሬ ይካሄዳሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በአዲስ ዓመት ዋዜማ “አስታራቂ” በሚል ርዕስ አልበም አውጥቶ ከፍተኛ ተቀባይነት ያገኘው ድምፃዊ አብነት አጐናፍር “አስታራቂ” የተሰኘ ኮንሰርት ዛሬ በጊዮን ሆቴል ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ያቀርባል፡፡ የተለያዩ ድርጅቶች በጋራ ባዘጋጁት በዚህ ኮንሰርት ላይ ሚካኤል በላይነህ ከዘመን ባንድ ጋር የቀድሞ ስራዎቹን ካቀረበ በኋላ ዋናው የኮንሰርቱ አቅራቢ አብነት አጐናፍር በ “ኬር” ባንድ በመታጀብ ተወዳጅ ስራዎቹን እንደሚያቀርብ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ጊዮን ሆቴል ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ በሩ የሚከፈት ሲሆን ከ10-12 ሰዓት በዲጄ ሙዚቃ እና በወጣት ድምፃዊያን፣ እንዲሁም በሚካኤል በላይነህ ስራዎች ታዳሚዎች እየተዝናኑ ቆይተው ወደ አብነት ስራዎች ይሸጋገራሉ ተብሏል፡፡ የኮንሰርቱ መግቢያ ለቪአይፒ 650 ብር ሲሆን ሌላው በ400 ብር እንደሚታደም ታውቋል፡፡
በተያያዘ ዜና ወጣቱ ድምፃዊ አቤል መሉጌታ ዛሬ ምሽት በኤግዚቢሽን ማዕከል “ልብ በ40 ዓመት” የተሰኘ ኮንሰርቱን ያቀርባል፡፡
በሀለ ኮሙኒኬሽን ኤንድ ኤቨንትስ ባዘጋጀው በዚህ ኮንሰርት ላይ ድምፃዊ አቤልን “ጊዜ ባንድ” ያጅበዋል የተባለ ሲሆን፤ በዲጄ ኪንግሰትን (ወዝወዝ) ፋታ እየወሰደ ስራዎቹን እስከ ምሽቱ 3፡00 ሰዓት ለታዳሚው እንደሚያቀርብ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኤግዚቢሽን ማዕከል በር ከዘጠኝ ሰዓት ጀምሮ ክፍት የሚሆን ሲሆን መግቢያው አንድ መቶ ብር እንደሆነም ታውቋል፡፡

Read 1337 times