Saturday, 13 December 2014 10:09

ታዋቂዋ ኒዘርላንዳዊት ተዋናይት የፕላን ኢንተርናሽናልን ሥራዎች ጐበኘች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በበርካታ ፊልሞችና የሪያሊቲ የቲቪ ፕሮግራሞች ላይ በትወና የተሳተፈችው ታዋቂዋ ኔዘርላንዳዊት ተዋናይት ላውራ ፓንቲኮሮቮ ፕላን ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ እያከናወናችው የሚገኙ ሥራዎችን ጐበኘች፡፡
“Because I’m a girl” በሚል መሪ ቃል በፕላን ኢንተርናሽናል የሚሰሩትንና የሴቶችን አቋመ በማጐልበትና ህይወታቸውን በመቀየር ላይ ትኩረት ያደጉትንና በደቡብ ክልል የተሰሩትን ሥራዎች የጐበኘችው ተዋናይቷ ባየችው ነገር እጅግ መደነቋንና ሴቶች በእውቀትና በልምድ የዳበር ሰብእና እነዲኖራቸው የሚደረገው ጥረት ሊቀጥልና ሊበረታታ የሚባው እንደሆነ ተናግግራለች፡፡
ተዋናይቷ ከትናንት በስቲያ በጁፒተር ሆቴል በሰጠችው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገረችው ሴቶች በእውቀት ታንፀው ሲያድጉ አቅም ያላቸው በቀላሉ የማይወድቁ በመሆኑ በዚህ ሴቶችን በማብቃቱ ተግባር ላይ የበኩሏን አስተዋፅኦ ለማድረግ ወደ ኢትዮጵያ መምጣቷ እንዳስደሰታት ገልፃለች፡፡
ኔዘርላንዳዊቷ ተዋሃይት ከተሳተፈችባቸው ፊልሞች መካከል X-factory, Stars dancing on ice, my dirty greasy, nasty fiancé, and I’m a star get me out of here የተሰኙት ይጠቀሳሉ፡፡ ተዋናይ ላውራ ለአራት ቀናት በኢተዮጵያ ያደረገችውን ቆይታ አጠናቃ ከትናንት በስቲያ ወደ አገሯ ተመልሳለች፡፡

Read 1132 times