Monday, 06 October 2014 08:43

ህፃናት ለእግዚአብሔር የፃፉት ደብዳቤ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ውድ እግዚአብሔር፡-
ወንድሜ ቶሎ ቶሎ ሽንቱን ይሸናል፡፡ እኔ ግን አይመጣብኝም፡፡ ለእኔ ብዙ ያልሰጠኸኝ አልቆብህ ነው?
ናቲ- የ5 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
ኤሊዬ ሞታብኛለች፡፡ ጓሮአችንም ቀብረናታል፡፡ አሁን ካንተ ጋር ናት እንዴ ?
ከሆነች ሰላጣ በጣም ትወዳለች እሺ፡፡
ዴቭ- የ5 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
ትልቅ ስሆን ቅርጫት ኳስ መጫወት እፈልጋለሁ፡፡ በደንብ መጫወት እንድችል ቆዳዬን ጥቁር አድርግልኝ፡፡ ቁመቴንም በጣም አርዝምልኝ፡፡
አሌክስ- የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
ወዳንተ ስፀልይ ደስ ይልሃል አይደል? እኔም ደስ ይለኛል፡፡
ጄሪ- የ7 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
የሰንበት ት/ቤት አስተማሪዬ አንተ ሁልጊዜ እንደምትወደኝ ነግራኛለች፡፡ እውነቷን ነው? ትላንት ሳራ ላይ ያንን ነገር ካደረኩም በኋላ ትወደኛለህ? አውቀኸዋል አይደል?! በጣም አዝናለሁ፤ አሁንም ብትወደኝ ግን ደስ ይለኛል፡፡
ቤቲ - የ7 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
አያቴ ልትሞትብኝ ነው፡፡ አንተ እንደምትፈልጋት ነግራኛለች፤ እኔ ግን እዚህ አብራኝ እንድትሆን እፈልጋለሁ፡፡ሌላ የፈለግኸውን ሰው መውሰድ ትችላለህ፡፡
ለእኔ ያለችኝ እሷ ብቻ ናት፡፡ እባክህን ከህመሟ ድና አብራኝ እንድትሆን አድርጋት፡፡
ጆኒ- የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
ለምንድነው እባብና ሸረሪቶችን የፈጠርከው? በጣም እኮ ነው የምፈራቸው፡፡
ጄሪ- የ6 ዓመት ህፃን

Read 1817 times