Monday, 06 October 2014 08:41

“መረቅ” ነገ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በደራሲ አዳም ረታ የተጻፈው “መረቅ” የረጅም ልቦለድ መጽሃፍ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የደራሲው አድናቂዎችና የጥበብ ቤተሰቦች በተገኙበት ነገ ጧት በሃገር ፍቅር ቲያትር አዳራሽ ይመረቃል፡፡
ለረጅም አመታት በውጭ አገራት የኖረው ደራሲ አዳም በሚገኝበት በሚከናወነው የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ፣ የተለያዩ ስነ-ጽሁፋዊ ዝግጅቶች የሚቀርቡ ሲሆን፣ ስለደራሲው ስራዎችም ማብራሪያ ይሰጣል፡፡
ለደራሲው ስምንተኛ ስራው የሆነውና 600 ገጾች ያሉት “መረቅ”፣ በሶስት ዋና ዋና ክፍሎች የተዋቀረ ሲሆን የመሸጫ ዋጋውም  120 ብር ነው፡፡

Read 2028 times