Saturday, 28 June 2014 13:10

“Visual Art Meets Fashion” ለ3 ቀናት ይጎበኛል ከ60 በላይ ሰዓሊያንና ቀራፂያን ይሳተፋሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በመርሲ ዲኮር ዲዛይንና ሞዴሊንግ ማሰልጠኛ ተቋም ለሁለተኛ ጊዜ የተዘጋጀ “Visual Art Meets Fashion” የተሰኘ የስዕልና ቅርፃ ቅርፅ አውደ ርዕይ ትላንት ከምሽቱ 11 ሰዓት ላይ ቦሌ መድኃኒዓለም አካባቢ በሚገኘው ካሌብ ሆቴል የተከፈተ ሲሆን መታሰቢያነቱ ለአርቲስት አለ ፈለገሰላም እና እጅግ ለተከበሩ ለዓለም ሎሬት ዶ/ር ሜድ ጥበቡ የማነብርሃን እንደሆነ ታውቋል፡፡ ትላንት በመክፈቻው ዕለት በዲዛይነር ምህረት ምትኩ የተሰናዳ የፋሽን ትርኢት የቀረበ ሲሆን የ57 ሰዓሊያንና የ6 ቀራፂያን ሥራዎች አውደርዕይ ተከፍቷል፡፡ አውደርዕዩ እስከፊታችን ሰኞ ምሽት ድረስ ለተመልካች ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡ ማሰልጠኛ ተቋሙ ባለፈው ዓመት ለተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ መታሰቢያነት ተመሳሳይ አውደርዕይ አዘጋጅቶ እንደነበር በላከው መግለጫ አስታውሷል፡፡

Read 1987 times