Saturday, 12 December 2015 11:44

ዓለም አቀፍ የሪል ኢስቴትና ኮንስትራክሽን ግብአቶች ኤግዚቢሽን ሊካሄድ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

     በሪል ኢስቴትና በኮንስትራክሽን ግብአቶች ላይ ያተኮረ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽን ለሦስት ቀናት ሊካሄድ ነው፡፡
አጀት ፕሮሞሽን ከመከር ሪል ስቴት ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና Home up የተሰኘው ይኸው ኤግዚቢሽን፣ በኮንስትራክሽኑ ዘርፍ የተሰማሩ አካላትን እርስ በርስ ለማገናኘትና የገበያ ትስስርን እንዲፈጥሩ ለማድረግ ከማስቻሉም በላይ ልምድና ተሞክሮአቸውን እንዲለዋወጡ እንዲሁም ከአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ጋር እንዲተዋወቁ በማድረግ በከተሞች ውስጥ የሚታየውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ ጥረግ በማድረግ ላይ የሚገኙትን የዘርፉን አካላት እንደሚያግዝ ተገልጿል፡፡
በሀርመኒ ሆቴል በተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ኤግዚቢሽኑ የግሉን ዘርፍ ከመንግስት አካላት ጋር በማገናኘትና በማወያየት በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ለማስወገድ እንደሚረዳ የጠቆሙት የአጀት ፕሮሞሽን ዋና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሪት ኤልሳቤጥ አድነው፣ ከዚህ በተጨማሪም በኮንስትራክሽኑ ዘርፍ እየታየ ያለውን የመረጃ ክፍተት በመሙላት ኢንዱስትሪው አድጎ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆን ያግዛል ብለዋል፡፡
በኤግዚቢሽኑ የአገር ውስጥና የውጭ አገር የሪል ኢስቴት አልሚዎች፣ የኪንስትራክሽን ግብዓት አቅራቢዎች፣ ፈርኒቸር አምራቾችና የፋይናንስ ተቋማት ተሳታፊ እንደሚሆኑም ተገልጿል፡፡ 

Read 1345 times