Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

ከአካል ብቃት ግንባታ ስፖርተኝነት፣ ወደ ፊልም ተዋናይነት ከዚያም ወደ ፖለቲካው ገብቶ የካሊፎርኒያ አገረ ገዢ የነበረው ሸዋዚንገር ወደፊልም ስራው ተመልሶ ትወናውን ቀጠለ፡፡ አርኖልድ ሸዋዚንገር በኒው ሜክሲኮ እየተሠራ ባለው “ዘ ላስት ስታንድ” ፊልም ላይ በመሪ ተዋናይነት ይሳተፋል፡፡ በላዩንስ ጊት የሚሠራው ፊልሙ ባለፈው ሰሞን ቀረፃውን በመጀመሩ መደሰቱን የገለፀው አርኖልድ ሸዋዚንገር፤ በአዲሱ ፊልሙ ላይ የሎስ አንጀለስ ፖሊስ የነበረ አንድ ግለሰብ በአነስተኛ የድንበር ከተማ በሸሪፍነት አገልግሎት የሚሸጥ ገፀባህርይን ይተውናል፡፡

ድምፃዊና የዘፈን ደራሲዋ ቴይለር ስዊፍት፤ የቢልቦርድ የዓመቱ ምርጥ ሴት ተብላ መመረጧን ሮይተርስ ከሎስ አንጀለስ ዘገበ፡፡ በ21 ዓመቷ ይህን ሽልማት በማግኘቷም የመጀመሪያዋ ወጣት አርቲስት ሆናለች፡፡ ቴይለር ስዊፍት ሰሞኑን ከሆሊውድ ሪፖርተር ጋር ባደረገችው ቃለምልልስ፤ ለቀጣይ አልበሟ 25 የዘፈን ግጥሞችን ጽፋ መጨረሷን ተናግራለች፡፡

ራፐሮቹ ኤሚነምና ሊል ዋይኔ ከሮሊንግስቶን ባንድ ጊታር ተጨዋች ኬዝ ሪቻርድስ ጋር “ጐድ ኦፍ ሮክ” በሚል ስያሜ መወደሳቸው ታወቀ፡፡ 43 አርቲስቶችን “ጐድ ኦፍ ሮክ” በሚል ርእስ አወድሶ ዘገባውን የሰራው ጂኪው የተባለ መፅሄት ሲሆን ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ለንባብ ይበቃል፡፡
ኤሚነም ወደ ራፕና ሂፕሆፕ ሙዚቃ ከመግባቱ በፊት በሮክ ሙዚቃ ስልቶች ሲያቀነቅን እንደነበር የተዘገበ ሲሆን፤ ራፐሩ ሰሞኑን 39ኛ ዓመት የልደት በዓሉን እንዳከበረ ታውቋል፡፡ ኤሚነም ከጂኪው መፅሄት ጋር ባደረገው ቃለምልልስ በ2000 እኤአ ላይ ዘ ማርሻል ማዘርስ ኤልፒ ብሎ በሰራው አልበሙ 6 ሙዚቃዎችን በሮክ ስልት ሰርቶ እንደነበር አስታውሶ በወቅቱ እነዚህ ዘፈኖች ስለተሰረቁበት በብስጭት ምትክ ዘፈኖቹን በራፕ እንዳቀነቀናቸው ተናግሯል፡፡

“መዝናናት መዝናናት፣ አሁንም መዝናናት!”(ጓድ ሌኒን) 
የተከበራችሁ አንባብያን፡-
አሀዱ
ባለፈው እትም “ህይወታችን በተአምራት አለም” በሚል ርእስ ዝርያችን ባለፉት ሩብ ሚልዮን አመታት ከዋሻ ጨለማ ተነስቶ እስከ ቤተ መንግስት ብርሀን የመጣበትን መንገድ ዋና ዋና ምእራፎቹን በጨረፍታ አይተናል፡፡ አብዛኛው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ግኝቶችንና ፈጠራዎችን የተመለከተ ነበር፡፡ ተጨባጭ ስጋዊ ነበሩ እንበልና፣ ዛሬ ደግሞ ሀሳባዊና መንፈሳዊ ዘርፎችን ለመዳሰስ እንሞክራለን (ጭብጣችን “ሀይማኖት” አይደለም፣ “Anthropology ሀይማኖትን በምን አይነት መነፅር እንደሚመለከት” ነው እንጂ)

የትምህርት ታሪክዎ ምን ይመስላል? 
ከጀማሪ አንስቶ እስከ 12ኛ ክፍል የተማርኩት በትውልድ መንደሬ በሚገኘው ካራማራ ትምህርት ቤት ሲሆን በ1958 ዓ.ም ዓለማያ ዩኒቨርሲቲ በመግባት ታሪክ ማጥናት ጀመርኩ፡፡ የዩኒቨርሲቲ ትምህርቴን ከሁለት ዓመት በላይ መቀጠል አልቻልኩም፡፡ በዘመኑ ወታደር ልዩ ክብርና ሞገስ ስለነበረውና እኔም የሠራዊቱ አባል የመሆን ጠንካራ ፍላጎት ስለነበረኝ፣ ሐረር ጦር አካዳሚ ለስልጠና ማስታወቂያ ሲያወጣ የዩኒቨርሲቲ ትምህርቴን በማቋረጥ በአካዳሚው ተመዘገብኩ በ1959 መጨረሻ በምክትል መቶ አለቃ ማዕረግ ተመርቄ በሠራዊቱ ውስጥ ማገልገል ጀመርኩ፡፡
የውትድርና ሙያ ላይ ፍቅር ያሳደረብዎት በቅርብ የሚያዩት ወታደር ከቤተሰብዎ ነበር?

የአለም ህዝብ ቁጥር እ.ኤ.አ. በጥቅምት 31፣ 2011 ዓ.ም. 7 ቢሊዮን ይደርሳል፡፡ በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ ይህ ህዝብ ወደዚች አለም የመጣዉ በሚድዋይፎች እገዛ ነዉ፡፡ነገር ግን የእርጉዝ ሴቶችን ፍላጎት ለሟሟላትና ጤናማ ወሊድን ለማረጋገጥ የሚድዉፍሪ አገልግሎቶችን ማስፋፋት ያሻል፡፡ሁሉም እርጉዝ ሴቶች ምርጥና ተግባራዊ ሊሆን የሚችል እንክብካቤና ምክር ሊያገኙ ይገባል፤ ይህ ደግሞ እርግዝናና ወሊድን የሚያግዝ ዉጤታማ መረጃ፣ መግባባት እና ክብር ላይ የተመሰረተ ሂደት ሊሆን ይገባል፡፡

“የዘመን ተልእኮና የትውልድ ጥያቄዎች” በሚል ርእስ የቀረበው የዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ፅሁፍ፤ የንጉሱንና የደርግን ዘመን እንዲሁም የኢህአዴግን ዘመን በምሳሌነት ጠቃቅሶ ሃሳቡን ሲቋጭ ውይይትን ይጋብዛል። የአፄ ሃይለስላሴ እና የደርግ መንግስታት፤ የታሪክ ተልእኳቸውን እንደፈፀሙና ከተልእኳቸው ውጭ ምንም ማድረግ እንደማይችሉ ከሄግል ፍልስፍና ጋር አያይዘው የጠቀሱት ዶ/ር ዳኛቸው፤ ወደኋላ ተመልሰን ስለመብት ጥያቄ እያነሳን ብናወግዛቸው ትርጉም የለሽ ነው ይላሉ። በተመሳሳይ መንገድ፤ የኢህአዴግ መንግስት ላይ የሚሰነዘሩ ጥያቄዎችም ትርጉም ላይኖራቸው ይችላል ብለዋል - ፀሃፊው።

አንድ የሩሲያውያን ተረት እንዲህ ይላል:-
አንድ ደሀ ገበሬ ለምስኪን እህቱ፤
“ነገ በጠዋት ተነስቼ ወደ ጫካ እሄዳለሁ” ይላታል፡፡
እህትየውም፤
“ወደ ጫካ ለምን ትሄዳለህ?” ስትል ትጠይቀዋለች፡፡
“አደን ላድን ነው የምሄደው፡፡ ጥንቸል አድኜ ይዤ እመጣና ጥንቸሏን ሸጠን ምግብ እንገዛለን፡፡ ነገ ጠግበን ነው የምናድረው”” ይላታል፡፡
“እስቲ እንዳፍህ ያርግልን” ትላለች፡፡

የአገር ጉዳይ ነው እየተባሉ በየሥፍራው የጥፋት ስንቃቸውን ይዘው የሚዞሩት የመረዳት ችሎታ የሌላቸው ስለሆኑ ነው ወይንስ የሀሰት ንድፈ ሀሣብ ሰለባ በመሆናቸው ነው? ዛሬ ሥርዓቱ ራሱ ተኩሶ የተተኮሰበት ይቅርታ እንዲጠይቀው የሚሻ ነው፡፡
መገንባት እና ማፍረስ ተፈጥሯዊ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ ሊያፈርሱ ተነስቶ መፍረስ እንዳለ ሁሉ ለመገንባት ተዘጋጅቶ ወደ ማፍረስ አዙሪት መመለስም አለ፡፡

ከ6 ሳምንታት በኋላ በአዲስ አበባ ከተማ ጎዳናዎች ላይ ለሚካሄደውና 10ኛው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ሲካሄድ የነበረው ምዝገባ በ9 ቀናት አለቀ፡፡ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዘጋጆች በ10 ኪሎሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድሩ ላይ ተሳታፊ ለመሆን 36ሺ ስፖርተኞች በ9 ቀናት ጊዜ ውስጥ መዝግበው መጨረሳቸውን እንደረኩበት ገልፀዋል፡፡ ለዚሁ ፈጣን የምዝገባ ሂደት የግልና የመንግስት ተቋማት ለሰራተኞቻቸው በአማካይ እስከ 1ሺ ቲሸርት በመግዛት ያረጉት ርብርብ፤ በፖስታቤት በኩል በመላክ እስከ 15ሺ ቲሸርት መሸጡና በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ያለው ፍላጎት መጨመር ምክንያት እንደሚሆንም አስረድተዋል፡፡