Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62

Saturday, 27 August 2011 13:42

የአባቱ ልጅ

የዜማና ግጥም ደራሲ፣ የሙዚቃ መሣሪያዎች ተጫዋችና ድምፃዊ ከነበረው አባቱ ተፈራ ካሣናከተወዛዋዥ
እናቱ ወ/ሮ አረጋሽ ኩምቴሳ መወለዱ ገና በልጅነት  ዕድሜው ስሜቱ ለሙዚቃ እንዲያዳላ ምክንያት እንደሆነው ይናገራል፡፡ ተወልዶ ያደገበት ፈረንሳይ ለጋሲዮን ለበርካታ የጥበብ ሰዎች መፍለቂያ የሆነና አንጋፋ የሙዚቃ ባለሙያዎች የከተሙበት አካባቢ መሆኑ ደግሞ ስሜቱ የበለጠ ከሙዚቃ ጋር እንዲተሳሰር አደረገው፡፡ ጐረቤታቸው የነበረው አንጋፋው ድምፃዊ ጥላሁን ገሠሠና ወላጅ አባቱ ተፈራ ካሣ የሙዚቃ ሥራ ልምምድ ሲያደርጉ ሁሌም ከሥራቸው አይጠፋም ነበር፡፡

በ1973 ዓ.ም. በፈረንሳይ አካባቢ የተወለደው አርቲስቱ፤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በብሔራዊ ኢትዮጵያ፣ ሁለተኛ ደረጃን በተፈሪ መኰንን እንዲሁም ከእንጦጦ ቴክኒክ ኮሌጅ በቲያትር ዲፕሎማውን አግኝቷል፡፡ ..ገመና ቁ.2.. ላይ ዶ/ር ምስክርን ሆኖ የሚጫወተው አርቲስቱ፤ ከጋዜጠኛ ሰላም ገረመው ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል፡፡
እስቲ ዳንኤል ሰውየውና ዳንኤል ተዋናዩ ምን እንደሚመስሉ ግለልኝ . . .  
|ህይወት´ ፊልም ላይ በዳይ አፍቃሪ የነበረና ይቅርታን የሚጠይቅ፣ ..የአውሬው  እርግቦች.. ላይ መቶ አለቃ ሆኖ በሶማሌ ጦርነት ከቤተሰቡ የተለያየ እና እህቱን የሚያፈቅር ወታደር፣ ..እቴጌ.. ላይ ሞኝና በራሱ ያልቆመ አፍቃሪ፣ ..ትስስር.. ላይ የታሪክ መምህር፣ ..ማክቤል.. ላይ ንፁህ አፍቃሪ፣ ..የታፈነ ፍቅር.. ላይ አጭበርባሪ  ..ተስፈኞቹ.. ላይ ለኢትዮጵያ የሚቆረቆር ከሙስና የዳ ሠራተኛ፣ ..ሰውየው.. ላይ  ዱርዬ የሀብታም ሹፌር፣ ..ባቢሎን በሳሎን.. ቲያትር ላይ ቦዘኔ አፍቃሪ፣ ..ገመና ቁጥር 2.. ላይ ዶ/ር ምስክር ነው ዳንኤል ማለት፡፡ የሚገርመኝ ..ባቢሎንን.. ስሠራ ጥሩ ያልሆነ ገ ባህሪ ወክዬ ስለምጫወት ተመልካቹ መጣ ደሞ እንደሚለኝ አውቃለሁ፡፡

በ2001 ዓ.ም. ተጀምሮ በአዲስ አበባና በየክልል ከተሞቹ ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያን አይዶል ውድድር እነሆ ወደመቋጫው ተቃርቧል፡፡ በስድስት ዙሮች የተካሄደውን የድም ውድድር አሸንፈው ለሰባተኛው ዙር ያለፉት አስር ተወዳዳሪዎችም ተመርጠዋል፡፡ የሐረሯ ተወዳዳሪ ህፃን ሃና ግርማ በልዩ ተወዳዳሪነት ለሰባተኛውና ምርጥ አምስቱ ብቻ ለሚመረጡበት ዙር በማለፍ yተወዳዳ ቁጥር አስራ አንድ አድርሳዋለች፡፡

በሆሊውድና በአሜሪካ መዝናኛ ኢንዱስትሪ ያሉ ዝነኞችን ገበና በመፈልፈል የሚታወቀው አንቶኒዮ ፔሊካኒ በወህኒም የተለመደ ስራውን እንደገፋበት ኒውስዊክ ገለፀ፡፡ ፔሊካኒ የዝነኞችን ምስጥራዊ ሰነድ በመፈልፈል፤ ስልክ በመጥለፍና የደህንነት መረብን ሰብሮ በመግባት አደገኛነቱ የተመሰከረለት ጉድ ጎልጓይ ጋዜጠኛ ነው፡፡ በሎስአንጀለስ ከተማ በግል መርማሪነት ይሰራ የነበረው ፔሊካኒ ከ3 ዓመት በፊት ጥፋተኛ ሆኖ በተገኘባቸው 76 ወንጀሎች የ15 ዓመት ኑ እስራት ተፈርዶበት በወህኒ ቤት ይገኛል፡፡

Monday, 08 August 2011 14:06

የ..ሐምሌ ስንኞች..

ባለፈው እሁድ በቢሾፍቱ ሲኒማ አዳራሽ ኪነጥበባዊ ዝግጅቱን ያቀረበው ..ሆራ ቡላ.. ታዋቂዋን አርቲስትና የማስታወቂያ ባለሙያ ሙሉ ዓለም ታደሰና በ..ሰው ለሰው.. ተከታታይ የቴሌቭዢን ድራማ ልጇ ብሩክን ሆኖ የሚሠራውና የድራማው አዘጋጅ አርቲስት ሰለሞን አለሙ ፈለቀን የክብር እንግዶች በማድረግ የጋበዘ ሲሆን አርቲስቶቹ ልምድና እውቀታቸውን ለደብረ ዘይት ወጣቶች አጋርተዋል፡፡

Saturday, 16 July 2011 11:00

1/2 ሌሊት - 1001 ትዝታ

..ኧረ መርሳ በለኝ!.. እያለ ትንሹ ትልቁ ደረሳው ወልዩ በፍቅር የሚወዳት የአባትዬዋን መንበር፤ የሸህ ሚዕዋን መንደር-መርሳን ከተማዬ ሃብሩን ወረዳዬ እያልኩ መኖር ከጀመርኩ አምስት ወር እንኳን አልሞላኝም፡፡ እኔ አንዷንም ሳላቃት የእሷ አድርጋኝ ከወዳጆቿ ቀላቅላ በዱአዋ እቅፍ ድግፍ አድርጋ አቀማጥላ የያችኝ ሃብሩ፤ አንዳንዶች እንደተረኩልኝ ስፋቷ የአንድ ጠቅላይ ግዛት ያህል ቢገዝፍብኝም፤ ጓዳ ጐድጓዳዋን አብጠርጥሬ ላውቀው ምኞቴ ነበር፡፡

Sunday, 24 July 2011 07:50

1/2 ሌሊት - 1001 ትዝታ

አንዴ ራሷን - አንዴ ልቧን - አንዴ ደግሞ እጇን እያመመ ትንሽ ካስጨነቃት በኋላ አሁን ቀለልሳይላት አልቀረም፡፡ ከተኛችበት ተነስታ እግሯን ዘርግታ ተቀምጣለች፡፡ እሷ ህመሟ ሲለቃት እኔ ድካሜ ቁጭ ብዬ እንድቀጥል ስላልፈቀደልኝ ጭኖቿን ተንተርሼ ወገቤን አሳርፌያለሁ፡፡

ከላይ የምትመለከቱት ስዕል የማህጸን ቅርጽ ነው። ማህጸን በተፈጥሮው የምትመለከ ቱትን ስእል ሲመስል አንዳንድ ገዜ ግን የተዛባ ተፈጥሮአዊ ሁኔታ ያጋጥማል። ለመሆኑ ማህ ጸን በመጀመሪያ ሲፈጠር በምን መልክ ነው? የሚከሰተው ተፈጥሮአዊ ችግርስ ምን መሳይ ነው? መፍትሔ ውስ? እነዚህን ጥያቄዎች ይዘን ያመራነው በቀድሞው አጠራሩ ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል በአሁን ደግሞ የቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ ነው። በሆስ ፒታሉ የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስትና ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት ዶ/ር አብዱልፈታህ አብዱልቃድር አብዶሽ ያነሳናቸውን ጥያቄዎች መልሰውልናል። የአምዱ አዘጋጆችም ለንባብ አቅርበነዋል።

በአለም ደሀ በተባሉት ሀገሮች ያሉ ሴቶች በየቀኑ ፀሎት ያደርሳሉ፡፡

ፀሎት የሚያደርሱበት ምክንያትም...

እርግዝና እንዳይከሰት ፣

እርግዝና ቢከሰት ክትትል ሊያደርጉበት የሚችሉበትን ክሊኒክ ርቀት በማሰብ፣

የእርግዝና ክትትል የሚያደርጉበት የጤና ተቋም ከሚኖሩበት አካባቢ እሩቅ በመሆኑ ...ይህን ሁሉ መንገድ ተጉዤ ብሄድ ተቋሙ ክፍት ሆኖ ይቆየኝ ይሆን ከሚል ስጋት፣ወደ ጤና ተቋሙ በሚኬድበት ጊዜ በትክክል ጥያቄዬን የሚመልስልኝ የጤና ባለሙያ አገኝ ይሆን?

በኢትዮጵያ ቅድመ ወሊደ የህክምና አገልግሎት ያገኛሉ የሚባሉት እናቶች ከአጠቃላዩ ሲታይ ወደ 80  አካባቢ ናቸው፡፡ ይህም ቁጥር ባለፉት ጥቂት አመታት ውስጥ እየጨመረ የመጣ ሲሆን ይህም በአገር ደረጃ የተሰማሩ የጤና ኤክስንሽን ባለሙያዎች በጤና ኬላዎች እና እናቶች ባሉበት ቦታ ሁሉ በየመኖሪያ ቤቱ ጭምር አገልግሎቱን መስጠት በመቻላቸው ነው፡፡ ከዛሬ አምስት አመት በፊት የነበረው አገልግሎት ከ30 በታች የነበረ መሆኑ አይዘነጋም፡፡

ዶ/ር ታደሰ ከተማ በኢፊድሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስር የእናቶች ጤና አማካሪ