Administrator

Administrator

 ለገበያ በሚያቀርቡት የመድሃኒት ምርት ላይ የ2600 % የዋጋ ጭማሪ አድርገዋል የተባሉ ሁለት የአሜሪካ ኩባንያዎች፣ በድምሩ የ112.7 ሚ. ዶላር እንዲከፍሉ ባለፈው ረቡዕ በአንግሊዝ ቅጣት እንደተጣለባቸው አሶሼትድ ፕሬስ ዘገበ፡፡
ፒፋይዘር የተባለው መድሃኒት አምራች ኩባንያ እና ፍሊን ፋርማ የተባለው አከፋፋይ ኩባንያ የሚጥል በሽታ ተጠቂዎች በሚወስዱት መድሃኒት ላይ ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ አድርገዋል በሚል በእንግሊዝ የገበያ ተወዳዳሪነት ባለስልጣን ክብረ ወሰን የተመዘገበበት የተባለውን የ112.7 ሚሊዮን ዶላር ቅጣት እንደተጣለባቸው ዘገባው ገልጧል፡፡
ኩባንያዎቹ እ.ኤ.አ በ2013 ኢፓኑቲን በተባለውና በእንግሊዝ ብቻ ከ48 ሺህ በላይ ታማሚዎች ይወስዱታል ተብሎ በሚገመተው በዚህ መድሃኒት ላይ የስያሜ ለውጥና እጅግ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ ተጠቃሚዎችን በዝብዘዋል በሚል ነው ቅጣቱ የተጣለባቸው፡፡
ኩባንያዎቹ በወቅቱ 2.83 ፓውንድ ይሸጥ በነበረውን በዚህ መድሃኒት ዋጋ ላይ ከፍተኛ ጭማሪ በማድረግ በ67.5 ፓውንድ እንዲሸጥ ማድረጋቸው ተጠቃሚዎችን ያለአግባብ በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር እንዲያወጡ አስገድዷል መባሉን የጠቆመው ዘገባው፤ ቅጣቱን የጣለው ባለስልጣን መስሪያ ቤት ዋጋውን እንዲቀንሱ ለኩባንያዎቹ ማስጠንቀቂያ እንደሰጣቸውም አመልክቷል፡፡

 ትራምፕ ስምምነቱን እንዲያፈርሱ አልፈቅድም ብላለች

        ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት ቃል የገቡትን የኒውክሌር ስምምነት የማፍረስ ሃሳብ ተግባራዊ እንዲያደርጉ አገራቸው እንደማትፈቅድላቸው  የገለጹት የኢራን ፕሬዚዳንት ሃሰን ሩሃኒ፤ ትራምፕ ስምምነቱን የሚያፈርሱ ከሆነ ግን የከፋ ነገር እንደሚከሰት ማስጠንቀቃቸውን ሲኤንኤን ዘግቧል፡፡
ተሰናባቹ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ የኒዩክሌር ስምምነቱን በመጣስ አሜሪካ በኢራን ላይ ከጣለቻቸው ማዕቀቦች አንዳንዶቹ ለ10 አመታት እንዲራዘሙ የሚፈቅደውን ህግ በፊርማቸው የሚያጸድቁ ከሆነ፣ አገራቸው ምላሽ እንደምትሰጥና ይህም አሜሪካን አላስፈላጊ ዋጋ እንደሚያስከፍላትም ሩሃኒ አስጠንቅቀዋል፡፡
ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት አገራቸው ከፈረመቻቸው አደገኛና አክሳሪ ስምምነቶች መካከል፣ ባለፈው የፈረንጆች አመት 2015 ከኢራን ጋር የተፈጸመው የኒውክሌር ስምምነት አንዱ መሆኑን በመጥቀስ፣ ስልጣን ከያዙ ለውጥ የሚያደርጉበት አንደኛው ጉዳይ ይህ ስምምነት እንደሆነ በተደጋጋሚ መናገራቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ ፕሬዚዳንት ሩሃኒ ግን ባለፈው ማክሰኞ ባደረጉት ንግግር ትራምፕ ስምምነቱን ለማፍረስ ከሞከሩ፣ መንግስታቸውና ህዝባቸው በዝምታ እንደማይመለከቱ አስጠንቅቀዋል፡፡
“አሜሪካ ጠላታችን መሆኗ አንዳች እንኳን የማያጠራጥር ሃቅ ነው፣ በቻለቺው አቅም ሁሉ በእኛ ላይ ጫና ለማሳደር ትፈልጋለች” ያሉት ፕሬዚዳንት ሩሃኒ፤ ሰውዬው ወደ ስልጣን ሲመጡ የተለያዩ የለውጥ ተግባራትን የመፈጸም ፍላጎት አላቸው፣ ያም ሆኖ ግን ትራምፕ ከሚወስዱት እርምጃ ኢራንን ተጎጂ የሚያደርግ አንድ እንኳን አይኖርም ብለዋል በቴህራን ዩኒቨርሲቲ ባደረጉት ንግግር፡፡ ኢራን ለአለማቀፍ ሰላም ስጋት አይደለቺም፣ አለም በእኛ ላይ የተዛባ አመለካከት እንዲኖረው ያደረገው የአሜሪካና የእስራኤል ፕሮፓጋንዳ ነው ብለዋል- ፕሬዚዳንት ሩሃኒ፡፡
ኢራን የኒውክሌር ፕሮግራሟን በተመለከተ ከአሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ቻይና፣ ሩስያና ጀርመን ጋር በ2015 ስምምነት መፈጸሟ ይታወሳል፡፡

 “ጦቢያ ጃዝ” 65ኛውን የግጥም በጃዝ ምሽት የፊታችን ረቡዕ ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ በራስ ሆቴል አዳራሽ ያካሂዳል፡፡
በዚህ ኪነ ጥበባዊ ፕሮግራም ላይ አንጋፋና ወጣት ገጣሚያን ‹‹ነፃ አውጭ›› በተባለው የሙዚቃ ባንድ ታጅበው ግጥሞቻቸውን ለታዳሚው እንደሚያቀርቡ ታውቋል፡፡ የጥበብ ምሽቱ አዘጋጅ እናት የማስታወቂያ ስራዎች ድርጅት ለአዲስ አድማስ እንደገለጸው፤ በመድረኩ ከግጥሞች  በተጨማሪ ዲስኩርና መነባንብም ይቀርባሉ፡፡ 

 የመጽሐፉ ርዕስ፡- ዘፍ ያለው
                  ደራሲ፡- ሌተና ኰሎኔል ተፈራ ካሣ
                   የገጽ ብዛት፡- 340
                    ዋጋ፡- 150 ብር
             ገምጋሚ፡- ብርሃነሥላሴ ኃ/መስቀል

     ማርክ ክራመር  በቀዝቃዛው ጦርነት ዙሪያ  በኤም አይ ቲ ፕሬስ የሚዘጋጀው ‹‹ዘ ጆርናል ኦፍ ኮልድ ዎር››  የተሰኘው ጆርናል ኤዲተር ነው፡፡ “ሰፓይስ” በሚል ርዕስ በዚህ ጆርናል ላይ በተካተተው ጽሑፍ መግቢያ ላይ “Espionage and covert operations are notoriously difficult to study” ይላል- ስለላና ምሥጢራዊ ዘመቻዎችን ማጥናት የቱን ያህል አስቸጋሪ  እንደሆነ ሲያብራራ፡፡
እነዚህን ተግባራት ለማጥናትና ጽሑፎችን ለመጻፍ በድርጊቱ ውስጥ ተዋናይ መሆንንን ይጠይቃል፡፡ ያ ደግሞ ሕይወትን ሊያስከፍል ይችላል፡፡ እንደዛም ሆኖ በእንደነዚህ ዓይነት ተግባራት ላይ ምሥጢራዊነት እጅግ ስለሚበዛ በድርጊቱ ውስጥ ተሳታፊ ሆነውም የተሟላ መረጃ ለማግኘት እጅግ አዳጋች እንደሆነ ይታመናል። ለዚህም ነው የስለላና ምሥጢራዊ ዘመቻዎችን የተመለከቱ ታሪኮች “በስማ በለው!” ሳይሆን ድርጊቱ ውስጥ በነበሩ ግለሰቦች  ሲተረኩ እጅግ ጣፋጭና ተዓማኒነት ያላቸው የሚሆኑት፡፡
የስለላ ሥራ በዓለም ላይ መቼ እንደተጀመረ እስካሁን ድረስ በግልጽ ባይታወቅም ከክርስቶስ ልደት በፊት እንደተጀመረ ይነገራል፡፡ በሁለቱ የዓለም ጦርነቶች፤ በተለይም ደግሞ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የስለላ ተግባር ጎልቶ የወጣበት ጊዜ ነበር፡፡ የጦርነቱን መገባደድ ተከትሎም በቀዝቃዛው ጦርነት ውስጥ እራሳቸውን ያገኙት ኃያላን ሀገራት፤ በምድሪቱ ላይ የኃይል ሚዛኑን የበላይነት ለመረከብ በምዕራቡና በምሥራቁ ጎራ ተሰልፈው ከባድ ወደ ሆነ መጠላለፍ ውስጥ ገብተው እንደነበር የሩቅ ጊዜ ትዝታ አይደለም፡፡
የቀዝቃዛው ጦርነት የማይረሳ ዋነኛ መለያውም በጊዜው ይከናወኑ የነበሩ “የሾተላዩ ሰላዮች” ዓይነት ለሁለት ወገን የሚሠሩ የምሥጢራዊ ወኪሎችና የበላይነቱን ለመያዝ በየቦታው የሚፈፀሙ ግድያዎች ታሪክ ነበር፡፡ ይህ ታላቅ ምሥጢራዊነትንና ግለሰቦችን መንታ ሰብዕና እንዲኖራቸው ያደርግ የነበረ ተግባር፣ ጠላት ተብለው የተፈረጁ ሃገራት መንግሥታዊ መዋቅርና ተቋማት ውስጥ ሰርጎ ለመግባት የሚያስችል ጥበብ የታከለበት ነበር፡፡
የወቅቱ ኃያላን ሃገራት በተለይም ደግሞ፣ አሜሪካና ሶቭየት ሕብረት በእጅጉ እዚህ ተግባር ውስጥ ተዘፍቀው ነበር፡፡ የስለላን ሥራ በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችና በረቀቁ ዘዴዎች ለመደገፍ፣ የበቁ ሰላዮችንና ምሥጢራዊ ወኪሎችን ለመመልመል  ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ወጪ ያደርጉ እንደነበርም ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ በተመሳሳይ ቡድን ውስጥ የተካተቱ ሃገራት እየተጣመሩ የተቃራኒን ጎራ የስለላ መዋቅር ለመበጣጠስ ጥረት አድርገዋል፡፡ አንዱ በአንዱ ቡድን ላይ የበላይነቱን ለመውሰድ በብርቱ ሲደክሙ እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ይመሰክራሉ። ጠላት በሚሏቸው ሃገሮች ላይ ሰላዮቻቸውን በመበተን የየሃገራቱን ምሥጢር ሲቦጠቡጡ፣ ወታደራዊ አቅማቸውን፣ የሚያደርጓቸውን ዝግጅቶችና የሚያራምዷቸውን ርዕዮተ ዓለሞች ሲሰልሉ፣ ፖለቲከኞችንና የተቃራኒ ጎራ ወኪሎችን ሲያስገድሉና ሲያሳፍኑ መዋል የዕለት ተዕለት ተግባራቸው ነበር፡፡
እነዚህ “የኢምፔርያሊስቱና የሶሻሊስቱ ጎራ” በሚል የተሰለፉ ሃገራት፣ በተለይ ከ1940ዎቹ አንስቶ በአፍሪካ ሃገራት ላይ የነበራቸውን ተቀባይነት ለማስፋፋት መረቦቻቸውን ዘርግተው የተንቀሳቀሱበት ወቅትም ነበር፡፡ በየሃገራቱ ላይ መረቦቻቸውን በመዘርጋት ሊያራምዱት የሚፈልጉትን ተግባር ለማከናወን ረቀቅ ያሉ የስለላ መዋቅሮችን በአፍሪካ ሃገራት ላይ ዘርግተው ተንቀሳቅሰዋልም፡፡    
በዚያን ወቅት ኃያላኑ ሃገራት የየጎራዎቻቸውን ርዕዮተ ዓለም በሌሎች፣ በተለይም ደግሞ አዳጊ በሚባሉት ሃገራት ላይ ለመጫን ሲጣደፉም የነበረበት ወቅት ነው። ስትራቴጂካዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባላቸው እንደ ምሥራቅ አፍሪካ ባሉ ቦታዎች፣ በተለይም በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የነበረው የሁለቱ ጎራዎች ትንቅንቅና ሽኩቻ ደግሞ እጅግ አስገራሚና ፍትጊያ የበዛበት እንደነበር ታሪክ ይነግረናል፡፡ በዚህ ሽኩቻ ውስጥ ኢትዮጵያ አጭር በሚባል የጊዜ ልዩነት ውስጥ የሁለቱንም ጎራዎች ርዕዮተ ዓለም ተቀብላ ያስተናገደችበት ታሪካዊ አጋጣሚም ተፈጥሮ ነበር፡፡ መጀመሪያ ከምዕራቡ አለም ጋር ወግና የነበረችው ኢትዮጵያ፤ ከአብዮቱ መፈንዳት በኋላ ደግሞ ወደ ምሥራቁ አለም ጠቅልላ የገባችበት ሁኔታ ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ነው  እ.ኤ.አ በ1977 ዓ.ም ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ጋር አድርጋው የነበረው ጦርነት፤ የቀዝቃዛው ጦርነት አስተሳሰብ የተንጸባረቀበት ጦርነት ተደርጎ የሚወሰደው፡፡  ከ1960ዎቹ መጀመሪያ አንስቶ እስከ አብዮቱ መባቻ ድረስ ኢትዮጵያ በተለያዩ ጉዳዮች ተወጥራ፣ ከወዲያ ወዲህ መላወስ ተስኗት የከረመችበት ጊዜ ነው፡፡ በወቅቱ በሹማምንቱ መካከል የነበረው የእርስ በእርስ ሹክቻ የገነገነበት ጊዜ ነበር፡፡ ይህም ሃገሪቱ በሰከነ መንፈስ የውጭ ጠላቶቿን ሁኔታ እንዳትከታተል እንቅፋት ሆኖባታል፡፡ በስለላና በአፈናው መረብ ተወጥራ እንደነበር፣ የሌተናል ኮሎኔል ተፈራ ካሣ ‹‹ዘርፍ ለው የተሰኘ መፅሃፍ ይገልፃል (ገፅ 314) የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች “ሃገሪቱ ለውጥ ያስፈልጋታል! መሬት ላራሹ!”። የሚለውን የትግል እንቅስቃሴያቸውን በተደራጀ ሁኔታ አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ በሰሜኑና ሰሜን ምሥራቅ የሃገሪቱ ክፍል አሰቃቂ ረሀብ ተከስቶ፣ “ገባሩ ሕዝብ በጠኔ ተመትቶ እንደ ቅጠል እየረገፈ ነው፡፡ ‹‹የሚቆረጥልን ደመወዝ አንሶናል፤›› የሚሉ ወታደሮች በሃገሪቱ አራቱም አቅጣጫ በጉርምርምታ ላይ ናቸው፡፡ ለንግሥና ያቆበቆቡ የቤተ መንግሥት ሰዎች፣ አፍንጫቸውን ነፍተው በንጉሡ ዙሪያ ተሰባስበው የሚሆነውን በጉጉት ይጠባበቁ ይዘዋል፡፡ ሹማምንቱና መኳንንቱ የአስተዳደር ሥራዎቻቸውን ቸል ብለው በየራሳቸው የግል የንግድ ሥራ በመጠመዳቸው በሃገሪቱ የፍትህና የአስተዳደር ተግባር እንዲዳከም ሆኖ፣ የመንግሥት መዋቅሩ በህዝብ ብሶት እየተንገጫገጨ ነው”  ከዚህም ባሻገር፣ ሹማምንቱ በተማሪ አመፅና ተቃውሞ ስም ወረቀት እያስበተኑ ንጉሡ የተሳሳተ ውሳኔ እንዲያሳልፉ ሊያደርጉ ሲሞክሩ ጥበበኞቹ የህዝብ ደህንነት ባለሙያዎቻችን ደርሰውበት ውርደትን እንዲከናነቡ አድርገዋቸዋል ይላል  መፅሀፉ፡፡ (ገፅ 172)
በእነዚህ ሁሉ ጉዳዮች መላወሻ ያጡት ሃገሪቱና ንጉሡ በትካዜ ተውጠዋል፡፡ አዛውንቱ ንጉሥ ከላይ የተዘረዘሩት ጉዳዮች በአዕምሯቸው እየተመላለሱ እረፍት ቢነሷቸውም፣ አልጋቸውን ወርሶ ሃገሪቱን ወደ ቀጣይ ምዕራፍ የሚያሸጋግራት ሁነኛ ሰው የማጣታቸው ነገር ቢያብሰለስላቸውም ተስፋ ግን አልቆረጡም፡፡ በዋነኛነት ዘወትር አያሳፍረኝም በሚሉት ፈጣሪያቸው ተማምነዋል። ከፀሎትና እምነት በሻገርም ታማኝና ትጉህ ናቸው ከሚሏቸው ባለሟሎቻቸው ጋር ሆነው የጎበጠውን ለማቅናት፣ የደፈረሰውን ለማጥራት፣ የፈሰሰውን ለማፈስ፣ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ አብዝተው ይደክማሉ፤ ይዘክራሉ፡፡ በአዛውንት ጉልበታቸው  ጎንበስ  ቀና ይላሉ። በዚህ መካከል ግን፣  “ሲያመጣው ልክ የለው” እንዲሉ፣  ሃገሪቱንና ንጉሠ ነገሥቱን ከሌላ አቅጣጫ የሚወጥር ክስተት ተከስቷል ይሉናል ደራሲው፡፡   
ከዚህ ሁሉ ውጥረት በስተጀርባ ከብዙሃኑ የአገሬው ሰው የተሰወረ የአፈናና የስለላ ትንቅንቅን፣ በአለም የኃይል ሚዛን ላይ በከባድ ሚዛን ምድብ ውስጥ የተመደቡ ሃገራትን የስለላ አቅም የፈተነ፣ የድሀይቱን ምሥራቅ አፍሪካዊት ሃገር፣ የኢትዮጵያን “የህዝብ ጸጥታ ጥበቃ መሥሪያ ቤት” አገርን ያኮራ ተግባር የሚያስቃኝ መጽሐፍ ነው- ‹‹ዘፍ ያለው››፡፡
“ማን ይናገር የነበረ ማን ያርዳ የቀበረ” እንደሚባለው፣ ኰሎኔሉ፣ “አስጨናቂና እንቅልፍ አልባ የአፈና እና የስለላ ትንቅንቅ” በሚል መፅሃፍ ውስጥ በገለፁት ተልዕኮ ወስጥ ተሳታፊ የነበሩ፣ የሕዝብ ጸጥታ ጥበቃ መሥሪያ ቤት ባልደረባ መኮንን ናቸው፡፡  ደራሲው ጥብቅ ምሥጢሮችን አዋቂ እንደሆኑም ከታሪኩ ለመገንዘብ ይቻላል፡፡ ምሥጢር አጠባበቅን በተመለከተ እንዲህ ያስረዳሉ፡- “በምሥጢር የተሠራ በግልም ሆነ የአገር ጉዳይ እስከነ አካቴው /መጨረሻው/ ድረስ ተደብቆ ምሥጢር ሆኖ አያልፍም፡፡ ምሥጢር ሽታ አለው፣ የሚተንም ነው፡፡ የተወሰነ ዕድሜም አለው…”
ማናቸውም የአገርንና የሕዝብን ጥቅምና ደህንነት ለማስጠበቅ የሚደረጉ ምሥጢር ነክ ጉዳዮች ሁሉ ሊሸከሟቸው በሚችሉ ዜጎች አዕምሮ ውስጥ መቆለፍ እንዳለባቸው እሙን ነው፡፡ የአገርን ምሥጢርን ጠብቆ እስከ ውጤትም ማቆየት፣ ከውጤትም በኋላ ቢሆን፣ የምሥጢርን ዕድሜ በትንሹ ከሃያ እስከ ሠላሳ ዓመት ማቆየት” ጠቃሚ ነው ይሉናል፡፡ ዛሬም ልጆቻቸው ከዓመታት በኋላ መጽሐፉን ለህትመት ብርሃን ሲያበቁት፤ “የአሳታሚው ማስታወሻ” በሚለው ስር፣ ልጃቸው ቴዎድሮስ ተፈራ ከገለፀው መረዳት እንደሚቻለው፣ ከመጠነኛ አርትኦትና ከአንዲት ሃረግ በስተቀር የቀነሰውና የጨመረው የለም፡፡
የኢትዮጵያና የሶማሊያ ጉዳይን ዋነኛ መሠረት አደርጎ የተዋቀረው “ዘፍ ያለው” የተሰኘው መፅሃፍ፤ “የተደገሰን የእልቂት ሽል ማጨናገፍ አስፈላጊነቱን አምነውበት ከአገራቸው ወደ ኢትዮጵያ ተሰደው የነበሩት የሶማሊያ አየር ኃይል አዛዥ ኰሎኔል ጋሌብ ሐጂ ዩኒስ አሊ፤ ወደ ኢትዮጵያ በመሰደዳቸው ብቻ በኢትዮጵያ ላይ ሠይጣናዊ ጠላትነት ያሳደሩ ሦስት አገሮች፡- በታሪክ ተመዝግበዋል፡፡ በኢትዮጵያ የሶማሊያ አምባሳደር፣ የሶቪየቱ ዲፕሎማትና የኬጂቢ ሰው ጋር ሦስተኛው ዲፕሎማት፣ ‘ከአንድ አፍሪካዊት ዓረብ አገር’ የሶማሊያ አየር ኃይል አዛዥ የነበረው ኰሎኔል አፍነው በመውሰድ፣ ኢትዮጵያን ሦስት ሆነው ብቻዋን በስለላና በአፈና ትንቅንቅ ሲገጥሟት፣ ‘አገሬ ላይ ነኝ’ ብላ ሳትንቅ የተቋቋመችው በዘዴ ነበር፡፡”   በማለት መፅሃፉ የታሪኩን አኩሪ ተልዕኮ ይዘከዝክልናል፡፡  
ሃገርን ከወራሪ ጠላት ለመታደግ የሚያስችል መረጃን ያቀበለ የሶማሊያ አየር ኃይል አዛዥ የነበረን ኰሎኔል ለመጠበቅ ሲባል የተደረገ ውጥረት የተሞላበት ትንቅንቅ ነው፡፡ መፅሃፉ የሚተርከው፡፡ የሕዝብ ጸጥታ ጥበቃ መሥሪያ ቤት ባልደረቦች ለሃገራቸው ሲሉ፣ በኃያላን ሃገራት የስለላ ተቋማት ጣልቃ ገብነት ወደ ሶማሊያ ኤምባሲ ታፍኖ የተወሰደውን ሶማሊያዊ ኰሎኔል ከአፋኞቹ እጅ ፈልቅቆ ለማውጣት “እንቅልፍ ለምኔ?” ብለው፣ ውሎና አዳራቸውን በቢሯቸው ውስጥ አድርገው የፈፀሙትን እልህ አስጨራሽ ግብግብ ያስቀኛል  የኮሎኔል ተፈራ ካሣ መፅሃፍ፡፡ “በአደገኛ ሰላይነቱ (የኬጂቢ ሰላይ) ከተሰጠው የዲፕሎማቲክ ሥራ ውጪ አልፎ ያልተፈቀደለትን በመሥራቱ /ፐርሶና ኖን ግራታ/ ተሰጥቶት ከአገር እንዲባረር ተደርጓል” (ገፅ 175) ያሉት ሰው ተባሮ ሲወጣ ቦሌ አውሮፕላን ጣቢያ ሲሳፈር፣ “ዛሬ ብታስወጡኝ ነገ በክብር ተመልሼ እንደምመጣ እንድታውቁት!” ብሎ ዝቶባቸው፤ ዳግም ተመልሶ ወደ ሃገራችን መግባቱን የምናውቅ ስንቶቻችን ነን? ከዲፕሎማቲክ ግኝኙነት ውጪ ሲንቀሳቀስ ተገኝቶ የተባረረ ዲፕሎማት፤ መንግስት ቢለወጥ እንኳ ዳግም ወደተባረረበት ሃገር እንዳይገባ የሚደነግገውን የቬይና ኮንቬንሽን በማንና ለምን ተጥሶ ወደ ሃገራችን ሊገባ ቻለ? ድርጊቱ በመፈፀሙ ለሃገራቸው ሲሉ የደከሙና በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ዋነኛ ተጠቃሽ የሆኑትን የጸጥታ ባለሙያዎቻንን (ደራሲውን ጨምሮ) ያሳዘነና ያስከፋ እንደነበር በሚጋባ በቁጭት ተርኳል፡፡      
የመጽሐፉ ዓቢይ የታሪኩ ማዕከል የሶማሊያ አየር ኃይል አዛዥ በነበረው ኰሎኔል ዙሪያ የሚያጠነጥን ቢሆንም በአጠቃላይ በወቅቱ በሃገሪቱ የነበረው ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዴት በውጥረቶች የተሞላ እንደነበር ደራሲው በጥልቀት ገልፀውታል፡፡
መፅሃፉ፤ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ (ጃንሆይ) በዙሪያቸው ያጋጠማቸውን ከባድ ፈተና እያስታወሱ ሲቆዝሙ ያስቃኘናል፡፡ ንጉሡ የገጠማቸው ፈተና፤ “አይጋፉት ባላጋራ” ዓይነት ሆኖ ሲሰማቸው፣ ደግሞ መለስ ብለው “እስካሁን የጠበቀን እግዚአብሔር ነው፡፡ አሁንም እሱ ነው ተስፋችን” እያሉ ሲጽናኑ፤ በስነ ጽሑፋዊ ጥበቡ እንድንሰማው ሲያደርገን፣ ሹማምንቶቻቸው፣ መኳንንቶቹና መሳፍንቶቹ በወሬ፣ በስብቅ፣ በሸፍጥ በአሉባልታ ምን ያህል ይጠላለፉ እንደነበር መረጃን መሠረት አድርጎ፤ ምሥጢራቸውን ሲካፍለን፣ ይህም በሕዝብ አስተዳደር ላይ ያሳደረውን ተፅእኖ ይተነትንልናል፡፡ደራሲው የመጽሐፉ ዓቢይ ገፀ ባህሪ አድርጎ “በራሪ የሠላም አምባሳደር በሚል” የሰየመው፣ የሶማሊያው አየር ኃይል አዛዥ ኰሎኔል ጋሌብን ሕይወት ከልጅነት ጊዜው ጀምሮ በቅኝ ገዢ የእንግሊዝ የጦር መኮንኖች ቤት ያሳለፈውን፣ አየር ኃይሉን የተቀላቀለበትን ሁኔታ፣ በፖለቲካዊ አመለካከቱ ሳቢያ በወጉ ሳያጣጥመው ስለከሸፈው ጅምር የፍቅር ሕይወቱ፣ በአገሩ ሶማሊያ ላይ እንደ አልቅት ተጣብቀው ሀብቷን ስለሚቦጠቡጡ ወዳጅ ነን ባይ ሃገራት ስለሚሰማው ሰሜትና ስለደረሰበት በደል፣ በሃገራችን በስደት በቆየበት ጊዜ ያሳለፋቸውን ገጠመኞች እንዲሁም በጣልያን ሃገር በሮም ከተማ ዳግም በስደት ሲኖር ባደረገው ታጋድሎ፣ የኢትዮጵያ የውጭ መረጃ /ፎሪን ኢንተልጀንስ/ ሰዎች ስላደረጉለት ድጋፍና በመጨረሻም ባደረገው ፅናትና ተጋድሎ በመገረም፤ “የሮም ከተማ ከአፍሪካ ዳግማዊ ዘርዓይ ደረስን ወይንም አብዲሳ አጋን ልትፈጥር ይሆን?! (ገፅ 310)” ስላሉበት ዝርዝር ምሥጢር በጥልቀት ይተርክልናል፡፡
የሕዝብ ጸጥታ ጥበቃ መሥሪያ ቤት ከፍተኛ መኮንኖችና ባልደረቦች ከ1953 መፈንቅለ መንግስት በኋላ ‹‹ተገፍተናል›› የሚል ስሜት ተሰምቷቸዋል፡፡ የእኛን ተግባር ሌሎች ታማኝ ነን ባዮች እንዲሠሩት ተደርጓል የሚል ቅሬታ ውስጣቸው ገብቷል፡፡ ከፍተኛ መኮንኖቹ በየአጋጣሚው ብሶታቸውን ይገልፃሉ (ገጽ 168)፡፡  “ደግሞስ ከእናንተ ምን ይጠበቃል? ተባልን፤ አመኔታ ከአጣን አሥር ዓመት አለፈን” ሲሉ አቤቱታቸውን እናነባለን፤ ቢሆንም ግን ስለ ሥራ ክፍላቸው አብዝተው ይጨነቃሉም ይላል- “ዘፍ ያለው”፡፡
“ስለ ኢንተለጀንስ ክፍሉ ሥራ ኃላፊነት፣ በተለይ ‘የጃንሆይንና የዘውዱን ክብርና ሞገስ ተዳፈሩ’ የምንላቸው ሰዎች ላይ ብቻ ማተኮር የለብንም፡፡ ለሀገርና ለወገን የሚጠቅም ሥራ እንሥራ” (ገፅ 166) የሚል ሀገራዊ ስሜት በውስጣቸው የሚመላለስባቸው ስለመሆናቸውም ያስረዳናል፡፡ የተቋሙ ኃላፊ የበላይ መኮንኖችን የተከፋ ስሜት ለንጉሡ በማቅረብ የነበረውን ስሜት ለማደስ ሲውተረተሩም እናያለን፡፡ ይህም ተሳክቶላቸው ለሚካሄደው ዘመቻ መኮንኖቹን በነቃ ሁኔታ የሚያሳትፉበትን ታሪካዊ ክስተት መፍጠራቸው መጽሐፉ ይዳስሳል፡፡
እዚህ አዲስ አበባ ውስጥ የሶማሊያ አምባሳደር፣ ከዲፕሎማሲ ሥራው ባሻገር ወዳጅ ከሚላቸው ሃገራት የሰለላ መዋቅሮች ጋር አብሮ የሃገሪቱን ምሥጢር በመሰለል ሥራ ላይ ተጠምዷል፡፡ በተለይም ደግሞ  “ከአንበሳ መንጋጋ ሥጋ ፈልቅቄ ወስጃለሁ” ብሎ ካመነ ወዲህ ኩራትና ትዕቢት ልቡን ወጥሮታል፡፡ የፈለቀቀውን ሥጋ ከኢትዮጵያ በሆነ ዘዴ አሾልኮ በሃገሩ መሬት  ከሃገሩ መሪዎች ጋር ሊያላምጠው ቋምጧል፡፡ ለዚህም በልዩ ሁኔታ የሰለጠኑ ሁለት ቁመተ ሎጋ ኮማንዶዎችን ወደ ሃገር ውስጥ እንዲገቡ አድርጓል፡፡ ወዲህ ደግሞ “የፈለቀቁትን ሥጋ አፋቸው ሳይከቱት መልሰን እንነጥቃቸዋለን” የሚሉት የኢትዮጵያ የሕዝብ የጸጥታ ጥበቃ መሥሪያ ቤት ከፍተኛ መኮንኖችና ባልደረቦች፣ ሥራዎቻቸውን በተጠና እና ምሥጢራዊ በሆነ መንገድ እያከናወኑ ነው፡፡ “/Mission Accomplished/ ተግባር ተፈፀመ!” ይሉናል። ግን እንዴት የቀረውን አንብባችሁ ድረሱበት- ከመፅሃፉ፡፡ ትገረማላችሁ፡፡ ትደመማላችሁ፡፡

Monday, 12 December 2016 12:15

ማወቅ ይጠቅማል!

መጠጦችና የአልኮል ይዘታቸው
ቢራ- 4%-6%
ወይን ጠጅ- 11.5%-13.5%
ውስኪ- 40%-46%
ጂን- 40%-50%
ቮድካ 35%-50%
ብራንዲ 35%-60%
ራም- 37.5%-80%
ኡዞ- 40%-46%
ሻምፓኝ- 12%
ተኪላ- 40%-50%
ሳምቡካ 38%
ፓስቲስ- 40%-45%
ሬሚ ማርቲኒ 40%
ማሊቡ- 21%

• በመልካም አስተዳደር---በዲሞክራሲ ግንባታ----በግልጽነት---??
• መንግስትስ እንዲጠናከሩ በምን በኩል ደገፋቸው?
   የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት ኤጀንሲ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት እንዲስፋፉና ተልዕኳቸውን በሕግ መሰረት እንዲወጡ ብሎም አሰራራቸው ግልፅነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት እንዲሆን እየሰራ ይገኛል፡፡ ኤጀንሲው በህገ-መንግስቱ አንቀፅ 31 የተደነገገውን የዜጎች የመደራጀት መብት እውን ለማድረግ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራትን መዝግቦ ፈቃድ በመስጠት ዘርፈ ብዙ የክትትልና ድጋፍ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ማህበራት በሀገራቸው ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታና የልማት ስራዎች ላይ የመሳተፍ እድል አግኝተዋል፡፡ በርካታ ቁጥር ያላቸው የሙያና የብዙኃን ማህበራት ተደራጅተው ፍቃድ በመውሰድ በሀገሪቱ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ። ምንም እንኳ አብዛኞቹ ማህበራት ተመዝግበው መንቀሳቀስ የጀመሩት በቅርብ ዓመታት ቢሆኑም ከተመሰረቱ ግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ እድሜ ያላቸው ማህበራትም አሉ፡፡ ሆኖም እንደ ቁጥራቸው ብዛትና እንደ እድሜያቸው ልክ የሙያ ማህበራት በሀገሪቷ የፖለቲካ ህይወት ውስጥ የራሳቸውን አሻራ አኑረዋል ማለት ግን አይቻልም፡፡ የሙያም ሆኑ የብዙሃን ማህበራት የህዝብን ጥያቄ በተደራጀ መልኩ እያቀረቡ እንዲፈቱ ለማስቻል፣ በመንግስትና በህብረተሰቡ መካከል እንደ ድልድይ ሆነው እያገለገሉ አይደለም። በበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት ኤጀንሲ ተመዝግበው ፍቃድ የወሰዱ በጥቅሉ 333 ገደማ የሚሆኑ የሙያና የብዙኃን ማህበራት ቢኖሩም የረባ ስራ ሰርተዋል ለማለት አያስደፍርም፡፡ ሆኖም በጥቅሉ ሁሉም ማህበራት ለተቋቋሙለት ዓላማ በተገቢው መልኩ አስተዋፅኦ አላበረከቱም ማለታችን አይደለም። ለዓብነት የሚጠቀሱ ስኬታማ ስራ መስራት የቻሉ ማህበራት መኖራቸው አይካድም፡፡ እንደ ኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ያሉ ጥሩ ተሞክሮ ያላቸው በጣት የሚቆጠሩ ማህበራት መኖራቸው ልብ ሊባል ይገባል፡፡  
አብዛኞቹ የሙያና ብዙኃን ማህበራት የሚፈለገውን ውጤት እንዳያመጡ እንቅፋት የሆነባቸው ሀገሪቱ በዘርፉ የምትከተለው ህግ መሆኑን በአፅንኦት ይገልፃሉ፡፡ ለምሳሌ የ10/90 ህግ፣ ማህበራት የገንዘብ ድጋፍ ከውጭ ሀገር እንዳያገኙ በማድረጉ ለመዳከማቸው ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳደረገ ይናገራሉ። ሆኖም ህገ-መንግስቱ በደነገገው መሰረት፣ በማህበር የመደራጀት መብት የተሰጠው ለዜጎች ብቻ ነው፡፡ በአዋጅ 621/2001 መሠረት፣ የኢትዮጵያ ማህበራት ፍቃድ ወስደው ለመስራት ሁሉም አባላት ኢትዮጵያዊ መሆን ይኖርባቸዋል እንዲሁም የገቢ ምንጫቸው ከሀገር ውስጥ መሆን እንዳለበት ተደንግጓል፡፡ በመሆኑም በህግ ከተፈቀደው ውጪ ከውጭ የገንዘብ ምንጭ መጠቀም አይቻልም፡፡ የሙያና ብዙሃን ማህበራት የአባላትን መብትና ጥቅም ለማስጠበቅ የሚሰሩ በመሆናቸው፣ እንደ በጎ አድራጎት ድርጅቶች ሰፊ የሀብት መጠን ላያስፈልጋቸው ይችላል፡፡ 90 ከመቶ የሚሆነውን ሀብት ከሀገር ውስጥ በማመንጨት እንዲሁም 10 ከመቶ የማይበልጠውን ከውጭ ሀገር በማምጣት ከሰሩ የተቋቋሙለትን አላማ ከዳር ማድረስ ይችላሉ፡፡ ማህበራት የአባላትን መብትና ጥቅም ለማስከበር የውጭ እርዳታ ሳያስፈልግ በሀገር ውስጥ ሀብት መስራት ይችላሉ፡፡ በመሆኑም በሀገራችን እየተንቀሳቀሱ ያሉ ማህበራት የ10/90 ህግ ውጤታማ ላለመሆናቸው ምክንያት ሊሆን አይችልም፡፡ ይህ ህግ ሲወጣ ማህበራት ሀብት የማግኘት አቅማቸው እንዳይዳከም ብዙ ታሳቢ የተደረጉ ጉዳዮች አሉ፡፡ ለዓብነት ያህል ማህበራት ከተቋቋሙለት ዓላማ ጋር ግንኙነት ባላቸው ብሎም ዓላማቸውን ለማስፈፀም ብቻ የሚውል የተለያዩ ገቢ ማስገኛ ስራዎች ላይ እንዲሰማሩ አማራጮች ተቀምጠዋል፡፡ የንግድ ህግ ጠብቀው ተጨማሪ ገቢ ማስገኛ ስራዎች ላይ መሰማራት ይችላሉ፡፡ የተለያዩ መንገዶችን ተጠቅመው ህዝባዊ መዋጮ በማካሄድ ከሀገር ውስጥ ሀብት ማመንጨት ይችላሉ። እነዚህ ሁሉ አማራጮችን ተጠቅመው ከጥገኝነትና ከተመፅዋችነት አመለካከት ተላቀው፣ ራሳቸውን ችለው መንቀሳቀስ ስለሚችሉ የ10/90 ህግ አላሰራንም ማለት ምክንያት ማብዛትና ከህግ አንፃርም ተገቢነት የሌለው በመሆኑ፣ ማህበራት ቆም ብለው ማጤን ይኖርባቸዋል፡፡ ህልውናቸው የሚወሰነው እራሳቸውን ለማጠናከር በሚሰሩት ስራ ነው፡፡
ይህ ሲባል የብዙሃንና የሙያ ማህበራት ምንም ተግዳሮቶች የሉባቸውም ማለት አይደለም፡፡ አብዛኞቹ ስራ መስሪያ ቢሮ የላቸውም፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ለስራቸው ግብዓት የሚሆኑ ቁሳቁሶችን የማግኘት ችግር አለባቸው፡፡ በየዘርፉ ያሉ የመንግስት ተቋማት ለሙያና ብዙሃን ማህበራት ድጋፍ ሊያደርጉላቸው ይገባል፡፡ የሙያ ማህበራትም ለአባላት ስልጠና እና የትምህርት እድልን ከማመቻቸት ባለፈ ያላቸውን እውቀትና ክህሎት ተጠቅመው ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምሮችን በማካሄድ፣ ለፖሊሲና ስትራቴጂዎች ግብዓት የሚሆኑ የመፍትሄ ሀሳቦችን በማቅረብ እንዲሁም መንግስትን በማማከር ለሀገሪቷ አቅም መፍጠር አለባቸው፡፡ ይህንን ኃላፊነት በመወጣት ረገድ ማህበራት የጎላ አስተዋፅኦ አድርገዋል ማለት አይቻልም፡፡ በቀጣይ በመስኩ የሚፈለገው ውጤት እንዲመጣ፣ የሙያ ማህበራት በየዘርፋቸው ከሚገኙ የመንግስት ተቋማት ጋር የጠበቀ ቁርኝት ፈጥረው፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን እጅና ጓንት ሆነው መፍታት አለባቸው፡፡ የሙያ ማህበራት ውጤታማ የሚሆኑት ያላቸውን እምቅ እውቀትና ክህሎት ሳይሰስቱ ለሀገራቸው ማበርከት ሲችሉ ነው፡፡ በሌላ በኩል መንግስት፣ እነዚህ በጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት እንዲጠናከሩ የማህበራዊ ተጠያቂነት ፈንድ (Social Accountability fund) ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ ይኖርበታል፡፡   
የሙያና ብዙሃን ማህበራት በራሳቸው የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ተምሳሌት መሆን መቻል አለባቸው፡፡ የአባላትን መብትና ጥቅም በማስከበር፣ በጠቅላላ ጉባኤ መሪዎችን መምረጥ፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ነቅሶ በማውጣት እንዲፈቱ ማድረግ፣ ያልተመለሱ መብቶችን ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲመለሱ አባላትን በማለማመድ እንደ ሀገር በሚደረገው የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ መነሻና ትምህርት ቤት መሆን አለባቸው፡፡ የአንዳንድ ማህበራት የስራ ኃላፊዎች የጊዜ ሰሌዳቸውን ጠብቀው ጠቅላላ ጉባኤ በመጥራት የስራ አፈፃፀማቸውን አያቀርቡም፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ለበርካታ አመታት ስልጣናቸውን ለሌሎች አባላት ሳይለቁ የሚቆዩበት ሁኔታ አግባብነት የለውም፡፡ የመተዳደሪያ ደንባቸው ላይ በተቀመጠው መሰረት በየሁለት ዓመቱ የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባዎችን በማካሄድ፣ ስልጣናቸውን አዲስ ለሚመረጡ ሌሎች አባላት አሳልፈው መስጠት አለባቸው፡፡ የማህበራት አመራር አባላቱን በአገራዊ ጉዳዮች ላይ እያወያዩ፣ ዜጎች የጠራ አመለካከት ይዘው ለልማት እንዲነሳሱ የበኩላቸውን ሚና መጫወት አለባቸው፡፡ የሙያና ብዙሃን ማህበራት የሀገሪቷ አይን፣ ጆሮና አፍ መሆን አለባቸው፡፡ ማህበራቱ ሰፊ ቁጥር ያላቸው አባላትን ከመያዛቸው አንጻር ወሳኝ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የሚኖራቸው የጠራ ግንዛቤ፣ ብሄራዊ መግባባትን ለመፍጠር ትልቅ አስተዋፅኦ ማበርከት ይችላል፡፡
የሙያና ብዙኃን ማህበራት ውስጣዊ አሰራርም ግልፅነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት መሆን አለበት፡፡ ይህ ሲሆን ነው  መልካም አስተዳደርና ዲሞክራሲያዊ አሰራር ሊጎለብት የሚችለው፡፡ ማህበራት በሀገሪቷ የፖለቲካዊ ህይወት ውስጥ የነቃ ተሳትፎ ማድረግ ሲችሉ የዜጎችን ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች በማስከበር ረገድ ጉልህ ሚና ሊጫወቱ ይችላሉ፡፡ አቅም ሲፈጥሩ በሀገሪቱ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ውስጥ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ማበርከት ይችላሉ፡፡ በዚህ ረገድ የሙያም ሆኑ ብዙኃን ማህበራት በጉልህ የሚታይ ነገር አልሰሩም፡፡
አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ የብዙኃን ማህበራት ገዢው ፓርቲ ያቋቋማቸውና ለሱ በመወገን የፖለቲካ ስራ እንደሚሰሩ አድርገው የሚቆጥሩ አካላት አሉ። ነገር ግን የሙያና ብዙኃን ማህበራት ከየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ነፃ ሆነው በገለልተኝነት ለዜጎች እኩል የሚሰሩ ናቸው፡፡ ህጉም ይህንኑ ነው የሚደነግገው፡፡ በሌላ መልኩ የሙያና ብዙኃን ማህበራት በመንግስት መዋቅር ውስጥ ያሉ ክፍተቶችን ነቅሰው በማውጣት እንዲፈቱ ጫና እየፈጠሩ አይደለም፡፡ በእርግጥ ማህበራት ይህንን እንዲያደርጉ መንግስት ምቹ ሁኔታ ፈጥሮላቸዋል ወይ የሚለው ጥያቄ በአግባቡ መፈተሽ አለበት፡፡ ሌላው ቀርቶ የአባላትን መብትና ጥቅም ማስጠበቅ የሚችሉበት ደረጃ ላይ አልደረሱም። ምንም እንኳን ሁሉንም ማህበራት የሚገልፅ ባይሆንም ማህበራት የሙያ ብቃት ባላቸው ግለሰቦች እየተመሩ አይደለም፡፡ ከዚህ በተጨማሪም አንዳንድ ማህበራት ስልጣን ለመያዝ በሚያደርጉት ሽኩቻ በመጠመዳቸው፣ ትርጉም ባለው መልኩ ሀገራዊ ራዕይ አንግበው ሙያውን ለማሳደግ እየሰሩ አይደለም። ይህም በዘርፉ የሚፈለገው ውጤት እንዳይመጣ አሉታዊ ተጽዕኖ አድርጓል፡፡  
የሙያም ሆኑ ብዙኃን ማህበራት በስነ-ምግባር የታነፁና በእውቀት የበለፀጉ፣ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን በማፍራት ረገድ ትኩረት ሰጥተው መስራት አለባቸው፡፡ የአባላትን አቅም በመገንባት ዙሪያ ብዙም የተሰራ ስራ የለም፡፡ ማህበራት በተጨባጭ አባላትን ማፍራትና አቅም መገንባት መቻል አለባቸው፡፡ ማህበራት ሲጠናከሩ የአባላትን መብትና ጥቅም ማስከበር ይችላሉ፡፡ የፋይናንስ አቅማቸው እንዲጠናከር የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችና ለጋሾች ድጋፍ እንዲያደርጉላቸው ጥረት ማድረግ አለባቸው። ከዚሁ ጎን ለጎን ማህበራት እንቅስቃሴያቸው በበጎ ፍቃደኞች እንዲደገፍ ለማስቻል፣ የበጎ ፍቃደኝነት ባህል እንዲዳብር ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል። በሀገሪቱ የሚገኙ የህትመትና የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያዎች ትኩረት ሰጥተው የሙያና ብዙኃን ማህበራትን የስራ እንቅስቃሴ እንዲሁም ያሉባቸው ተግዳሮቶች ላይ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ በሰፊው መስራት አለባቸው፡፡ ሚዲያዎች በዘርፉ ያሉ ድክመቶችን ለመፍታት የሚያስችል ጥልቅ እይታና አቅጣጫ አመላካች የመፍትሄ ሀሳቦችን መስጠት መቻል አለባቸው፡፡
የሙያ ስነ-ምግባርና ብቃትን ከማሳደግ አንፃር የሙያ ማህበራት ብዙ ርቀት መጓዝ ቢኖርባቸውም ስንዝር እንኳን መራመድ አልቻሉም፡፡ ተዝቆ የማያልቅ ትልቅ አቅም ቢኖራቸውም፣ ከስብሰባ የዘለለ ትርጉም ያለው ስራ ለመስራት ለማከናወን  የቁርጠኝነት ማነስ እንዳለባቸው ይጠቀሳል፡፡ ይሄን ድክመታቸውን ማሻሻል አለባቸው፡፡ ነገር ግን ለማህበራት ተገቢውን እገዛ ሳያደርጉ በድፍኑ መውቀስም ተገቢ አይሆንም። ስለዚህ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላትም ለሙያና ብዙኃን ማህበራት ትኩረት ሰጥተው አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ አለባቸው፡፡ የብዙኃንና የሙያ ማህበራት ያላቸውን ምርጥ ተሞክሮ ቀምሮ ማስፋፋት ያስፈልጋል፡፡ የሀገር ውስጥም ሆነ ያደጉ ሀገራት ተሞክሮዎችን ከሀገሪቱ ነባራዊ ሁኔታ ጋር አጣጥሞ ማስፋፋት፣ ለነገ የማይባል ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ተግባር ሊሆን ይገባል:: እንደ ሀገር የሙያም ሆኑ የብዙኃን ማህበራት፣ በዜጎች መብት ነክ ጉዳዮችና የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ሂደት ውስጥ በንቃት መሳተፍ የሚያስችላቸው አሰራር መዘርጋት አለበት እንላለን፡፡
የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት ኤጀንሲ
ኢሜይል አድራሻ - This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

‹‹የፍራየርስ ክለብ ኢንሳይክሎፒዲያ ኦፍ ጆክስ›› ካካተታቸው ቀልድ አከል ቁምነገሮች ውስጥ  የሚከተለው ይገኝበታል፡፡
ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ሚስተር ሁበርት ሐምፍሬይ የተባሉ ምሁር ለአንድ የዩኒቨርስቲ ተማሪ የመጨረሻ የጥናት ወረቀት መካር (advisor) ሆነው ይቀጠራሉ፡፡ የመካርነቱን ሥራ በታላቅ ደስታ ነበር የተቀበሉት፡፡ እንዲህ ብለው፡-
‹‹በዕውነቱ ወጣት ምሁራን ለወግ ማዕረግ ይበቁ ዘንድ የመጨረሻ የጥናት ወረቀታቸውን ሲያቀርቡ ማገዝና ሙያዊ ክህሎታቸውን ማብቃት፣ ለእኔ ታላቅ ደስታና ዓይነተኛ ክብር ነው፡፡ በተቻለኝ አቅም ዕውቀቴን ላጋራው ፍቃደኛ መሆኔን እገልፃለሁ!›››
ሚስተር ሐምፍሬይ ተማሪውን መርዳት ቀጠሉ፡፡ ተማሪውም በትጋት መሥራቱን ቀጠለ፡፡
ወረቀቱን የማቅረቢያው ወቅት ሲደርስ ተማሪው በቆንጆ ሁኔታ የተጠረዘ ፅሑፉን ይዞ ሚስተር ሐምፍሬይ ዘንድ ከች አለ፡፡
‹‹ሚስተር ሐምፍሬይ፤ በወረቀቴ ላይ አስተያየትዎን ይሰጡኝ ዘንድ ይሄው መጥቻለሁ፡፡ ምን ይሉኝ ይሆን?››
ሚስተር ሐምፍሬይም፤
‹‹መልካም፡፡ አየውና መልስ እነግርሃለሁ›› አሉና አሰናበቱት፡፡ ተማሪው አመስግኖ ከቢሮአቸው ወጣ፡፡
ሁለት ወር አለፈ፡፡ ከሚስተር ሐምፍሬይ በኩል ምንም የተሰማ ነገር የለም፡፡ ስለዚህ ተማሪው ቢሮአቸው ሄደ፡፡
ከዚያም፤ ‹‹ሚስተር ሐምፍሬይ፤ ወረቀቴን እንዴት አገኙት?” ሲል ጠየቃቸው፡፡
ሚስተር ሐምፍሬይም፤
‹‹እርግጠኛ ነህ ይሄ የመጨረሻውና ያለቀለት ሥራህ ነው? ዕውቀትህ ይሄ ብቻ ነው?›› ሲሉ ትኩር ብለው እያዩት ጠየቁት፡፡
ተማሪው  ቅር ያላቸው ነገር እንዳለ በመገመት፤
‹‹አንዴ ወስጄ ልየው?›› አለ፡፡
‹‹ይሻላል›› አሉት፡፡
ተሜ፤ በድጋሚ መሥራቱ እየከፋው የወረቀቱን ጥራዝ ተቀብሎ ሄደ፡፡ ፕሮጄክቱን አንዴ ሊከልሰው ነው፡፡
ከሁለት ወራት በኋላ ተማሪው የከለሰውን ወረቀት አጠናቅሮ፣ ቀንብቦ፣ ለሚስተር ሐምፍሬይ አምጥቶ አስረከባቸው፡፡ ሁለት ወር አለፈ፡፡ ከሚስተር ሐምፍሬይ በኩል ምንም ወሬ የለም፡፡ ስለዚህ ‹‹ቢሮአቸው ብሄድ ይሻላል›› ብሎ ወደዚያው አመራ፡፡ እንደደረሰም፤
‹‹እንዴት ሆነልኝ፤ ሚስተር ሐምፍሬይ?›› ሲል ጠየቀ፡፡
ሚስተር ሐምፍሬይ ግን፤
‹‹በቃ ይሄው ብቻ ነው ችሎታህ? እንደገና ቢሠራ ይሻላል›› አሉት፡፡
‹‹እሺ፤ የመጨረሻ ሙከራ ላድርግ›› አለና ተሜ፤ እየከፋው ወደ ቤቱ ሄደ፡፡ በጣም ቅር እያለው በነጋታው ጥናት ክፍሉ ገብቶ ለሶስተኛ ጊዜ ወረቀቱን ፃፈና፤
‹‹አሁንስ ‹አልቀበልም› ቢሉኝ፤ የራሳቸው ጉዳይ፤ እተወዋለሁ!›› እያለ ወደ ሚስተር ሐምፍሬይ ቢሮ ሄደና አስረከባቸው፡፡
ሚስተር ሐምፍሬይም፤
‹‹በቃ ይሄ ነው የመጨረሻ ሥራህ?›› አሉት፡፡
‹‹አዎ፤ ከዚህ በላይ ምንም የምጨምረው ነገር የለም›› አላቸው፤ ፍርጥም ብሎ፡፡
ቀጥሎም
‹‹አንዴ ብቻ ሳይሆን ሁለት ሶስቴ ተመራምሬበታለሁ፡፡ ሁለት ሶስት ዓይነት ትንተና ተንትኛለሁ፡፡ ደጋግሜም ፅፌዋለሁ፡፡ ይኸው ነው!››
ሚስተር ሐምፍሬይ ትኩር ብለው ካስተዋሉት በኋላ፤
‹‹ጥሩ! እንግዲያው ከሰጠኸኝ ወረቀቶች ሁሉ ለመጀመሪያ ጊዜ ይሄኛውን አነበዋለሁ!›› ብለው አሰናበቱት፡፡ ተሜ ወጣና፤
‹‹ወይኔ! እስከ ዛሬ አንዱንም ሳያነብቡ ነበር ለካ የሚያፈጉኝ!›› እያለ ሄደ፡፡
                                                          *    *    *
የሰውን ድካም ማቃለል የሚችሉ አመራሮችና ኃላፊዎች የየተቋማቱ ምሰሶዎች ናቸው፡፡ በአንፃሩ የሰው ድካም የማይሰማቸው ሰዎች፤ ሙሉ ልብ እንዳይኖራቸው የማያግዙ፣ የራሳቸውን መንገድ ብቻ የሚያሰላስሉና የመልካም አስተዳደር አካላት ያልሆኑ ግለሰቦች አሉ፡፡ ያልተገነዘቡት ነገር አለ፣ ለውጥ አሮጌውን ጥሎ አዲስ ይዞ እንደሚራመድ አዳዲስና ወጣት ኃይሎችን ያላቀፈ ዕድገት ወንዝ አይሻገርም፡፡ ከዚህም ጎን ለጎን የሲቪክ ማህበራትን ያላጠናከረና አዳዲስ እንዲፈጠሩ ያላገዘ የለውጥ ጉዞ፤ አገራዊ መግባባቶች፣ አገራዊ እርቆች፤ ቀና ውይይቶችና ሽምግልናዎች  የሚሰምሩት ሲቪል ማህበራት እንደ ልብ ሲንቀሳቀሱ ነው፡፡ አመራሮች ስለ ዕቅዳቸው የሚናገሩትና የሚገቡት ቃል የግብር-ይውጣ እንዳይደለ ማረጋገጥ ተገቢ ነው፡፡ የአመራር ለውጦች ሲደረጉ ከነበሩ ተጨባጭ የህዝብ ችግሮች ጋር በቅጡ የተሳሰሩና እነዚያን ችግሮች የሚፈቱ መሆን አለባቸው፡፡ አለበለዛ ‹‹ትሻልን ትቼ ትብስን አገባሁ›› የሚል ሥጋት ይፈጠራል፡፡ በተለይ ከሙስና ጋር ቁርኝነት ያላቸው የኃላፊነት ቦታዎች ብርቱ ጥንቃቄ ይጠይቃሉ። የቢሮክራሲና የደላሎች፣ የኤጀንሲዎች፣ የአስመጪና ላኪዎች ግንኙነት፣ ዛሬ ባገራችን ብዙ የተወራለት ስስ-ብልት ነው፡፡ ‹‹ዛር ልመና ሳይያዙ ገና›› ይሏል አበው፡፡ ከወዲሁ የነገሮችን አካሄድ ማጤንና መንቀሳቀስ ብልህነት ነው። ለትላንትና መልስ ለመስጠት፣ ዛሬም የቆምንበትን ሁኔታ አምርሮ መመርመር፣ የአዳዲስ ሹማምንት ሁሉ ብርቱ ኃላፊነት ነው፡፡
 አንዳንድ ፀሐፍት ስለ አንዳንድ ቢሮክራቶች መመሪያ ይህን ይላሉ፡፡
 ‹‹ ሀ-ኃላፊ ስትሆን ጠያቂና ተመራማሪ ምሰል
   ለ- ችግር ሲፈጠር የበታችህን ወክል (delegate)
   ሐ- ስትጠራጠር የማይገባ ነገር አጉተምትም፤ አነብንብ
   መ- የቢሮክራትነት ዋና ጥበብ ይሄው ነው››
ከዚህ ይሰውረን! ስንት ቢሮክራቶች ይህን አባዜ ተሸክመው ይሆን? ብሎ መጠየቅ የአባት ነው፡፡
በሌላ ወገን ደግሞ ስለ ፕሮጄክት ልዩ ልዩ ደረጃዎች ሲፅፉ ፡- ‹‹ አንደኛው የፕሮጄክት ደረጃ ወይም ምዕራፍ/
           ስለ ፕሮጄክቱ ሥራ መጓተት ነው፡፡ ሁለተኛው/
           ከግራ-መጋባት ነፃ መሆን ነው፡፡ ሦስተኛው/
           መሸማቀቅና መጨናነቅ መጀመር ነው፡፡
አራተኛ/ ጥፋተኛውን ፍለጋ መግባት ነው፡፡ የማነው ጥፋቱ? መባባል ነው፡፡ አምስተኛው/ ምንም ያላጠፋውን የዋህ ሰው እንዲቀጣ ማድረግ ነው፡፡ ስድስተኛውና የመጨረሻው በፕሮጄክቱ ሥራ ምንም ያልተሳተፉ ሰዎችን ማሞገስና ክብር ሰጥቶ ማወደስ ነው፡፡››
ከላይ የተጠቀሱት ጉዳዮች እኛም ጋ አሉ የምንል እራሳችንን መፈተሽ ነው፡፡ ሹማምንቶቻችን አገርና ህዝብን ያስቀድማሉ ወይ? ካላስቀደሙስ? ከዚህም ይሰውረን እንበል፡፡ ምክንያቱም የተለያዩ እርስ በርስ የሚግባቡ፣ የሚሞዳሞዱ ወዳጅ አመራሮች፤ የሆድ ለሆድ መርህ ኔት-ወርክ፤ አላቸው፡፡ መደጋገፊያ መረብ ነው፡፡ በዚያም ክፉኛ ይጠቃቀማሉ፡፡ ሀቀኛና ምስኪን ሠራተኞች ግን ላባቸውን አፍስሰው ሥራዎች እንዲሳኩና አገራችን ከድህነት እንድትወጣ ዕለት-ሰርክ ደፋ-ቀና ይላሉ፡፡ ዛሬ ሁኔታችን ይሄን መሳይ ነው፡፡ ‹‹ሹም ለሹም ይጎራረሳሉ፤ ድሀ ለድሀ ይላቀሳሉ›› የሚባለው ለዚህ ነው! ሹመትና ሽረት የተለመደ ነው፡፡ ትልቁ ቁም-ነገር የተሾመው ሹም፤ ብቁና ከተሻረው ሹም ስህተትና ጥፋት ምን ተማረ፤ የሚለው ነው! ‹‹ትላንትና ማታ ቤትህ ስትገባ የመታህ የድንጋይ እንቅፋት፣ ዛሬ ማታም ከደገመህ፤ ድንጋዩ አንተ ነህ›› የሚለውን የቻይናዎች አባባል አለመርሳት ነው! ሹመት የብቃት ማረጋገጫ ይሁን!!

   መንግስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች በዓመት ሦስት ጊዜ ፓርላማ ገብተው በውይይት እንዲሳተፉ ለማድረግ ማኑዋል እየተዘጋጀ መሆኑን የገለፀ ሲሆን ተቃዋሚዎች በበኩላቸው፣ ሳይወከሉ በፓርላማ ውይይት ህገ መንግስታዊ አይደለም ሲሉ ተችተዋል። ተቃዋሚዎች ለምን አላማ ከመንግስት ጋር በዚህ መንገድ እንዲወያዩ እንደተፈለገ አይገባንም ያሉት የአረና ም/ሊቀመንበር አቶ ጎይቶም ፀጋዬ፤ ውይይቱ በፓርላማ መደረጉ ምናልባት ኢህአዴግ ብቻውን ተቆጣጥሮታል የሚለውን ሃሜት ለማስቀረት ካልሆነ በቀር ሌላ ፋይዳ አይኖረውም ብለዋል። “የተቃዋሚዎች የመወሰን ሚና ጨርሶ በሌለበት ሁኔታ የሚደረጉ ውይይቶች ጥቅማቸው እምብዛም ነው” ይላሉ አቶ ጎይቶም፡፡
የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ም/ሊቀመንበር አቶ ሙላቱ ገመቹ በበኩላቸው፤ ተቃዋሚዎች የህዝብ ውክልና ሳይኖራቸው በፓርላማ መገኘታቸው በምን አግባብ ነው? ሲሉ ይጠይቃሉ፡፡ “ፓርላማው ላይ መገኘት የሚቻለው በህዝብ ሲወከሉ ብቻ ነው” ያሉት አቶ ሙላቱ፤ ተቃዋሚዎች የመወሰን ሚና ሳይኖራቸው የሚያደርጉት ውይይት ምንም ፋይዳ አይኖረውም ብለዋል፡፡
“መንግስት ከተቃዋሚዎች ምክር የሚፈልግ ከሆነ፣ በፓርላማው መሆን የለበትም” ያሉት አቶ ሙላቱ፤ ሌሎች ልዩ መድረኮች መዘጋጀት አለባቸው ይላሉ፡፡ ተግባራዊ ይደረጋል ብለው እንደማያምኑ የተናገሩት ም/ሊቀመንበሩ፤ ከዚህ በፊት መሰል የውይይት መድረኮች ይዘጋጃሉ ተብሎ መቅረቱን ያስታውሳሉ፡፡ አሁን መንግስት ማድረግ ያለበት ለህዝብ ጥያቄ መልስ መስጠት ነው ብለዋል - አቶ ሙላቱ፡፡
የፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባል የሆነው የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ (ኢራፓ) ፕሬዚዳንት አቶ ተሻለ ሰብሮ በበኩላቸው፤ “መንግስት ከተቃዋሚዎች ጋር ይወያያል የተባለው ከ2002 ምርጫ ማግስት ጀምሮ ነው፤ ሆኖም ተፈፅሞ አያውቅም፤ የአሁኑም የፓርላማው ውይይት የተስፋ ቃል ነው” ይላሉ፡፡
የመንግስትና የተቃዋሚዎች ውይይት እስካሁን ተግባራዊ ሲሆን አለማየታቸውን የገለፁት አቶ ተሻለ፤ “በእውን የሚደረግ ከሆነም፣ “በምን አግባብ ይከናወናል? መቼ ነው የሚጀምረው? እንዴት ነው ተቃዋሚዎች የሚሳተፉት? የሚሉትን ጥያቄዎችን መመለስ አለበት” ብለዋል፡፡ “የውይይት መድረኩ እውን ይሆናል ብለን እንድናምንና ምልክቶች መታየት አለባቸው ብለዋል” - ሲሉ አክለዋል፡፡
“የተቃዋሚዎች በፓርላማ መሳተፍ ምንን መርህ አድርጎ ነው? ህገ መንግስታዊ ነው? በአዋጅ የሚያሳትፍ ነው? የፖሊሲ አቅጣጫ አለው?” ሲሉ የጠየቁት የኢዴፓ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጫኔ ከበደ በበኩላቸው፤ “ተቃዋሚዎች በምን መንገድ፣ የትኛውን የህብረተሰብ ክፍል ወክለው  ነው በፓርላማ ሊሣተፉ የሚችሉት” ብለዋል፡፡
‹‹መንግስት ቅድሚያ መስጠት ያለበት ለህዝቡ ቀጥተኛ ጥያቄዎች መልስ መስጠት ላይ ነው ያሉት ዶ/ር ጫኔ፤ በአሁኑ ሰዓት ህዝብ ለተቃዋሚዎችም ለመንግስትም ፍላጎት ባላሳየበት ሁኔታ ተቃዋሚዎች በምን አግባብ ነው ፓርላማ ገብተው ሊነጋገሩ የሚችሉት ሲሉ ጠይቀዋል፡፡  ኢዴፓ ተቃዋሚዎችን ፓርላማ አስገብቶ በመወያየት ብቻ ችግሮች ይቀረፋሉ የሚል እምነት  እንደሌለው የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፤ ፓርቲያቸው የፖሊሲ አቅጣጫዎች እንዲሻሻሉና ህግ ሙሉ ለሙሉ እንዲከበር እንደሚፈልግ ገልፀዋል፡፡
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስና የፌደራሊዝም መምህር አቶ ናሁሠናይ በላይ የፓርላማውን ውይይት በተመለከተ ተጠይቀው ሲመልሱ፤ በፓርላማው ለየት ያለ ሃሳብ እንዲንፀባረቅ መፈለጉ መልካምና ጠቃሚ መሆኑን ገልፀው፤ የተቃዋሚዎች ሚና የሚለካው ከገዥው ፓርቲ ጋር በመገናኘታቸው ብቻ አይደለም፤ ገዥው ፓርቲ በተቃዋሚዎች ሚና የሚያምን ከሆነ፣ እንደ ፖለቲካ ፓርቲ የሚንቀሣቀሱበትን የመጫወቻ ሜዳ ምቹ ማድረግ አለበት ብለዋል፡፡
“ኢህአዴግ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገንቢ ሚና አላቸው ብሎ ማመን መጀመሩን ለማሳየት ከፈለገ፣ በፖለቲካ እንቅስቃሴያቸው ላይ እንቅፋት ከመሆን መቆጠብ ይኖርበታል፤ በአመት ሶስት ጊዜ ተቃዋሚዎችን በፓርላማ አሳትፋለሁ ማለት ብቻውን በቂ አይደለም፤ የተለያዩ መድረኮች መዘጋጀት አለባቸው” ያሉት ምሁሩ፤ “አሁን የሃገሪቱ ሁኔታ እንደ ቀድሞ የኔ ሃሳብ ብቻ  ይሰማ የሚባልበት ባለመሆኑ፣ ኢህአዴግ ከልቡ ተምሮ ከሆነ፣ ይህን ውጥኑን ተግባራዊ ሊያደርግ ይችላል” ሲሉ እምነታቸውን ገልፀዋል፡፡

     የታዋቂው ሞታውን ሪከርድስ ኩባንያ ፕሬዚዳንትና የአለማችን ትልቁ ሙዚቃ አሳታሚ ኩባንያ የዩኒቨርሳል ሚዩዚክ የኧርባን ሚዩዚክ ፕሬዚዳንት የሆነችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ የኩባንያ ስራ አስኪያጅ ኢትዮጵያ ሃብተማርያም፣ በቢልቦርድ የ2016 የአለማችን ምርጥ 100 የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ስራ ስኪያጅ ሴቶች ዝርዝር ውስጥ ተካትታለች፡፡
በአለማችን የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ የተሳካ ተግባራት የፈጸሙ የዘርፉ ኩባንያዎችን የሚመሩ ሴት የስራ አስፈጻሚዎችንና ማናጀሮችን እየመረጠ በየአመቱ ይፋ የሚያደርገው ቢልቦርድ፣ ሰሞኑንም ኢትዮጵያ ሃብተማርያምን ጨምሮ በአሳታሚነት፣ በአከፋፋይነትና በሌሎች ተያያዥ መስኮች የተሰማሩ ኩባንያዎችን የሚመሩ የአመቱ 100 ምርጥ ሴቶችን ዝርዝር አውጥቷል፡፡ የ37 አመት እድሜ ያላት ኢትዮጵያ ሃብተ ማርያም በምትመራቸው የሙዚቃ ኩባንያዎች አማካይነት በአመቱ ባከናወነቻቸው ተግባራት፣ ከአለማችን ምርጥ የሙዚቃ ኩባንያ መሪ ሴቶች ተርታ መሰለፏን ቢልቦርድ በድረገጹ ባስነበበው መረጃ ገልጧል፡፡ እ.ኤ.አ በ2011 የታላቁ የአለማችን የሙዚቃ ኩባንያ ሞታውን ሪከርድስ ከፍተኛ ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆን የተሾመችው ኢትዮጵያ፤ ስቲቪ ዎንደርን ጨምሮ ከአለማችን ታላላቅ ድምጻውያን ጋር ስኬታማ ስራዎችን በማከናወን ወደ ፕሬዚዳንትነት ማደግና በዩኒቨርሳል ሚዩዚክ ኩባንያ የኧርባን ሚዩዚክ ፕሬዚዳንት ሆና መስራት መቻሏ ተነግሯል፡፡
ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2014 በዚሁ የቢልቦርድ የአለማችን ምርጥ 100 የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ዘርፍ ሴቶች ዝርዝር ውስጥ ተካትታ እንደነበርም መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

ስልጠናና የቴክኒክ ድጋፍ እንሰጣለን ብለዋል

   በዓለም ታዋቂና ቀዳሚ ከሆኑት የኬክና ዳቦ አምራች ድርጅቶች አንዱ የሆነው ቤከልስ በቅርቡ ከተከፈተው ራማዳ አዲስ ሆቴል ጋር በመተባበር፣ ደረጃውን የጠበቀ ኬክና ዳቦ ለአዲስ አበባ ነዋሪ ሊያቀርብ ነው፡፡
ታዋቂው ጀርመናዊ ሼፍ ባስቲያን ኤቬርሰማን ትናንት በራማዳ አዲስ ሆቴል፣ ትክክለኛ ኬክና የዳቦ መጋገሪያ ቁሶችን (ዱቄት የተለያዩ ዓይነት ቸኮሌቶች…) በማቅረብ፣ ከተለያዩ ሆቴሎች ለተጋበዙ እንግዶች በመጋገር አሳይቷል፡፡
አዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ከተማ በመሆኗ ጥራት ያለውና ደረጃውን የጠበቀ ኬክና ዳቦ ማቅረብ አለብን ያሉት ሚ/ር ባስቲያን፤ ከ5 ኮከብ ሆቴሎች ጀምሮ አነስተኛ ኬክና ዳቦ መጋገሪያዎች፤ ትክክለኛውን ቁስ እንዲጠቀሙ፣ ለሁሉም የኬክና ዳቦና ዘርፍ ኢንዱስትሪ የቴክኒክ ድጋፍ፣ ጥራት ያለውት ምርት….. እናቀርባለን ብለዋል፡፡
ማንኛውም ሆቴልና ኬክና ዳቦ መጋገሪያ ትክክለኛውን ጥሬ ዕቃ ከራማዳ አዲስ ሆቴል ጋር በመነጋገር ሊያገኝ እንደሚችል ተገልጿል፡፡