Administrator

Administrator

እንዴት ሰነበታችሁሳ!
እኔ የምለው… በቃ ዘመኑ እንዲህ ሆነ ማለት ነው እንዴ… በቃ እኮ ሰው አየኝ አላየኝ ማለት መተፋፈር ምናምን ሁሉ ቀረ ማለት ነው? የእውነት እኮ እንደኔ ያለው በጋቢ ላይ ካፖርት መደረብ ‘ፋሺን’ የሚመስለው ‘ፕሪሚቲቭ’ ሰው.፣ ስምንተኛው ሺህ የደረሰ ቢመስለው አይገርምም፡፡ ኧረ እንደውም የእኛ ባስ ስለሚል ስምንተኛው መሆኑ ቀርቶ አስራ ስድስተኛው ሳይሆን አይቀርም፡፡ስሙኝማ… ስንት ነገር አምልጦናልሳ! አንዳንዴ ለአይን ያዝ ሲያደርግ በቦሌ መንገድ ‘ዎክ’ ሳጧጡፍ [ልጄ….ለእኛ ለእኛ ቦሌም ፓሪስም አንድ ናቸው] አንዳንድ ነገር አየት አደርግና ሲገርመኝ ያመሻል፡፡ እንዴ… ሰው እንዴት እንዴት ነው የሚያደርገው!
አንድ ወዳጄ አንድ ቅዳሜ ምሽት ቦሌ አካባቢን ሲያስስ አምሽቶ ኖሮ በማግስቱ ምን አለኝ መሰላችሁ? “የቆመ መኪና ሲመጣ ብቻ እየለየ የሚወዘውዝ መሬት መንቀጥቀጥ አለ እንዴ?” እኔ… በቃ ጭጭ አልኳ፡፡ ተናግሮ ከአናጋሪ ይሰውራችሁ፡፡


እና… ይኸውላችሁ ግርም የሚል ዘመን ነው፤ድሮ ድሮ “ሎሚ ብወረውር…” ተብሎ ነበር አሉ፤ ነገርዬው የሚያልቀው፡፡ የዘንድሮ ሰው… ልጄ ሎሚ የሚያክል ድንጋይ ይወረውር እንደሁ እንጂ … ብቻ አለመያዝ ነው፡፡ አሀ…‘ፋይል ለመክፈት’ ስንት ጣጣ አለ፡፡
አለላችሁ …. አንዳንዱ ሲያምጥ ከርሞ አንድ ቡና በወተት በትልቅ ብርጭቆና ዳበስ ዳበስ አርጎ ወፈር ያለ የልጅ ምሳ ሊሆን የሚል ቦምቦሊኖ ይጋብዛል፡፡ [ነገርዬዋ ማመልከቻ ቢጤ መሆኗ ነው] ታዲያ ልክ ሻኛው የሚገላበጥ የሀረር ሰንጋ የጣለላት ይመስል (ለነገሩ ዘንድሮ አይሞከረም!) “እንዴት ነው ታዲያ… ይመችሻል!” ይልላችኋል፡፡ ኧረ!... በቦምቦሊኖ ተመቸ! የእንትን ሰፈር ልጆች ቢሆኑ ኖሮ የዚህ ዓይነቱን ስልቻ ሙሉ ቦምቦሊኖ አሸክመው “በቀረበህ መንገድ ወደ ኬንያ…ወይ ኡጋዳ ተሰደድ…” ነበር የሚሉት፡፡
በስዋሂሊኛ ‘ይመችሻል!’ ምን እንደሆነ ስለማያውቅ አርፎ ይቀመት ነበር፡፡ ደግሞ ሌላው አለላችሁ… ተንከርፍፈህ ኑር ተብሎ ርግማን የተጣለበት የሚመስል፡፡ ጧት ይጠብቅና ከኮልፌ ኮከብ ጽባህ ቢሆን እኳን ይሸኛል፡፡ የትምህርት ሰዓት ሲያቅ ደግሞ
ቤት ይመልሳል፡፡ ምን አለፋችሁ እግሩ ስር ጎማ አልተገጠመም እንጂ ሶስት ቁጥር ታርጋ ካቻማሊ በሉት፡፡

አንድ ወዳጄ “እንዲህ ዓይነቱን…. እስኩል ባስ በለው” ነው ያለኝ፡፡ስሙኝማ ደግሞ አለላችሁ… ግርም የሚል ፍጡር፡፡ ፊልም የለ ትያትር የለ ሙዚቃ
የለ… የፈረደባትን ከጎኑ አድርጎ ድፍን አዲስ አበባን በእግር ሲያካልል ይውልላችኋል፡፡ በቃ “በእግር መጓዝ ጤንነት ነው…” እያለ ፀሀይ የለ፣ ቁር የለ ብቻውን የከተማውን ማስተር ፕላን ሲከልል የሚውል ነው የሚመስለው፡፡ የምር ግን… አንዳንዴ በቃ ነጩ ባንዲራ ቀረ እንጂ የሰላምም ተጓዥ ይመስላል፡፡ ‘ዎክ’ ሌላ ‘መንክራተት’ ሌላ፡፡እኔ የምለው … ነገርዬው ሁሉ እንደ ድሮ የተመለሰባቸው ቦታዎች አሉ እንዴ!
የመሀል አራዳ ውስጥ አዋቂዎች ሲነግሩኝ እዚያ አካባቢ “ትዝ አለኝ የጥንቱ” ዓይነት ጨዋታ አለ አለ፡፡ የት መሰላችሁ? አውቶብስ ፌርማታ፡፡ አንዳንዱ ቀኑን ሙሉ አውቶብስ ፌርማታ አይጠፋም አሉ፡፡ ምን አለፋችሁ… በቃ ሽፍቱ ያደረሰ ትኬት ቆራጭ ይመስል አላፊ አግዳሚውን ሲያይ ይውላል፡፡ እኔ’ኮ ሲኒማ ኢትዮጵያ አጠገበ ያለ ሁሉ ሰው አውቶብስ ጠባቂ ይመስለኝ ነበር፡፡ ለካስ ሌላም ጨዋታ አለ፡፡


ስሙኝማ የአንዳንዱ አራድነት ግርም የሚል ነው፡፡ [አንድ ጊዜ በዚህ ቢለኝ በዚያ የሆነ… ጥሬ ነገር የሆንኩበት ወዳጄ “አንተ ሰውዬ… አራድነትህን ሸጠህ በላኸው እንዴ!” ብሎኛል፡፡ እኔ የምለው ‘አራድነት’ ለ‘ፕራይቬታይዜሽን’ የሚቀርበው መቼ ነው? አንተ እንትና… ላንተ አራድነት የሚወጣው ጨረታ አይደለም ሶስቴ አሥራ ሶስቴ ነበር የሚሰረዘው! የእውነት ላንተ የሆነ ኤን.ጂ.ኦ በጣሳ የአራድነት እርዳታ ቢሰፍርልህ ይሻላል፡፡]እናላችሁ አንዳንዱ ኮተቤ አካባቢ ቆሞ “ስድስት ቁጥር አለፈች እንዴ?” ይላል፡፡ [ኧረ! ብልጥ ተሁኖ ልብ ውልቅ! ‘አይ የእንትን ሊዎንቺና ነች ያመለጠችህ’ ማለት ነበር፡፡]ስሙኝማ… ሴቶች ሰብሰብ ያሉበት አካባቢ ሲደርሱ የሚሸልሉ ወንዶች አይጥሟችሁም? በቃ… እኮ አሪፍ አክተሮች ናቸው፡፡ አረማመድ እግር ስር ስፕሪንግ የተገጠመ ነው የሚመስለው፡፡ አንዳንዱ ግንባሩን ከስክሶ እንዴት እንደሚኮሳተር!...
ብቻ ማን እንደሚነግራቸው እንጃ አንዳንዶች ሴቶች ኮስታራ ወንድ ይመቻቸዋል የሚል ፈሊጥ አላቸው፡፡ [ይኸው እኛ ስንት ዘመን ስንኮሳተር እንኳን ልንመቻቸው… መንገድ ተሻግረው ነው የሚያልፉት፡፡ እኔ እንደውም አንዳንዴ ኮስተር ብዬ ሸለልኩ ስል ለልጆቻቸው እየጠቆሙ “አያ ጅቦ መጣ…” ሳይሏቸው አይቀሩም፡፡]ስሙኝማ አንድ ነገሩ ሁሉ አልሆነ ያለው ወንደላጤም አለ አሉ፡፡ ምን አለ መሰላችሁ?
“ገንዘባችሁ ሁሉ አለቀ በሻይ ትዳሩን ሳናየው ዓለምን ሳናይ!”ታዲያ እኛ ከለከልን! አይ ሸጋው ወንደላጤ… አንተ ታዲያ ዘላለምክን የሰው ሆድ በስሙኒ ሻይ የምታነፍረው…የሻይ ቅጠል እርሻ የለህ፡፡ አንተ የዘጋኸውን እንጀራህን የምን “አላሳዝንም ወይ…” ነው፡፡ ገና በጠዋቱ በሻይ ላይ ሙጭጭ ያልከው በኋላ እኮ “ዋናው ነገር ፍቅሩ ነው…” እያልክ ቦምቦሊኖ አብረን እንግመጥ ከማለት አትመለስም!
ልጄ ድሮ ድሮ… ስንት ጣጣ ነበር፡፡ አንዷን እሺ ከማሰኘት የዓለም ባንክ ብድር ማስፈቀድ ይቀል ነበር - የምር፡፡ ያኔ እኮ… የወንዱም ሽለላ አሪፍ ነበር፡፡ ፀጉር ኖራቸውም ልኖራቸውም መሀል ላይ መከፈሏ አይቀርም፡፡ ካስፈለገም የሆነ ወፈር ያለ የእንግሊዝኛ ልብ ወለድ ይያዛል፡፡ አሀ… እንግሊዘኛ የሚያውቅ ‘አለመታወቂያ እንዲያልፍ’ ይፈቀድለታላ፡፡ ስሙኝማ… አንድ ወዳጄ መሀል ላይ ፀጉራቸውን የሚከፍሉ ሰዎችን ምን ትላቸው መሰላችሁ? “ሹል ቴክስ፡፡”ደግሞ አለላችሁ ብልጥነት ሞልቶ ይተርፈውና በብልጢኛ “ስምሽ መቅደላዊት
አይደለም?” ሲል ይጠይቃል፡፡ አጅሪትም “አይ አይደለም ፎዚያ ነው” ትለዋች፡፡ እሱ ምን ይላል መሰላችሁ? “አይ… ብዙም አልራቅሁም፡፡” ከዛ በብልጢኛ አሳሳቅ ይስቅና “ያው … መቼም ሞትና ትውውቅ አንድ ቀን ነው…” ይልና ብቻ ምን ለፋችሁበሴኮንድ ዘጠኝ ቃላት ይናገራል፡፡እኔ የምለው… አንዳንዶቻችሁ “እምቢ” ስትባሉ ድርቅና ነው እንዴ! በቃ ችክክ የሚል አለላችሁ፡፡ ነጋ ጠባ ከርቀት ይከተላታል፡፡ ምን አለፋችሁ ክላሺንኮቭ ቀረች እንጂ አንጋች ነው የሚመስለው፡፡በዛ ሰሞን እኔና ጓደኛዬ አንድ ሚኒ ባስ ውስጥ ሆነን… በቃ
“ፍቅር የተራበ” ዓይነት ድራማ ስናይ ነበር፡፡ አይተዋወቁም፡፡ ወንድዬው… ታዲያ በቃ የህይወት ታሪኩን ይዘረዝርላታል፡፡

እሷ ሆዬ… በተመስጦ ሳይሆን በመገረም ነበር የምታየው፡፡ አለ አይደለም… በሆዷ “ሰው እንዲህ ሞዛዛ ሆኖ ይፈጠራል?” የምትል ነው የሚመስለው፡፡እናላች…ኮሚክ ዘመን ሆኗል፡፡ አንዳንዱ የማያውቃትን “ሹራቡ ያምርብሽ…”
ይላል፡፡ “ፒንክ ቀለም እወዳለሁ፡፡” ኧረ! ታዲያ ጨርቅ ተራ አትሄድም! አይ ሽጋው ወንደላጤ… ገንዘቤ ሁሉ በሻይ አለቀ አለ! እንትን ሰፈር ብትሄድ ምን የመሰለ በሶ አለ መሰለህ፡፡ አሀ… የላጥካትን ጨጓራ ራስህ ጠግናታ! ስሙኝማ… እስቲ ቦሌ ሄጄ አስራ ዘጠኝ ቁጥርን ልጠብቅ፡፡ ማን ያውቃል…
‘ፒንክ’ ሹራብ ይመጣ ይሆናል!

Saturday, 16 December 2023 20:44

እኛማ እንቆጥራለን

እኛማ እንቆጥራለን
ዛሬም ሙሉ ሳቅክን
ያልተሸራረፈ ሙሉ ፈገግታህን
እንዳቀፍን አለን በየምላዳችን የነገ ሰብልህን..
አሴ ኩራ ኩራ፣ ባለህበት ኩራ፣
ብርሃን ያዘምራል፣ ያሳብህ ተራራ..
ዓመቱማ ያልፋል ወደ ፊት ገፍትሮን
ዘመኑ ቢሸብት፣
አይረሴ ራዕይ፣ ነጭ ፀጉር የለው
ከቶ መች ይረሳል
ህልምህ የወይን ጠጅ፣ ሲነጋ ይበስላል
የነበረህና የነበረን ሀሳብ፣ እያደር ይጠራል፡፡
ስምህ ማዘርዘሩ፣ መንፈስህ መብቀሉ
እምነት ፍልስፍና ውልና ፈትሉ
ዕውቀትና ትጋት ብርሃን ፊደሉ
ሩቅ እንዳሰብነው ሩቅ ነው ገድሉ
ዛሬም አለ ቃሉ፣
ያውም በርቶ ፈክቶ፣ እስከ ማዕዜኑ፡፡
አውቃለሁ ታውቃለህ
የመከረኛ አገር መከሯ እስኪገባ
መከራ መብዛቱ
እውን ቢሆን እንኳ
ራዕይህ አለ ምስክር ይቆማል፤ ቀኑ ለመንጋቱ
አይቆምም ጉዟችን ባይቆምም ስጋቱ....
አይደለም ራእይ ብሳና- ዛፍ ግንድ
ሽበት አይወርሰውም የዕድሜ ዘመን ግርድ
አይረሴ ራዕይ የቸገንክበትን
የፍል ዕውቀት እርሻ የዓለም አሂዶህን
ታያለህ ማሳውን፡፡
አሴ ኩራ ኩራ
ብርሃን ያዘምራል ያሳብህ ተራራ....
የራዕይ ተራራ....
ነቢይ መኮንን

በአፍሪካ ትልቁ የፓን አፍሪካ የሙዚቃ ሽልማት ሥነ ሥርዓት ኮራ ሽልማት ላይ (KORA AWARDS, THE BIGGEST PAN AFRICAN
MUSIC AWARDS CEREMONY) አምስት ኢትዮጵያዊያን ሙዚቀኞች በአምስት ዘርፍ እጩሆነው ተመርጠዋል፡፡ አምስቱም እጩዎች ከአርባ
ሌሎች ተፎካካሪዎቻቸው ጋር በሕዝብ በሚሰጥድምጽ እንደሚፎካከሩ በ KORA AWARDS የፌስቡክ ገጻቸው ይፋ አድርገዋል፡፡
1. በ BEST GROUP- AFRICANURBAN MUSIC ምርጥ 40ዎች ውስጥ የገቡትኢትዮጵያዊያን እጩ ጃኖ ባንዶች (JANO BAND)
ናቸው፡፡ ከታች ባለው ሊንክ በመግባት ድምጽእንድትሰጧቸው በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ VOTEHERE :HTTPS://WWW.KORAAWARDS.
COM/TOP40
2.በBEST ARTIST TRADITIONALMUSIC ምርጥ 40ዎች ውስጥ የገባውኢትዮጵያዊያዊ እጩ አስቻለው ፈጠነ(ASCHALEWU FETENE ) በእናትዋ ጎንደርእና በካሲናው ጎጃም ነው፡፡ ከታች ባለው ሊንክበመግባት ድምጽ እንድትሰጡት በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ V OTE H ERE : H TTPS://WWW.KORAAWARDS.COM/TOP403. በ BEST MALE ARTIST-RAP MUSIC ምርጥ40ዎች ውስጥ የገቡት ኢትዮጵያዊ እጩ ልጅሚካኤል (LIJ MICHAEL) ነው፡፡ከታች ባለው ሊንክ በመግባት ድምጽ እንድትሰጡት በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
VOTE HERE : HTTPS://WWW.KORAAWARDS.COM/TOP404.በ BEST COLLABORATION OF THEYEAR ምርጥ 40ዎች ውስጥ የገቡት ኢትዮጵያዊያንእጩ ጆሲ ሮያል (JESSE ROYAL) ናቸው፡፡ ከታችባለው ሊንክ በመግባት ድምጽ እንድትሰጧቸው በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡ VOTE HERE:HT TPS://W W W.KOR AAWARDS.COM/TOP405.በ BEST FEMALE AFRICAN URBAN
MUSIC ምርጥ 40ዎች ውስጥ የገባችው ኢትዮጵያዊት እጩ ሔዋን ገብረወልድ (HEWANGEBREWOLD) ናት፡፡ ከታች ባለው ሊንክ
በመግባት ድምጽ እንድትሰጧት በአክብሮትእንጠይቃለን፡፡ VOTE HERE : HTTPS://WWW.KORAAWARDS.COM/TOP40

እውቁ የትምህርት ባለሙያና የ95 ዓመት የእድሜ ባለፀጋው ዶ/ር አክሊሉ ሀብቴ ምስጋና ቀረበላቸው፡፡ የምስጋናና የእውቅና መርሃ ግብሩ
ባለፈው ማክሰኞ ታህሳስ 2 ቀን 2016 ዓ.ም ጦር ሀይሎች አካባቢ በሚገኘው “ሊባዊ ኢንተርናሽና” ት/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥየተካሄደ ሲሆን የምስጋና መርሃ ግብሩበለባዊ አለም አቀፍ ት/ቤትና በተወዳጅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን አማካኝነት የተሰናዳ ነው፡፡
በእለቱ ልዩ ልዩ ኪነጥበባዊ መሰናዶዎች የቀረቡ ሲሆን ዶክተር አክሊሉ በስፍራው ተገኝተው ለለባዊ ት/ቤት መምህራንናተማሪዎች ልምዳቸውን በማካፈል እውቀትና ልምድ እንዲቀስሙ አድርገዋል፡፡ ዶ/ር አክሊሉ ሀብቴ በሀገራችን ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ሲጀመር ከመጀመሪያዎቹ ምሩቃን
መካከል አንዱ ሲሆኑ ዩኒቨርስቲውንም በፕሬዚዳንትነትና በመምህርነት አገልግለዋል፡፡ ዶክተሩ በሀገራችን የትምህር ዘርፍ ላይ የጎላ ሚና ከማከናወናቸውም በተጨማሪ በአለም ባንክ ውስጥም በትምህርት ዘርፍ ላይ ያገለገሉና የቀዳማዊ ሀይስላሴ ዩኒቨርስቲን(የአሁኑን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን) ታሪክ በ600 ገፅ በመጽሀፍ በማሳተምና ታሪክ በመሰነድ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል፡፡
 እኒህ የ95 ዓመት የእድሜ ባለፀጋ ለረጅም ዓመታት መኖሪያቸውን በሀገረ አሜሪካ ያደረጉ ሲሆን አልፎ አልፎ ወደ ሃገራቸው ኢትዮጵያ ብቅ እያሉ
ይመለሳሉም ተብሏል፡፡ የማክሰኞ እለቱ የምስጋናና የእውቅና መርሃ ግብርም ከአሜሪካ ተመልሰው ሀገራቸው በነበሩበትአጋጣሚ የተሰናዳና በአካል የታደሙበት ነውም ተብሏል፡፡ በእለቱ በርካታ እንግዶች የለባዊ እንተርናሽናል አካዳሚ ሀላፊዎች ተማሪዎችና መምህራን በታደሙበትዶ/ር አክሊሉ ሀብቴ ምስጋናና እውቅና ተሰጥቷቸው ተመስግነዋል፡፡

 32ኛው የአውደፋጎስ የመፅሀፍ ውይይት ክበብ “አደፍርስ ልቦለድ በሙዚቃ መንፈስ መፅሀፍነቱ ሲዳሰስ” በሚል ርእስ ነገ ታህሳስ7 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በኢትዮጵያ ቤተ መፃህፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ (ወ መዘክር) እደሚካሄድ አዘጋጆቹአስታወቁ፡፡ የውይይቱን የመነሻ ሀሳብ ከላይ በተገለፀው ርዕስ የምታቀርበው ትሬዛ ዮሴፍ ስትሆን ፍላጎት ያለውና የስነ ፅሁፍ ወዳጅ የሆነ በውይይቱ ላይ እንዲታደምና እውቀት
እንዲቀስም አዘጋጆቹ ጋብዘዋል፡፡

ፈተናውን ማለፍ ያልቻሉ መቋቋሚያ ተሰጥቷቸው ከስራ ይሰናበታሉ ተብሏል

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስሩ ለሚገኙትና አዲስ የመዋቅራዊ ማሻሻያ አደረጃጀት ጥናት ባደረጉ ተቋማት ውስጥ ለሚገኙ ሁሉም ሠራተኞችና የስራ ኃላፊዎች የብቃት መመዘኛ ፈተና ሊሰጥ ነው ተባለ። ፈተናውን ያላለፉ ሰራተኞች መቋቋሚያ ተሰጥቷቸው ከስራ ይሰናበታሉ ተብሏል።
ከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ዘርፎች ለሰራኞቹ የብቃት ምዘና ፈተናውን የሚሰጥ ሲሆን በመጀመሪያው ዙር የብቃት ምዘና ፈተናውን የሚወስዱት የቤቶች ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት፣ የስራ ኢንተርፕራይዝ ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት፣ የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ጽ/ቤት፣ ህብረት ስራ ጽቤት የመሬት ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት መሆናቸውም ታውቋል። የብቃት ምዘና ፈተናው የሚሰጠው በክፍለ ከተሞቹና በከተማ አስተዳደሩ ስር ባሉ መዋቅሮች እንደሆነም ታውቋል።
የብቃት ምዘና ፈተናውን የወሰዱ ሠራተኞች ፈተናውን ማለፍ ካልቻሉ ሁለት የውሳኔ አማራጮች የቀረቡ ሲሆን፤ አንደኛው አማራጭ ሰራተኛ ድልድሉ ከመደረጉ በፊት አጭር ስልጠና ተሰጥቷቸው ፈተናውን በድጋሚ እንዲወስዱ የሚደረግ ሲሆን ሌላኛው አማራጭ ደግሞ ወደ ሌላ ተቋም ተዛውረው ባላቸው የትምህርት ዝግጅትና በነበራቸው ደመወዝ እንዲመደቡ ይደርጋል ተብሏል። ከእነዚህ ውጪ የሆኑት ደግሞ የማቋቋሚያ ድጋፍ ተደርጎላቸው ከሥራ እንደሚሰናበቱ ተነግሯል። ከስራ እንዲሰናበቱ ያደርጋል ተብሏል። በሃላፊነት ደረጃ ላይ ተመድበው ሲሰሩ የነበሩና የብቃት ምዘና ፈተናውን ማለፍ ያልቻሉ ሠራተኞች ደግሞ ከነበሩበት የስራ መደብና ደመወዝ ዝቅ እንደሚሉ ተገልጿል።የብቃት ምዘና ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ሜያቸው ለጡረታ የደረሱና ጡረታ መውጣት የሚፈልጉ ሠራተኞች በፍቃደኝነት የጡረታ መብታቸውን ማስከበር እንደሚችሉም ታውቋል።
የአስተዳደሩ ሰራተኞች በከተማ አስተዳደሩ ተግባራዊ ሊደረግ ስለተዘጋጀው የብቃት ምዘና ፈተና የሚያውቁት ነገር እንደሌለና ዱብዕዳ እደሆነባቸው ምንጮች ጠቁመዋል። ፈተናው በቀጣዮቹ ሳምንታት ውስጥ እንደሚደረግና መጪው ጥር ወር በፊት እንደሚጠናቀቅ ታውቋል። የኢትዮጵያ ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ መርሻል ብርሃኑ ጁላ ሰሞኑን ለፋና ቴሌቪዥን በሰጡት ቃለ-መጠይቅ የድሮን ጥቃቱን አስመልክተው
ሲናገሩ “ድሮን እኮ የተሰራው ለጦርነት ነው፣ለውጊያ ነው የገዛነው ልንዋጋበት ነው እንጂ ድሮን አለን እያልን በሚዲያ ልንገልጸው አይደለም የጦር መሳሪያ ነው ልክ እንደክላሹ ክላሽ የአቅሙን ይሰራል ሌላውም የአቅሙን ይሰራል፣ ድሮንም የራሱን ስራ ይሰራል፡፡ ድሮን እኛ የምንጠቀመው ለስብስብ ዓላማ ነው፡፡ ለወታደራዊ ስብብ ኢላማ የሚባል ነገር አለ፡፡ ስብስብ ኢላማ ማለት የጠላት ጠንካራ ቋጠሮ ማለት ነው፡፡ የጽንፈኛ
ስብስብ ስናገኝ በድሮን እንመታለን”ብለዋል፡፡

•  በትግራይ የተከሰተው ድርቅ ከ77ቱ የከፋ ነው ተባለ  

•  25 ህፃናትን ጨምሮ 400 ሰዎች በረሃብ   ሞተዋል  

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ በክልሉ   ከ2 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ለረሃብ መጋለጡን ያስታወቀ ሲሆን፤ እስካሁንም 23 ህጻናትን ጨምሮ 400 ሰዎች በረሃብ መሞታቸውን ጠቁሟል፡፡

በክልሉ ያጋጠመውን የድርቅ አደጋ ለመከላከል ያለመ፣ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ  22 አባላት ያሉት "አፋጣኝ ምላሽ ለትግራይ" የተሰኘ ግብረ ሃይል ተቋቁሞ እንቅስቃሴ መጀመሩም ተነግሯል፡፡

የ"አፈጣኝ ምላሽ ለትግራይ" ግብረ ሃይል ሰብሳቢ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ   በዛሬው ዕለት  ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ በአሁኑ ሰአት ለረሃብ አደጋ የተጋለጠውን ከ2 ሚሊዮን በላይ ትግራዋይ ህይወት ለመታደግ በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኝ የክልሉ ተወላጅና ወዳጅ እንዲረባረብ ጥሪ አቅርበዋል።  “ሰብዓዊነት የሚሰማው ሁሉ” የእርዳታ እጁን እንዲዘረጋም ጠይቀዋል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የአደጋ መከላከያና ዝግጁነት ኮሚሽን ኮሚሽነር ገብረሕይወት ገ/እግዚአብሔር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ድርቁ በአምስት የትግራይ ክልል ዞኖች ተከስቷል ብለዋል።


“በትግራይ የከፋው ድርቅ የተከሰተው በ1951 እና በ1977 ነበር፤ አሁን ያጋጠመን ከዚያም በላይ ነው፤ በዚህ ድርቅ ምክንያት 2 ሚሊዮን ሕዝብ ተርቧል። 400 የሚሆኑ ሰዎች ባለፈው ወር ብቻ  በረሃብ ምክንያት ሕይወታቸው አልፏል” ብለዋል፤ ኮሚሽነሩ፡፡

የ"አፈጣኝ ምላሽ ለትግራይ" ግብረ ሃይል ድጋፍ ማሰባሰቢያ የባንክ ሂሳብ ቁጥሮች የሚከተሉር ናቸው፡-

* አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ፡-00112180095-49

* ወጋገን ባንክ፡- 1001077411101

* የኢትዮጵያ  ንግድ ባንክ፡- 1000592420809

”አርቲስት ሀናን እንደምትጠቅመን አምነንበታል” -ድርጅቱ-

አርቲስት ሀናን ታሪክ፤ ድሪመር ፉድ ማኑፋክቸሪንግ ከተሰኘ ታዋቂና ግዙፍ የቻይና ኩባንያ ጋር የብራንድ አምባሳደር ለመሆን በዛሬው ዕለት በስካይላይት ሆቴል  ከስምምነት ላይ የደረሰች  ሲሆን፤ ለድርጅቱ የሁለት ዓመት የብራንድ አምባሳደር ለመሆን 10 ሚሊዮን ብር ተከፍሏታል፡፡

ኩባንያው በኢትዮጵያ ውስጥ በከፍተኛ ኢንቨስትመንት የምግብ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ያቋቋመ ሲሆን ፤ ‹‹ኤስ›› በሚል ብራንድ ያልተለመዱና አዳዲስ የታሸጉ የኬክ ወይንም የጫፋጭ ምግቦችን እያመረተ በመላው አገሪቱ እያከፋፈለ እንደሚገኝ ተጠቅሷል፡፡



ድርጅቱ ይህንን ‹‹ኤስ›› የተሰኘ ብራንድ ምርቶቹን በስፋት ለማስተዋወቅና ስርጭቱን ለማሳደግ የአንድ አመት የኮርፖሬት ብራንድ ፕሮሞሽን እቅድ ማውጣቱን ገልጿል፡፡ በዚህ እቅዱ ውስጥም ታዋቂዋን አርቲስት ሀናን ታሪክን ማካተቱን አስረድቷል፡፡

 ‹‹የኤስን ብራንድ ፕሮሞሽን ውጤታማና ስኬታማ ለማድረግ አርቲስት ሀናን እንደምትጠቅመን አምነንበታል›› ብሏል፤ ድርጅቱ በሰጠው መግለጫ፡፡

የቴሌግራም ቻናልችንን  በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ያዘጋጀውና የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አካል የሆነው “የኛ ምርት” የተሰኘ አውደ ርዕይና ባዛር በዛሬው ዕለት ረፋዱ ላይ በስካይ ላይት ሆቴል ተከፈተ፡፡

አውደ ርዕዩና ባዛሩ “ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት” በሚል መሪ ቃል፣ እስከ ታሕሳስ 7 ቀን 2016 ዓም ድረስ እንደሚቆይ  ተገልጿል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል በመክፈቻው ላይ ባደረጉት ንግግር፤ አምራቹን ዘርፍ ለማነቃቃት የተለያዩ ንቅናቄዎች ተጀምረው ለውጥ ማስመዝገብ ተችሏል፤ የዚህ ንቅናቄ አካል የሆነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኤግዚቢሽንና ባዛር፣ አምራቾችን ከሸማቾች ጋር በማገናኘት፣ የሀገር ውስጥ ምርትን በማስተዋወቅና የኑሮ ውድነቱን በማረጋጋት ሰፊ ጠቀሜታ ይኖረዋል ብለዋል።


የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በበኩላቸው፤ አምራች ዘርፉን መደገፍ ኢትዮጵያ ለምታደርገዉ የብልጽግና ጉዞ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህ አውደ ርዕይና ባዛር ላይ ከ85 በላይ የሀገር ዉስጥ አምራች ኢንተርፕራይዞች የተሳተፉ ሲሆን፤ ከ50 ሺ በላይ ሰዎች እንደሚጎበኙት ይጠበቃል ተብሏል፡፡