Administrator

Administrator

- ባለፉት 10 አመታት የተገደሉ ጋዜጠኞች 787 ደርሰዋል
በተጠናቀቀው የፈረንጆች አመት 2015 በአለማችን 100 የተለያዩ አገራት ጋዜጠኞች በስራቸው  ምክንያት ወይም ባልታወቀ ሰበብ መገደላቸውን ሪፖርተርስ ዊዝአውት ቦርደርስ የተባለው አለማቀፍ የጋዜጠኞች
መብት ተሟጋች ተቋም ባለፈው ማክሰኞ አስታወቀ፡፡ በአመቱ ለህልፈተ ህይወት ከተዳረጉት ጋዜጠኞች መካከል ስድሳ ሰባቱ በስራቸው ላይ እያሉ  ተገድለዋል ያለው ተቋሙ፤
ይህም ባለፉት አስር አመታት ከሙያቸው ጋር በተያያዘ የተገደሉ ጋዜጠኞችን ብዛት 787 እንዳደረሰው ጠቁሞ ሌሎችበሰላማዊ አገራት የሚንቀሳቀሱ በርካቶችም በስራቸው ምክንያት የግድያ ኢላማ መሆናቸውን
አስታውቋል፡፡ በአመቱ 43 ጋዜጠኞች የግድያ ሁኔታቸው ወይም የመገደላቸው ሰበብ ሳይታወቅ መገደላቸውን
የገለጸው ተቋሙ፣ በሙያቸው ጋዜጠኛ ባይሆኑም በዘርፉ የተሰማሩ 27 ግለሰቦችና በሌሎች ሚዲያዎች ላይ የሚሰሩ 7  ሰራተኞች መገደላቸውንም ጠቁሟል፡፡
በአብዛኞቹ ጋዜጠኞች ላይ የተፈጸሙት ግድያዎች ሆን ተብለው የተቀነባበሩ ናቸው ያለው ተቋሙ፣
ለጋዜጠኞች የሚደረገው ከለላ አናሳ መሆኑን ጠቁሞ፣ የተባበሩት መንግስታት በሟቾቹ ላይ ለተወሰደው እርምጃ  የሚመለከታቸው አካላት ተገቢውን ምላሽ እንዲሰጡ የሚያስችል አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ ጠይቋል፡፡ በ2014 በተለያዩ የአለማችን አገራት ከሞቱት ጋዜጠኞች መካከል ሁለት ሶስተኛ ያህሉ ጦርነት
ባለባቸው አካባቢዎች የተገደሉ እንደነበሩ ያስታወሰው ሪፖርቱ፤ በተቃራኒው በ2015 ከሞቱት ጋዜጠኞች መካከል ሁለት ሶስተኛ ያህሉ ሰላማዊ ተብለው በሚታወቁ አካባቢዎችና አገራት የተገደሉ መሆናቸው ተረጋግጧል ብሏል፡፡ በአመቱ 11 ጋዜጠኞች የተገደሉባት ኢራቅ፣ለጋዜጠኞች አደገኛ የሆነች የአለማችን ቀዳሚዋ አገር  መሆኗን የጠቀሰው ተቋሙ፤10 ጋዜጠኞች የተገደሉባት ሶርያ በሁለተኛነት መቀመጧን፣ በቻርሊ ሄቢዶ መጽሄት ዝግጅት  ክፍል ላይ ሽብርተኞች በፈጸሙት ጥቃት 8 ጋዜጠኞች የተገደሉባት ፈረንሳይም ሶስተኛ ደረጃን መያዟን  ገልጧል፡፡
አይሲስና አልቃይዳን የመሳሰሉ የሽብር ቡድኖች በአመቱ 28 ጋዜጠኞችን መግደላቸው የተነገረ
ሲሆን በተለያዩ አገራት የታሰሩ ጋዜጠኞች ቁጥርም 153 ደርሷል፡፡

- ከ6 አመታት ወዲህ ዝቅተኛው ዕድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል
በዋና ዋናዎቹ የአለማችን የበለጸጉ አገራት የተከሰተው የተቀዛቀዘ የኢኮኖሚ እድገትና ሌሎች አለማቀፍ ኔታዎች በሚያስከትሉት አሉታዊ ተጽዕኖ ሳቢያ በ2016 የአለም ኢኮኖሚ እድገት በእጅጉ ይቀንሳል ተብሎ
እንደሚጠበቅ አለማቀፉ የገንዘብ ተቋም ማስታወቁን ዘ ጋርዲያን ዘገበ፡፡
የተቋሙ ዳይሬክተር ክርስቲያን ላጋርድ ባለፈው ረቡዕ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፣ የ2006
የአለማችን የኢኮኖሚ እድገት እ.ኤ.አ በ2009 ከተከሰተው የኢኮኖሚ ቀውስ ወዲህ ዝቅተኛው ደረጃ ላይ ይደርሳል  ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የኢኮኖሚ እድገቱ በ2014 አመት ከተመዘገበው 3.4 በመቶ እድገት በታች ይሆናል ያሉት  ዳይሬክተሯ፤ በ2015 በአለማቀፍ ንግድ እድገት ላይ ከፍተኛ ቅናሽ መታየቱን ጠቁመው በሸቀጦች ዋጋ ላይ የታየው  ቅናሽም ሃብትን መሰረት ያደረገ ኢኮኖሚ ባላቸው አገራት ላይ ተጽዕኖ ይኖረዋል ብለዋል፡፡በአዲሱ የፈረንጆች ዓመት ሩስያና ብራዚልን የመሳሰሉ አገራት የከፋ የኢኮኖሚ ችግር
እንደሚገጥማቸውም ዳይሬክተሯ ተናግረዋል፡፡ የምርታማነት መቀነስ፣ የአምራች ዜጎች ቁጥር ማሽቆልቆል፣ ከፍተኛ ብድር፣ አነስተኛ  ኢንቨስትመንትና የመሳሰሉት ጉዳዮች በአውሮፓና በሌሎች አገራት ኢኮኖሚ ላይ ተጽዕኖ እንደሚፈጥሩ ይጠበቃል ተብሏል፡፡

- የአልቃይዳው መሪ ስሜት ቀስቃሽ ግጥም ለሰልጣኞች ታድሏል
አልቃይዳን የመሳሰሉ አሸባሪ ቡድኖች ግጥምን ተጠቅመው የግለሰቦችን ልብ በማማለል አዳዲስ  አባላትን እየመለመሉ እንደሚገኙና የፕሮጋንዳ መሳሪያ እንዳደረጉት ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ሰሞኑን ያወጣውን የጥናት
ውጤት ጠቅሶ ዘ ቴሌግራፍ ዘገበ፡፡ ታጣቂ ቡድኖቹ የግለሰቦችን ስነ ልቦና ለመቀየርና ስሜታቸውን ለመግዛት ግጥምን በመሳሪያነት  እየተጠቀሙ ነው ያለው ዘገባው፤ ይህም አላማቸውን ለማስረጽና አዳዲስ አባላትን ለማፍራት ሁነኛ መሳሪያና ስልት  እንደሆነ ጠቁሟል፡፡ አልቃይዳ በየመን ግጥምን እንደ አንድ ሃይለኛ የጂሃድ መሳሪያ እየተጠቀመ ነው ያለው  ዘገባው፤የሽብር ቡድኑ የግለሰቦችን ቀልብ የሚስቡ አማላይ ግጥሞችን በማሰራጨት ሰፊ የፕሮፓጋንዳና የቅስቀሳ ስራ  እንደሚያከናውን አስታውቋል፡፡ ኦሳማ ቢን ላደን በ2000 ዓ.ም በተፈጸመ ጥፋትና በሌሎች የአልቃይዳ አንቅስቃሴዎችና አላማዎች  ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ግጥሞችን እንደጻፉ ያስታወሰው ዘገባው፣ ሌላ የቀድሞ የቡድኑ መሪ የጻፋቸው ስሜት  ቀስቃሽ ግጥሞችም፣ በቡድኑ ለሽብር ተመልምለው ሲሰለጥኑ የነበሩ ጂሃዲስቶችን ለጥቃት ለማነሳሳት በስፋት  ተሰራጭተው እንደነበር አመልክቷል፡፡

- አዲሱ ቴክኖሎጂ በአይን ይከፈታል ተብሏል
   ታዋቂው የሞባይል አምራች ኩባንያ ሳምሰንግ፣ ጋላክሲ ኤስ በሚል መለያ ሲያቀርባቸው የቆዩት
የስማርት ፎን ምርቶቹቀጣይ የሆነውን ጋላክሲ ኤስ 7 በየካቲት ወር አጋማሽ በገበያ ላይ ያውላል ተብሎ እንደሚጠበቅ ሲኒውስ ድረገጽ ዘግቧል፡፡ ጋላክሲ ኤስ 7 እና ጋላክሲ ኤስ 7 ኢጅ ተብለው የሚጠሩት አዲሶቹ የኩባንያው ምርቶች፣ በ5.2  እና በ5.5 ኢንች መጠን ለገበያ እንደሚቀርቡ ታውቋል ያለው ዘገባው፤ ሞባይሎቹ ለአጠቃቀም ምቹና የተለየ ዲዛይን ያላቸው እንደሆኑ ጠቁሟል፡፡ኩባንያው አዳዲሶቹን የሞባይል ምርቶቹን ለመጀመሪያ ጊዜ በሚያስመርቅበት ወቅት 3.3 ሚሊዮን  ያህል ጋላክሲ ኤስ 7 እንዲሁም 1.7 ሚሊዮን ጋላክሲ ኤስ 7 ኢጅ ሞባይሎችን በገበያ ላይ የማዋል እቅድ እንዳለው  ተነግሯል፡፡
አዳዲሶቹ ሞባይሎች ተጠቃሚው በአይኑ በማየት ሊከፍታቸው የሚችላቸው እንደሆኑ ሲወራ መቆየቱንም ዘገባው አክሎ አስታውሷል፡፡

Saturday, 02 January 2016 12:04

ኪነት ጥግ

(ስለትወና)
ትወና ምትሃታዊ ነው፡፡ ገፅታህንና አመለካከትህን ይለውጠዋል፡፡ እናም ማንኛውንም ዓይነት ሰው ልትሆን ትችላለህ።
አሊሺያ ዊት
ሞዴሊንግ በዝምታ የሚከወን ትወና ነው፡፡
አሪዞና ሙሴ፡፡
ትወና ለብቸኝነቴ ያገኘሁለት ግሩም መልስ ነው፡፡
ክሌይር ዴንስ
ትወና ደስ የሚል ስቃይ ነው፡፡
ዣን ፖል ሳርተር
ሙዚቃ ህይወቴ ነው - ትወና የትርፍ ጊዜ ማሳለፊያዬ ነው፡፡
ስቲቭ በርንስ
ሙዚቃ ሚስቴ ስትሆን ትወና ፍቅረኛዬ ናት።
ማርክ ሳሊንግ
ትወና ዝነኛ የመሆን ጉዳይ አይደለም፤ የሰውን ልጅ ነፍስ የመፈተሸር ጉዳይ ነው፡፡
አኔቴ ቤኒንግ
ለትወና አጋሮችህ በጣም ግልፅና በታሪኩ የምታምን መሆን አለብህ፡፡
ራሄል ማክ አዳምስ
ትወና በጣም ጥበባዊ ሙያ ነው፤ ራሳቸውን ተዋናይ አድርገው የሚያስቡ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አሉ፤ እውነተኛ ተሰጥኦ ያላቸው ግን በጣም ጥቂት ናቸው፡፡
ዎልፍጋንግ ፑክ
በቴሌቪዥን ትወናዬ ትልቁ እርካታዬ ከዓለም ጋር የመገናኘት ዕድል ማግኘቴ ነው።
ራይሞንድ ቡር
ጥቂት ፊልሞችን እስክሰራ ድረስ ከትወና ጋር በፍቅር አልወደቅሁም ነበር፡፡ አሁን ግን ያለ እሱ መኖር አልችልም፡፡
ጌራልዲን ቻፕሊን
በሚዲያ ሙሉ በሙሉ  የመረሳትን ዋጋ ከፍዬ ኮሌጅ በመግባት ከትወና ጋር ግንኙነት የሌለውን ፍቅሬን ተወጣሁት የሂሳብ ትምህርት ተማርኩ፡፡
ዳኒካ ማክኬላር
ወላጆቼ ወደ ትወና እንዳልገባ ከመምከር ውጭ ፈፅሞ ጫና አላደረጉብኝም፡፡
ኢሚልያ ፎክስ

መቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል ለሚያስገነባው ህንፃ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የ200 ሺህ ብር ድጋፍ አደረገ፡፡
ባለፈው ማክሰኞ በርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ባህረ ባደረጉት ንግግር፤ ባንካቸው የማዕከሉ ግንባታ ፕሮጀክት ፕሮፖዛል ተጠናቆ ሲቀርብ የበለጠ ድጋፍ እንደሚያደርግ ጠቅሰው፣ በጉብኝቱ ወቅት በተመለከቱት ስሜታቸው በመነካቱ በግላቸው የ10ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ አበርክተዋል፡፡
በመቄዶንያ ስም የዕርዳታ ቼኩን የተረከቡት የማዕከሉ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወ/ሪት ኤልሳቤጥ ንጉሤ፣ በአረጋውን ስም ምስጋና በማቅረብ ሌሎች መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ባለሀብቶችና የግል ድርጅቶች ለማዕከሉ ግንባታ የኩላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
መቄዶንያ፣ መንግሥት ለማዕከሉ ልዩ ትኩረት በመስጠት በአዲስ አበባ ከተማ አያት ዋና መንገድ ላይ ከሊዝ ነፃ በሰጠው 30ሺህ ካ.ሜ ቦታ የአረጋውያን ማዕከል ለመገንባት እየተዘጋጀ ሲሆን ለማዕከሉ ግንባታ 300 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ አስታውቋል፡፡
መቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን ማዕከል፤ በአሁኑ ወቅት ከ850 የሚበልጡ አረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን እየተንከባከበ ሲሆን የተረጂዎቹን ቁጥር 3ሺ ለማድረስ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል፡፡


… የቡዳ ጉዳይ በሀገራችን ባሕል ውስጥ የታወቀ ስለሆነ ለማስረዳት ዝርዝር ውስጥ አልገባም፡፡ ቡዳና ፖለቲካችንን ምን አገናኛቸው ለሚለው ጥያቄ ግን ተገቢ መልስ መስጠት ስለአለብኝ አንዳንድ ጭብጦችን ላስቀምጥ፡፡ ተረቱ እንደሚለው፣ አንድ ቡዶችን ለይቶ የማያውቅ ሰው፣ የቡዶች መንደር ይደርስና፣ “እዚህ አካባቢ የቡዶች መንደር አለ ይባላል፣ የትኛው ነው” ብሎ ራሱን፤ ቡዳውን ይጠይቀዋል፡፡ ቡዳው ሰው፣ “ቡዶች የምንባለው እኛው ነን” ለማለት ድፍረት ስላጣ፣ “እኛ እዛ ማዶ ያሉት ናቸው እንላለን፣ እነሱ ደግሞ እኛን ይሉናል” አለ ይባላል፡፡
ላለፉት አርባ ዓመታት ለውጥ ለመምጣት ከአንድ ትውልድ በላይ ቀላል ያልሆነ መስዋእትነት ተከፍሎዋል። የሀገራችን ፖለቲካ ባለህበት እርገጥ ከመሆን፣ አንዳንዴ ደግሞ የኋሊት ከመሄድ አላለፈም፡፡ ሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ለፀረ - ቅኝ አገዛዝ ትግል ከከፈሉት በላይ ሀገራችን ውድ ዋጋ ከፍላለች፣ የታሰበው ለውጥ ግን አልመጣም፡፡ እዚህ ላይ ዋናው ጥያቄ ለሀገራችን ፖለቲካ ምስቅልቅል ጉዞ ኃላፊነቱን የሚወስደው ማነው? የሚለው ነው። ቢያንስ አንዱ በሌላው ላይ ጣት ከመቀሰር አልፎ የየድርሻችንን እንኳ እንውሰድ ሲባል አይታይም፡፡ እንደቡዳው፤ ስህተት የሠራሁት እኔ ነኝ ከማለት ይልቅ፤ አጥፊዎች እነዛ ናቸው ማለት ይቀላል፡፡ የአንድ ትውልድ ምርጦችን ያለርህራሄ የጨፈጨፈው መንግሥቱ ኃይለማርያም እንኳ “ሰው ይቅርና ዝንብ አልገደልኩም” ነበር ያለው፡፡ ተባባሪዎቹ የነበሩ የደርግ ባለሥልጣናትም ያንን አስከፊ ግፍ የፈጸምነው “የሀገር ፍቅር ያንገበገበን ወታደሮች ነበርን” እያሉ መጽሐፍ እየጻፉ ነው፡፡ የጥፋት ኃላፊነቱንም በሌሎች ላይ እየደፈደፉ ነው፡፡ ቢያንስ ብዙዎቹ በድንቁርና ለጨፈጨፉዋቸው ዜጐች ኃላፊነቱን ለመውሰድ አልተዘጋጁም፡፡ እውነቱን ለመናገር እኔም ባለፈው ጊዜ በጻፍኩት መጽሐፌ ላይ የነገሮችን ሚዛን ለመጠበቅ በጣም አስቸግሮኝ እንደነበረ አስታውሳለሁ። ለአብነት፤ የቀድሞ የመኢሶን ጓዶቼ ከኢሕአፓ ጋር አመሳሰልከን የሚል ቅሬታ እንዳላቸው ነግረውኛል። ታሪክ ፀሐፊዎች ስለ አንድ ድርጊት እርግጠኛ ሆነው መጻፍ ያለባቸው የድርጊቱ ተሳታፊዎች ሲሞቱ ነው የሚሉት የገባኝ አሁን ነው፡፡
አንድ ቀን ከቀድሞ የሕወሓት አመራር አባል ጋር ስለዚህ ጉዳይ አንስተን ስናወራ ለተሠሩት ስህተቶች የኃላፊነት ደረጃ ለድርጅቶች ስጥ ብትለኝ ደርግ አንደኛ፣ ሕወሓት ሁለተኛ፣ ኢሕአፓ ያንተ ድርጅት ስለሆነ ነው ወንጀሉን ያስነሳከው” አለኝ፡፡ የቀልድም ይሁን፤ የምር አስተያየቱ ቢያናድደኝም፣ ገርሞኛል፡፡
በእኛ ትውልድ ስላየናቸው የአፄ ኃይለሥላሴ፣ የደርግና የኢሕአዴግ መንግሥታት የትኛውን ትመርጣለህ ቢባል፣ የየዘመኑ ተጠቃሚ ያለምንም ጭንቀት እራሱ ተጠቃሚ  የነበረበትን ሊመርጥ እንደሚችል ይገመታል። በሕዝብ ደረጃ ሲታሰብ ግን፤ እንደጊዜው ሁኔታ ሊታይ እንደሚችል አያጠራጥርም፡፡ ከቀይ ሽብር በኋላ፣ አብዮቱ የደርግ መንግሥት ጭፍጨፋ እየመረረው ሲመጣ ብዙ ወጣቶች፤ “ተፈሪ ማረኝ፣ የደርጉ ነገር ምንም አላማረኝ” ሲሉ መስማቴን አስታውሳለሁ፡፡ ይህ ምርጫ እንደየ ማህበረሰቡም ሊለያይ ይችላል፡፡ ኦሮሚያና ደቡብ ውስጥ፣ ከዝንጀሮ ቆንጆ…ቢሆንም የደርግ መንግሥት ሊመረጥ ይችላል፡፡ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ውለታ ይሁን፣ የደርግ መንግሥት፣ የመሬት አዋጅ በእነዚህ አካባቢዎች እስከ ዛሬም ድረስ እጅግ በጣም ሰፊ ድጋፍ አለው፡፡
የቡዳ ፖለቲካችንን ከሁሉም በላይ አስቸጋሪ የሚያደርገው ሁሌም ጥፋተኞች እኛ ሳንሆን እነዛ ናቸው ብለን ስለምንደርቅ ነው፡፡ እዚህ ላይ ፈረንጆች የሚበልጡን በሁለት መሠረታዊ ጉዳዮች ነው፡፡ አንደኛው፣ ለነሱ ዛሬ ለደረሱበት ደረጃ ጥፋት መቀበልን እንደሞት አያዩትም፡፡ ሁለተኛ፤ ሥልጣንን የሙጥኝ በማለት አጥፍቶ መጥፋትን ከባህላቸው አስወግደዋል ወይም የኋላቀሮች አስተሳሰብ አድርገውታል፡፡ ቢያንስ ከሂትለር ወዲህ የአብዛኞቹ ጉዞ በዚህ አቅጣጫ ነው፡፡ ሦስተኛው፣ ፖለቲካቸው ሰጥቶ መቀበል ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ሁሉንም አግኝ ወይንም ሁሉንም እጣ (Zero –sum-game) የሚባለውን ፖለቲካ ከልብ እየተው መጥተዋል፡፡ ይበልጥ ደግሞ ከሥልጣን በኋላ፣ ጥሩ ኑሮ መኖርም፣ ክብር ማግኘትም እንደሚቻል አውቀዋል፡፡ እንደውም ከሥልጣን በኋላ ያለጭንቀት የተደላደለ ኑሮ መኖር እንደሚቻል ያውቃሉ፡፡ ኦባማ በአፍሪካ ኅብረት ንግግሩ የአፍሪካ መሪዎችን ለማስተማር የሞከረው ይህንኑ ነው፡፡ ትምህርቱ ገብቶት ይሁን፤ በተለመደው የኢሕአዴግ ባለሥልጣናት የማስመሰል ፖለቲካ፤ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትርም ሲያጨበጭብ አይቻለሁ፡፡ …
(“የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ህልሞች” በሚል ርዕስ አንጋፋው ፖለቲከኛና የፖለቲካ ሣይንስ ምሁር ዶ/ር መረራ ጉዲና ሰሞኑን ለንባብ ካበቁት ሁለተኛ መጽሐፋቸው የተቀነጨበ






Saturday, 02 January 2016 11:51

የዘላለም ጥግ

ልዕልና ወደ ገፅ 11 ዞሯል
(ስለድንቁርና)
- ራስህን ከሀሰተኛ ዕውቀት ጠብቅ፤
ከድንቁርና የበለጠ አደገኛ ነው፡፡
ጆርጅ በርናርድ ሾው
- ድንቁርና የእግዚአብሔር እርግማን ነው፤
ዕውቀት ወደ ገነት የምንበርበት ክንፍ ነው፡፡
ዊሊያም ሼክስፒር
- የራስን የመሃይምነት ልክ ለማወቅ ትልቅ
ዕውቀት ይጠይቃል፡፡
ቶማስ ሶዌል
- ዘረኝነት ከድንቁርና ይመነጫል፡፡
ማርዮ ባሎቴሊ
- ድንቁርና የሰው ልጅ ጭንቅላቱን
የሚያሳርፍበት ለስላሳው ትራስ ነው፡፡
ማይክል ዲ ሞንታ ግ
- ግጭት ከድንቁርናና ከጥርጣሬ ይወለዳል፡፡
ጎርዶን ቢ. ሂንክሌይ
- ድንቁርና የኃጢያቶች ሁሉ እናት ነው፡፡
ፍራንሶይስ ራቤላይስ
- ውይይት የዕውቀት ልውውጥ ሲሆን ክርክር
የድንቁርና ልውውጥ ነው፡፡
ሮበርት ኪውሌን
- በሰው ልጅ ታሪክ ድንቁርና ከዕውቀት ተሽሎ
የተገኘበትን ጊዜ አላውቅም፡፡
ኔይል ዲግራሴ ታይሰን
- ድንቁርና ሁልጊዜ ለውጥን ይፈራል፡፡
ጃዋሃርላል ኔህሩ
- የድንቁርና እውነተኛ ባህርያት፡- እብሪት፣
ኩራትና ትቢት ናቸው፡፡
ሳሙኤል በትለር
- ድንቁርና፣ ጥላቻና ስግብግብነት ተፈጥሮን
እየገደሏት ነው፡፡
ፓውል ሃሪስ
- ድንቁርና ፍርሃትን ይፈለፍላል፡፡
ማይክ ዊልሰን
- በድንቁርና አፈር ላይ ፍርሃት በቀላሉ ሊዘራ
ይችላል፡፡
ሂዘር ብሩክ

እንኳን ለብርሀነ ልደቱ አደረሳችሁማ!
እንዴት ሰነበታችሁሳ!
ስሙኝማ…ያው እንደተለመደው ከተማችን “ታላቅ ቅናሽ” ‘Sale’ ምናምን የሚሉ ማባበያዎች በብዛት እየታዩ ነው፡፡ ኮሚክ እኮ ነው… እዚሀ አገር መጀመሪያስ ነገር ብዙዎቹ ዕቃዎች፣ በተለየ ደግሞ አልባሳት፣ በድርድር አይደል እንዴ ሸመታ የሚካሄደው! እናማ…ከምኑ ላይ እንደቀነሱ ለማወቅም አስቸጋሪ ነው፡፡ መጀመሪያ የ‘እርግጡን ዋጋ’ ሳናውቀው…“ምናምን ፐርሰንት ቅናሽ…” የሚሉትን ባናምን አይፈረድብንም፡፡
ሌላ ደግሞ ‘Sale’ ማለት በሚጢጢው እንደሚመስለን ‘ማጣሪያ’ ሽያጭ ነው እንጂ ‘ታላቅ ቅናሽ’ ቅብርጥስዮ አይደለም፡፡ እናማ ‘Sale’ የምትሉ ሰዎች የመቶ ብሯን ዕቃ በአሥርና በአምስት ብር ምናምን መሸጥ ነው፡፡ ልክ ነዋ… ከ‘አማሪካን’ ሦስትና አራት ሻንጣ ልብስ በስጦታ የሚመጣው ምስጢሩ ‘Sale’ ነው፡፡
ስሙኝማ…እንግዲህ ጨዋታን ጨዋታ ያነሳው የለ… እኔ የምለው፣ የባቡር ሀዲድና ቀላል ባቡር በየድራማው ላይ ብቅ፣ ብቅ ማለት ጀመሩ አይደል! ገና ወላ የዘፈን ክሊፕ፣ ወላ ምን በሉት…ሀዲድ በሀዲድ… ባቡር በባቡር ባይሆን! ደግነቱ እስካሁን ሀዲዱ ላይ መጨፈር አልተፈቀደም መሰለኝ፡፡
ያኔ ቀለበት መንገዱ ‘አዲስ’ የነበረ ጊዜ እንዲሁ ነበር፡፡ የትራፊክ ህግ የለ…‘አካፋዩን መዝለልና ላዩ ላይ ‘አይ ላቭ ዩ ሞር ዛን አይ ካን ሴይ’ አይነት ለአደጋ ያጋልጣል ማለት የለ…ብቻ ምን አለፋችሁ… ሲደነከርበት ከረመላችሁ፡፡
እናላችሁ… ከባቡር ሀዲዱ ጋር መክረማችን ካልቀረ ለምን የዘፈን የምናምን ግጥሞች በዛው አይጻፉልንም፡
ትመጫለሽ ብዬ ማዶ ማዶ ሳይ
ይሄ ቀላል ባቡር መቅረቱ ነው ወይ
አሪፍ አይደል! ልክ ነዋ… ያውም በኤሌትሪክ መቋረጥ አንዳንዴ ቀጥ እያለ ነው እየተባለ ባለበት ጊዜ…በሰዓቱ ትድረስ፣ አትድረስ ማን ያውቃል!
ደግሞም ሌላ አለላችሁ…
በቀላሉ ባቡር መንሸርሸር ለምደሽ
ከእኔ ከድሀው ጋር መች ትሄጃለሽ
ልክ ነዋ! ዘንድሮ ልጄ…
“ድሀ የዋህ ነው…”
“ከጠገበ ሀብታም የተራበ ድሀ ይሻለኛል…”
ምናምን የሚባሉ ነገሮች የመጠቀሚያ ጊዜያቸው አብቅቷል፡፡ ተወደደም ተጠላም እንዲሉት አማርኛ…ተወደደም ተጠላም ፈረንካ ዘንድሮ ሁሉንም ነገር እያሽከረከረ ነው፡፡
እናማ…
“ከእሱ ጋር ቆሎ ቆርጥሜ እኖራለሁ…ከዕለታት አንድ ቀን ያልፍልናል…” ብሎ ነገር የለም፡፡
እናላችሁ ባቡርና ሀዲድ ድራማ ላይ መምጣታቸው ካልቀረ ውሀ ባይኖርም ነገ፣ ተነገ ወዲያ እንደ ‘ቢች’ ማገልገላቸው ካልቀረ ግጥሞች አሁኑኑ ይገጠሙልንማ፡፡
እንደ ባቡሩ ሀዲድ የተጠመጠመው
እንደ ባቡሩ ሀዲድ የተጠማዘዘው
ምን መስሎሽ ነበረ የእኔ ልብ እኮ ነው
ቂ…ቂ…ቂ…. የምር ግን እንዲህ ብሎ የሚገጥም ሰው መጀመሪያ ኤ.ኬ.ጂ. ነው ምናምን የሚሉትን ነገር ነው መታየት ያለበት፡፡
ስሙኝማ…እንግዲህ ከተማችን ‘ህንጣ በህንጣ’ አይደል…ህንጻዎቹ አናት ላይ ሳይቀር ዘፈንና ምናምን ሁሉ ተጀምሯል፡፡ የምር ግን…በዚህ አይነት ነገር ከዓለም ከቀዳሚዎቹ መሀል ሳንሆን አንቀርም። ታዲያላችሁ…
 በህንጻው አናት ላይ የቆምኩት አሁን
 ከሺህ ሰው መካከል አይሽ እንደሆን
ምናምን ማለት አሪፍ አይደል! “ስንቱን አሳልፌው እዘልቀው ይሆን…” የሚለውን ‘አፕዴት’ እንደማድረግ ማለት ነው፡፡
የምር ግን ይሄ የኮፒራይት ነገር መልክ ሲይዝ የዘፈን ግጥም መሞከር አለብኝ፡፡
እንደ ባቡሩ ሀዲድ ልብሽ የረዘመው
አልጎተት አለኝ ብስበው፣ ባስበው
ይሄ አሁን ምን ይወጣለታል!
ስሙኝማ… እንግዲህ ጨዋታን ጨዋታ ያነሳው የለ…በየፊልሙና በየድራማው ላይ መአት ተዋንያን እያየን ነው፡፡ አንዳንዴ ግን… አለ አይደል… “እንደው አሁን ከዚህኛው/ከዚችኛዋ ሻልየሚል  ሰው ጠፍቶ ነው!” እንላለን፡፡
በዛ ሰሞን… አንድ ሬድዮ ጣቢያ ላይ “እንዴት እንደማይተወን የሚያሳዩ ተዋንያን…” ምናምን ተብሎ የተጠቀሰው አይነት ማለት ነው፡፡ እኔ የምለው…እሱ ፕሮግራም ምነው ባለፈው ሳምንት ቄሱም ጭጭ፣ መጽሐፉም ጭጭ ሆነ! ‘ሰዎች አስቀየመ’ እንዴ!
እናማ…‘የማለዳ ኮከቦች’ ላይ የምናያቸው ልጆች የምርም ይቺ አገር የተዋንያን ችግር እንደሌለባት የሚያሳዩ ናቸው፡፡ ዳኞቹ ብዙ ጊዜ የሚጠቀሟትን ቃል ለመጠቀም “የሚገርም ችሎታ” ያላቸው መአት ልጆች አሉ፡፡ እናማ… የተዘጉ በሮች በበዙበት ዘመን የትወና ዓለምን ቶሎ እንዲቀላቀሉ አንድዬ በሩን ወለል አድርጎ ይክፈትላቸውማ!
ስሙኝማ… የድራማዎችን ነገር ካነሳን አይቀር…አሁን፣ አሁን አንዳንዴ ግራ የመጋባት ነገር እየገጠመን ስለሆነ ታሪኮቹን እያጠራችሁልን ሂዱማ!
እንግዲህ ጨዋታን ጨዋታ ያነሳው የለ…ይቺን ስሙኝማ፡፡ እሷዬዋ ለጓደኛዋ ስለሆነ ሰው እየነገረቻት ነው፡፡
“ምን እንዳለኝ ታውቂያለሽ… ‘በጣም ታምሪያለሽ’ አለኝ፣” ትላታለች፡፡
ጓደኝዬዋ ምን ብላ ብትመልስ ጥሩ ነው…
“ፍቅር እውር ነው የሚሉት እውነታቸውን ነው፣” ብላት አረፈች፡፡
የዘንድሮ ጓደኝነት! ያቺኛዋ እኮ በሆዷ… አለ አይደል… “ቆይ ብቻ፣ ቀላል ባቡር ሀዲድ ላይ ክሊፕ ሠርቼ ኮረንቲ ባላስጨብጣት!” ምናምን ልትል ትችላለች፡፡
እናማ ቀላል በባሩንና ሀዲዱን ታሳቢ ያደረጉ ግጥሞች አሁኑኑ ተዘጋጅተው ይቀመጡልንማ፡፡
እኔ እዚህ ታቹን ኮብልስቶን ላይ
አንቺ ከበላዬ በሀዲዱ ላይ
ምሰሶ ቧጥጬ ልመጣ ነው ወይ!
ይቺ የምር አሪፍ ነች፡፡ በነገራችን ላይ ሁሉም ‘ስንኞች’ (“ተባለ!” የሚሉ አራዶች አንድ ዘመን ላይ ነበሩ፣) ለ‘ፍሪ ዳውንሎድ’ ዝግጁ መሆናቸውን ለማሳወቅ ነው፡፡
እስቲ ሸመታውም በልኩ ይሁን…
ሲፑም’ በልኩ ይሁን…
በሰው ሰው ላይ ‘ጆፌ መጣሉም’ ለሌላ ጊዜ ይተላለፍና መልካም የበዓል ሰሞን ይሁንላችሁማ!
ገንዘብ ካጠረ ‘ጥቆማ’…“ገንዘብ ስትበደር ከጨለምተኛ ሰው ተበደር…” የሚሏት ነገር አለች። ለምን መሰላችሁ… ጨለምተኛ ስለሆነ “ገንዘቤን ይመልስልኛል…” ብሎ አያስብማ፡ አሪፍ ስትራቴጂ አይደለች!
ደህና ሰንብቱልኝማ!



Saturday, 02 January 2016 11:50

የገና ዛፍ እውነታዎች!

• የተፈጥሮ ፅድ አሳድጐ ለገበያ ለማቅረብ ከ7-10
ዓመት ይፈጃል፡፡
• በአሜሪካ 98 በመቶ ያህሉ የገና ዛፍ የሚያድገው
በእርሻ ማሳ ነው፡፡
• በአሜሪካ ከአንድ ሚሊዮን ሄክታር በላይ
የሚሆን መሬት ለገና ዛፍ እርሻ ይውላል፡፡
• በአሜሪካ 21 ሺህ የተፈጥሮ ፅድ አብቃይ ገበሬዎች
አሉ፡፡
• በአሜሪካ በገና ወቅት የተፈጥሮ ፅዶች ከተቆረጡ
በኋላ እንዳይበላሹ በግል በሄሊኮፕተሮች
ይሰበሰባሉ፡፡
• በአሜሪካ በየዓመቱ ከ34 እስከ 36 ሚሊዮን
የሚደርሱ የተፈጥሮ የገና ዛፎች የሚመረቱ ሲሆን
95 በመቶ የሚሆኑት ወደ ውጪ አገር የሚላኩ
ናቸው፡፡ ከዚህ ውስጥ አብዛኛዎቹ የሚሸጡት
ማሳው ላይ እንዳሉ ነው፡፡
• በአሜሪካ “ብሔራዊ የገና ዛፍ ማህበር” በየዓመቱ
ለአገሪቱ ፕሬዚዳንት የገና ዛፍ ስጦታ ይልካል፡፡
• ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ የቆመውና በልዩ ልዩ
ጌጣጌጦች የተዋበው የገና ዛፍ የተሰራው እ.ኤ.አ
በ1510 ዓ.ም በላቲቪያ ነው፡፡
• በአሜሪካ አንድ መቶ ሺህ ያህል ግለሰቦች በገና
ዛፍ ፋብሪካ ውስጥ ተቀጥረው ይሰራሉ።