Administrator

Administrator

ኩኑዝ ኮሌጅ ከደረጃ ሁለት እስከ አራት በአካውንቲንግ ያስተማራቸውን 81 ተማሪዎችና ሁለት መፅሃፍት ዛሬ ከጠዋቱ 3 ሰዓት በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ትያትርና ባህል አዳራሽ እንዲያስመርቅ አስታወቀ፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ረዳት ፕሮፌሰር በድሉ ዋቅጅራ በክብር እንግድነት ይገኙበታል ተብሎ በሚጠበቀው የምረቃ ሥነስርዓት ላይ “የኢትዮጵያ የትምህርት ችግሮች ያስከተለው ኪሳራና መፍትሄዎች” የሚለውና “ወርቃማ ቁልፍ” የተሰኘ የእንግሊዘኛ ማስተማሪያ መፅሃፍ ይመረቃሉ ተብሏል፡፡ መፅሃፎቹን ያዘጋጁት የኩኑዝ ኮሌጅ እና የሜሪት የቋንቋ ትምህት ቤት ባለቤትና ፕሬዝዳንት አቶ ተስፋዬ ለጋ ናቸው፡፡
በተያያዘ ዜና ቅድስት ልደታ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ በነርሲንግ፣በፋርማሲና በህክምና ላብራቶሪ የሰለጠኑ 169 ተማሪዎችን ነገ ከጠዋቱ 2 ሰአት፣ አምስት ኪሎ በሚገኘው የጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ ያስመርቃል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ በምርቃት ሥነስርዓቱ ላይ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በሌላም በኩል ኒው ጄኔሬሽን ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 250 ተማሪዎች ዛሬ ያስመርቃል። ተማሪዎቹ የሚመረቁት ሜክሲኮ አደባባይ በሚገኘው የአፍሪካ ህብረት አዳራሽ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የትያትር ጥበባት መምህር የሆኑት አቶ ኤፍሬም ለማ ያዘጋጁት “መሰረታዊ የፊልም ድርሰት አፃፃፍ ዘዴ” መፅሃፍ ነገ ይመረቃል፡፡ መፅሃፉ በቀኑ 8ሰዓት የሚመረቀው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስድስት ኪሎ ግቢ፣ ኔልሰን ማንዴላ አዳራሽ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ትያትር በኢትዮጵያ ኪነጥበብ ጉልህ ድርሻ ያላቸውን ከያንያን ዛሬ እንደሚዘክር አስታወቀ፡፡ የትያትር ቤቱ ባልደረቦች “የኢትዮጵያ ብሄራዊ ትያትርን በአዲስ ራዕይ” በሚል መርህ በሚያቀርቡት ዝግጅት ላይ በትያትር ቤቱ የሰሩ እና ሌሎች አንጋፋ ባለሙያዎች ልምዳቸውን የሚያካፍሉ ሲሆን የቀይ ምንጣፍ አቀባበልና የምሳ ግብዣ እንደሚደረግላቸው ትያትር ቤቱ ጨምሮ ገልጿል፡፡

Saturday, 31 August 2013 12:40

ላ-ቦረና ሰኞ ይመረቃል

በኢንጂል አይስ ፊልም ፕሮዳክሽን የተዘጋጀውና በደራሲ ዮናታን ወርቁ የተደረሰው ላ-ቦረና ፊልም፣ የፊታችን  ሰኞ በ11 ሰዓት በብሄራዊ ትያትር ቤት ይመረቃል፡፡ በላይ ጌታነህ ዳሬክት ያደረገው ፊልሙ፣ በአንዲት ፈረንሳዊት አንትሮፖሎጂስት ጥናት ላይ ያተኮረ ሲሆን የቦረናን ባህልና ወግ ያንፀባርቃል  ተብሏል፡፡ በፊልሙ ላይ አለም ሰገድ ተስፋዬ፣ ማርያኔ ቤለርሰን፣ አንተነህ ተስፋዬና ሌሎችም ተውነውበታል፡፡ ፊልሙ የ1፡40 ርዝማኔ እንዳለውም ተገልጿል፡፡

(ነገር ንአጓዲኣ ትልክም፣ ታኼላ ንኣታዊኣ ተስጥም)

ከእለታት አንድ የክረምት ቀን፣ አንዳች አውሎ ንፋስ በመጣ ሰዓት፤ ፈረስ፣ በሬ እና ውሻ አንዱን የሰው ልጅ እንዲያስጠልላቸውና እንዲያሳድራቸው ለመኑት፡፡ ሰውዬው መልካም ፈቃዱ ሆነ፡፡ የክረምቱ ብርድ በርዷቸዋልና ይሞቃቸው ዘንድ እሳት አነደደላቸው፡፡ የሚተኙበት ምቹ ስፍራም ሰጣቸው፡፡ ይበሉት እንዳይቸገሩም ለፈረሱ ገብስ ሰጠው፡፡ ለበሬው ጭድ ሰጠው፡፡ ለውሻውም ከራሱ ራት ከተረፈው ፍርፋሪ አቀረበለት፡፡
በነጋታው ነፋሱ ካቆመ በኋላ ሲለያዩ ምሥጋናቸውን ለሰውዬው ለማቅረብ አሰቡ፡፡
“እንዴት አድርገን እናመስግነው?” አለ ፈረስ፡፡
“የሰውን ልጅ እድሜ እናስላና፤ በየፊናችን ተካፍለን፣ ያለንን ጥሩ ጠባይ ብንሰጥስ?” አለ ውሻ፡፡
“እንዴት ማለትህ ነው?” ሲል ጠየቀ በሬ፡፡
ውሻም፤
“እያንዳንዳችን ልዩ ችሎታ አለን አይደል? ያንን የው ልጅ እድሜ፣ ከእድሜው ጋር በሚሄደው ፀባዩ አንፃር እናጤነዋለን” አለ፡፡
ፈረስ፤
“አሁንም ልትል የፈለግኸው በደንብ አልገባኝም”
ውሻ፤
“ልዘረዝርልህ እኮ ነው፡፡ ለምሳሌ በመጀመሪያ የህይወቱ ክፍል፣ የሰው ልጅ ወጣት ነው፡፡ ለዚህ የሚሆን ጠባይ ማን ይስጠው?” ሲል ጠየቀ፡፡
ፈረስ፤
“እኔ እሰጠዋለሁ” አለና ሰጠ፡፡ በዚህ ረገድ ወጣቶች ሁሉ ትእግስት-የለሽና ጉልበተኛ እንዲሆኑ ሆኑ፡፡
ውሻ ቀጠለና፣
“ቀጥሎ፣ ሁለተኛው የህይወቱ ክፍል የመካከኛ እድሜ ጐልማሳነቱ ነው - ለዚህስ የሚሆን ፀባይ ማን ይስጠው?” አለ፡፡
በሬ፤
“እኔ እሰጠዋለሁ፡፡ የእኔን ጠባይ ይውሰድ” አለ፡፡ እውነትም የሰው ልጅ በመካከለኛ እድሜው በሚሰራው፣ ሥራ ዘላቂ ምን ጊዜም ደከመኝ የማይል፣ ምንጊዜም ታታሪ የሆነ ባህሪ ኖረው፡፡
በመጨረሻም ውሻ፤
“የሽምግልና ጊዜ ጠባይን እኔ እለግሰዋለሁ” አለ፡፡ በዚህም መሰረት የሰው ልጅ በእርጅናው ጊዜ ነጭናጫና በትንሹ የሚያኮርፍ፣ “ውሻ በበላበት ይጮሃል” እንደሚባለው ምግብ ላበላውና ምቾት ለሀጠው የሚያደላና፤ ፀጉረ - ልውጥ ሰው ላይ ግን የሚጮህና የሚናከስ ሆነ፡፡
***
ትእግስት-የለሽና ጉልበተኛ ወጣቶች ለአደጋ ይጋለጣሉ፡፡ ዘላቂና ታታሪ ዜጐች ለሀገር ህልውና ዋና ቁምነገር ናቸው፡፡ የሽማግሌዎች መርጋትና መሰብሰብ፤ ለሀገር የረጋ ህይወት መሰረት ነው፡፡ በአንፃሩ ሽማግሌው ነገር ፈላጊ፣ ጉልቤ ልሁን ባይ፣ የማያረጋጋ ከሆነ የአገር አደጋ ነው፡፡ የፈረሱም፣ የበሬውም፣ የውሻውም ባህሪ በሰው ልጆች ህይወት ውስጥ ወሳኝነት ያላቸው ጉዳዮች እንደመሆናቸው፤ ህብረተሰባችንን ለመመርመር ያግዙናለ፡፡ በየሥራ ምድቡና በየሀብት መደቡ፣ እንዲሁም በአገር አመራር ደረጃ ባሉ ዜጐች ላይም ይንፀባረቃሉና፡፡
የሀገር መሪዎች ወደ አመራሩ ቡድን ፊታቸውን ሲያዞሩ፤ ለህዝቡ ጀርባቸውን መስጠታቸው አይቀሬ ነው ይላሉ የፖለቲካ ፀሐፍት፡፡ ”ከጭምብሉ በስተጀርባ” በተባው መፅሐፍ ደራሲው ባድዊን፤
“ኦርኬስትራውን ለመምራት የሚፈልገው ኅብረ-ዜማ - አቀናጅ (Conductor) ጀርባውን ለተመልካቹ ህዝብ ይሰጣል” ይለናል፡፡
ኦርኬስትራው መስመር ከያዘ በኋላ ግን ወደ ህዝቡ መዞር ያስፈልጋል፡፡ ኦርኬስትራውም የሚያነጣጥረው ተመልካቹ ላይ ነው፡፡ የኅብረ-ዜማውን ቃና ማጣጣም ያለበት ህዝቡ ነው፡፡ ኦርኬስትራውም ሆነ መሪው ኅብረ-ዜማው ለኅሩያን ኅዳጣን (ለጥቂቶች ምርጦች እንዲሉ) ብቻ እንዲሰማ ከሆነ የታቀደው፤ አዲዮስ ዲሞክራሲ!
በሀገራችን እንደተመላላሽ በሽተኛና አልጋ ያዥ በሽተኛ ተብለው ሊከፈሉ የሚችሉ አያሌ ችግሮች አሉ፡፡ አንድኞቹ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሳይገባ በፊት ሲነገሩ፣ ሲመከሩ የሚሰሙ ዜጐች “እሺ፤” ጐርፍ ከመጣም ሲደርስ እናቋርጠዋለን” የሚሉ የሚፈጥሩት ነው፡፡ ሁለተኞቹ ጐርፍ እሚባል ከነጭራሹም ሊመጣ አይችልም፤ የሚሉቱ የሚፈጥሩን ችግር ነው፡፡ ሦስተኞቹ ሀሳቡን ወይም መረጃውን ያመጡትን ክፍሎች “በሬ ወለደ ባዮች” ብለው የሚፈርጁ በመሆናቸው የሚፈጠር፡፡ አራተኞቹ ግን በጣም ጥቂቶቹ ምክር ተቀብለው፤ ድምፅ የላቸውም እንጂ፣ እንጠንቀቅ እያሉ ጥሩ ደወል ቢያሰሙም የመደማመጥ ችግር ነው፡፡ ደጋግመን በከበደ ሚካኤል ልሳን እንደተናገርነው፡- ዛሬም “…አሁን የት ይገኛል ቢፈልጉ ዞሮ
መስማት ከማይፈልግ የባሰ ደንቆሮ”
እንላለን፡፡
እንሰማማ፡፡ ችግሮች ይግቡን፡፡ ቀድመን ሁኔታዎችን እንይ! የቅድመ-አደጋ ጥሪ ማዳመጥን ትተን፤ ጐርፉ ሲመጣ አንጩህ፡፡ ጉዞ እሚሰምረው ነገር ማጣጣም ሲኖር ነው፡፡ ጉዞ ይሳካል እሚባለው ቅድመ-እንቅፋትን ማየት ሲቻል ነው፡፡
እንቀሰቅሳለን ያልነው መንገድ ውሎ ሲያድር ምን እሳት ይዞ እንደሚመጣ እናስተውል፡፡ “እዚያም ቤት እሳት አለ!” ጨዋታ ንግገር አይደለም፡፡ ቀድሞ ማስላት ጉዳት የለውም፡፡ የቀደሙ ስህተቶችንም አውቆ ማረም ነውር አይደለም፡፡ እሳቱ ሲለኮስ ማገዶ ሲጫር ያልነቃ ልቦና፤ ብዙ ጊዜ አደጋ ያስተናግዳል፤ ይባላል፡፡
የተዳፈነ እሳትን ለማንቃት መሞከር አላግባብ ድካም ነው፡፡ ያ እሳት ከተንቀለቀለ ደግሞ ራስንም ጭምር ያነዳል፡፡ ይሄ ማለት ደግሞ፤ እንደትግሪኛው ተረት፤ “ነገር ለጫሪዋ ትተርፋለች፣ ረግረግ የረገጣትን ታሰጥማለች” ማለት ነው፡፡

አቢሲኒያ ባንክ ዘንድሮ 351.2 ሚሊዮን ብር አጠቃላይ ትርፍ ማግኘቱንና ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ12.2 በመቶ ብልጫ እንዳለው ገለፀ፡፡ ባንኩ በላከው መግለጫ ላይ እንዳስታወቀው፤ የባንኩ አጠቃላይ ገቢ 895 ሚሊዮን ብር መድረሱንና ካለፈው ዓመት በ126 ሚሊዮን ብር ብልጫ ያለው መሆኑን ጠቁሟል፡፡ ለተለያዩ የንግድና አገልግሎት ዘርፎች በአጠቃላይ 4.7 ቢሊዮን ብር ብድር የሰጠ መሆኑን የገለፀው ባንኩ፤ አጠቃላይ ተቀማጭ ሂሣቡ 8.5 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቋል፡፡ አቢሲኒያ ባንክ 371ሺ 420 የሚሆኑ የገንዘብ አስቀማጭ ደንበኞች እንዳሉት መግለጫው ጠቅሶ፤ በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞችና ክልሎች 82 የሚደርሱ ቅርንጫፎችን ከፍቶ ለደንበኞቹ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ አመልክቷል፡፡

Saturday, 31 August 2013 11:48

አገሬ፣ እኔ እናሻማ!

መሸ
ቤቴ ገባሁ፡፡
ያው ደሞ እንዳመሉ
እንደባህሉ ሁሉ …መብራቱ ጨልሟል፡፡
እና ሻማ ገዛሁ
በሻማው ብርሃን፣ ልፀዳበት አሰብሁ፡፡
እና ሻማ ገዛሁ…ሁሉንም ባይሆንም
አንድ ሁለት አበራሁ
በሻማው ብርሃን …መንፈሴን አፀዳሁ
እንደ አያቴ መስቀል
እንደሼኪው ሙሰባህ
እንደ አበው መቁጠሪያ
እንደአገሬ ማተብ …እንዳገሬ ክታብ
አምኜ ጀመርኩኝ፣ ማስታወሻ መፃፍ
ህይወት ባገኝ ብዬ፣ ከጨለማው ደጃፍ፡፡

ከሐምሌ ጨለማ
ከጨረቃዋ ሥር፣ ጉም ከተናነቃት
ክረምቱ ዘንቦባት
ብርድ እንደዛር - ውላጅ፣ እያንቀጠቀጣት፤
አገሬ ጨልማ፤
በእንግድነት ቤቴ፣ መጥታ ልትጠይቀኝ
“መብራቴን ሸጫለሁ፣ ሻማ ለኩስልኝ”
ብላ ለመነችኝ፡፡
“የሸጥሽበት ገንዘብ፣ የት ደረሰ?” አልኳትኝ፡፡
(ይሄኔ ነጋዴ ኖሮ ቢሆን ኖሮ፤ “አትርፋለች?” ባለኝ፡፡
ይሄኔ አንድ ምሁር፣ ኖሮ ቢሆን ኖሮ
ማን ፈቅዶ ነው ይሄ፣ ምን ‘ማንዴት’ አላቸው?
ጉድ መጣ ዘንድሮ፤
ኖሮ ቢሆን ኖሮ፣ የጋዜጣ አንባቢ፤
“ህዝብ ያቃል ይሄንን?
ደባ ሲሰሩ ነው!” ባለ ነበር ምሩን
ሁሉን አስባበት፣ ሻማዊ ሳቅ ሳቀች
ሁሉን አስቤበት፤ ሻማዊ ሳቅ ሳኩኝ፡፡

ከነልብሴ ተኛሁ፣ ብርድ ልብስም የለኝ፡፡
እሷም ሌጣዋን ነች፤ ጐኔ ገለል አለች፡፡
ልክ ዐይኔን ስከድን፣ ቀና አለች ወደኔ
“ሻማውን አጥፋ እንጂ፤ ለነገ አታስብም?
የቁጠባ ባህል፣ ዛሬም አልገባህም?!”
ስትል ገሰፀችኝ፡፡

ሻማው ሰማ ይሄንን፣ ጣልቃ ገባ እንዲህ ሲል
“መብራት ከሄደበት፣ እስኪመለስ ድረስ
ዓመት ፍቃድ ላይ ነኝ፣ ይሁን ልሥራ ለነብስ
የበራሁ መስዬ፣ ተዉኝ ትንሽ ላልቅስ!
ብቻ ወዳጆቼ፤
እንሰነባበት፣ እንሳሳም በቃ፤
ስለማይታወቅ፣ ነግ ማን እንደሚከስም
ነግ ማ እንደሚነቃ!!”
(የነገን ማን ያውቃል ለሚሉ)
ከግንቦት 2004-2005 ዓ.ም

“ሆራይዘን ቢዩቲፉል ፊልም ውዝግብ አስነሳ” በሚለው ዘገባ ”ብሉ ናይል የፊልም እና ቴሌቪዥን አካዳሚን የሚመለከት ዘገባ መውጣቱ ይታወሳል፡፡ ይሁን እና የቀረበው አጭር ዘገባ የተዛቡ መረጃዎችና ስህተቶችን የያዘ በመሆኑ እንደሚከተለው እንዲታረም እንጠይቃለን፡፡
ለመነሻ ያህል ሆራይዘን ቢዩቲፉል በብሉ ናይል የፊልም እና የቴሌቪዥን አካዳሚና ቴል ፊልም በተባለ የስዊዘርላንድ ድርጅት የተሰራ የትምህርታዊ ፕሮጀክት ፊልም ሲሆን፣ ትምህርት ቤቱ በፊልሙ ስራ የተሳተፈበት አላማም ተማሪዎቹ ልምድ ካላቸው የውጭ የፊልም ባለሞያዎች ጋር ጐን ለጐን የሚሰሩበትን ተግባራዊ ልምምድ በማመቻቸት፣ የፊልም ስራ ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩ ማስቻል ነው፡፡
ተማሪዎች በትምህርታዊ ፕሮጀክቱ ላይ የሳተፉት ገንዘብ እንደሚከፈላቸው ተነግሯቸው ሳይሆን ከፕሮጀክቱ ለመማር እና ራሳቸውን የተሻለ የፊልም ባለሞያ ለማድረግ በሙሉ ፈቃደኝነትም ጭምር ነው፡፡ በፊልም ስራው ላይ ከተለያዩ የትምህርት ዘመን የተውጣጡ ከ35 በላይ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን፣ በፕሮዳክሽኑ መጨረሻ ከተማሪዎቻችን ጋር በተደረገው ግምገማ እና ውይይትም ትምህርታዊ ፕሮጀክቱ እጅግ ውጤታማ እና ተማሪዎቹ በርካታ ጠቃሚ እውቀት እና ልማዶችን ያካበቱበት መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡
የጋዜጠኛዋ ዘገባ፣ በፊልሙ ላይ የተሳተፉ ተማሪዎች አካዳሚው የሚገባንን ክፍያ እንዲሁም አንድ አመት የተማርንበትን ሰርተፊኬት ከልክሎናል እንዳሉ ያትታል፡፡ “ሆራይዘን ቢዩቲፉል” ብሉ ናይል የፊልም እና ቴሌቪዥን አካዳሚ ቀደም ሲል ያስመረቃቸው እንዲሁም በወቅቱ በትምህርት ላይ የነበሩ ከ35 በላይ ተማሪዎች የተሳተፉበት ፊልም ነው፡፡ ጋዜጠኛዋ ክፍያ እና ሰርተፊኬት ተከልክለናል ያሉትን ግለሰቦች ስም ለመጥቀስ አልፈለችም፡፡ ከትምህርት ቤቱ ምክትል ስራ አስኪያጅ ጋር ባደረገችው ቃለ ምልልስ ሁሉንም ተማሪዎች እንደምታነጋግር ቃል የገባች ሲሆን ትምህርት ቤቱም በፊልሙ ላይ የተሳተፉትን ተማሪዎች ስም ዝርዝር እና ስልክ ቁጥር ሰጥቷት ነበር፡፡ ጋዜጠኛዋ በወቅቱ እንደገለፀችው “ከተማሪዎቹ አንዳቸውም እንኳን ከላይ ክፍያ እና ሰርተፊኬት ተከልክለናል በሚለው ባይስማሙ በዘገባው ላይ ይህ ጥያቄ የተማሪዎቹ ጥያቄ እንደሆነ አድርጐ ማውጣት አግባብ አይደለም” ብላለች፡፡ ይሁን እና ሁሉንም ተማሪዎች ይቅርና የተማሪዎቹን ድምጽ ለመወከል የሚበቃ ቁጥር ያላቸውን ሳታናግር ብሉ ናይል የፊልም እና የቴሌቪዥን አካዳሚ ከመላው ተማሪዎቹ ጋር ተቃርኖ ውስጥ የገባ በማስመሰል ለማቅረብ ሞክራለች፡፡ የጥቂት ግለሰቦች አጀንዳ የሆነን ጉዳይ ግለሰቦቹን በማንነታቸው ከማቅረብ ይልቅ “ተማሪዎች” ከሚል መከለያ ጀርባ በመደበቅ ለማራመድ መሞከር ተገቢ የጋዜጠኝነት ስነ ምግባር አይመስለንም፡፡
“ተማሪዎቹ ተከለከልን አሉ” ስለተባለው ሰርተፊኬት ጉዳይም ለጋዜጠኛዋ የሰጠነው መልስ “…ያላሟሉት ነገር ቢኖር ነው” የሚል የመላምት መልስ ሳይሆን የሚከተለውን ነው፡፡ በፊልሙ ላይ የተሳተፉት ከተለያየ አመት የተውጣጡ ተማሪዎች እንደመሆናቸው መጠን፣ ከፊሎቹ ትምህርታቸውን አጠናቀው ፊልሙ ከመጀመሩ በፊት ሰርተፊኬታቸውን የወሰዱ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በወቅቱ በትምህርት ላይ የነበሩ ናቸው፡፡ ከእነዚህም መሀከል ከትምህርት ገበታ አለመቅረትን፣ የልምምድ እና የመመረቂያ ፕሮጀክት መስራትን እንዲሁም ስነ ምግባርን ጨምሮ በትምህርት ቤቱ መመሪያ መሰረት ማሟላት ያለባቸውን ቅድመ ሁኔታ ያሟሉ ተማሪዎች የመመረቂያ ሰርተፊኬት የወሰዱ ሲሆን ይህን ላላጠናቀቁ ተማሪዎች ሰርተፍኬት መስጠት ግን የትምህርት ቤቱ ደንብ አይፈቅድም፡፡
3. ዘገባው ብሉ ናይል የፊልም እና የቴሌቪዥን አካዳሚ ከቴል ፊልም ስዊዘርላንድ ጋር በመተባበር የሰራው ፊልም ወደፊት ትርፍ ከተገኘበት ለፀሐፊዎቹ 10% ይከፈላል እንዳለ ይገልጻል፡፡ ለጋዜጠኛዋ በሁለቱ ድርጅቶች መሀከል የተፈረመውን የፕሮዳክሽን ስምምነት ከነአማርኛ ትርጉሙ የሰጠናት ከመሆኑም በላይ በቃለ መጠየቁ ወቅት ቃል በቃል እያነበብን እንዳስረዳነው፣ ከፊልሙ ከሚገኝ ማናቸውም ገቢ የተጣራ ትርፍ ላይ ቴል ፊልም የተባለው የስዊዘርላንድ ድርጅት ለፊልሙ ዋና ፀሐፊ ለሆነው የውጭ ዜጋ 10 በመቶ የሚከፍል ሲሆን፤ ይህም በአራቱ ፀሐፊዎች መሀከል እኩል የሚከፋፈል ይሆናል፡፡ ብሉ ናይል ለፀሐፊዎች የ10 በመቶ ክፍያ ይከፍላል የሚል መረጃ አልሰጠንም፤ በፕሮዳክሽን ስምምነቱም ውስጥ የተገለፀው ይህን አይደግፍም፡፡
4. ዘገባው የፊልሙ ክፍያን በተመለከተ በተነሳው ውዝግብ ፊልሙ ለእይታ እንዳልበቃ ጠቅሷል፡፡ ይህ ዘገባ ስህተት ሲሆን ትምህርት ቤቱ እስከሚያውቀው ድረስ ፊልሙ ለእይታ ያልበቃው የፖስት ፕሮዳክሽን ስራው ተጠናቆ ባለማለቁ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ይህ ተጠናቆ ፊልሙ በተለያዩ የውጭ አገር ፌስቲቫሎች ላይ በመታየት ላይ መሆኑን ከፊልሙ የፌስ ቡክ ገጽ መረዳት ይቻላል፡፡ ፊልሙ በአገር ውስጥ ለመታየት ያልቻለውም እንደተባለው በክፍያ ውዝግብ ሳይሆን በፊልሙ ላይ ምንም መብት የሌለው እና የቀድሞ የትምህርት ቤቱ ተማሪ የነበረ ግለሰብ፣ ከትምህርት በቱ ፈቃድ ውጭ ፊልሙን ለማሳየት በዝግጅት ላይ መሆኑን ትምህርት ቤቱ በመረዳቱ እና ይህን ለማስቆም ለሚመለከታቸው አካላት ባቀረበው አቤቱታ መሰረት፤ ትምህርት ቤቱ የፊልም ባለቤትነቱን በማረጋገጥ ሂደት ላይ በመሆኑ ነው፡፡ ይህ ከተጠናቀቀ በኋላ ለእይታ የሚቀርብ ይሆናል፡፡ ከዚህ ውጭ ፊልሙ በሌሎች ወገኖች ለእይታ ቢቀርብ ግን ትምህርት ቤቱ ህጋዊ እርምጃ የሚወስድ ይሆናል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ጋዜጠኛዋ ያቀረበችው መረጃ የአንድ ወገን እይታን ብቻ ያንፀባረቀ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡
ዘገባው ተማሪዎቹን እና ጸሀፊዎቹን ለያይቶ ለማቅረብ ያልቻለ ቢሆንም የፊልሙ ጸሀፊዎች የፊልሙን ጽሁፍ በሚያዘጋጁበት ጊዜ እያንዳንዳቸዉ 2500 ብር ብቻ እንደተከፈላቸዉ እና ለትራንስፖርት እና ሌሎች ወጪዎች ከኪሳቸዉ ሲያወጡ እንደነበረ ይገልጻል፡፡ አሁንም የጸሀፈዎቹን ስም ለመግለጸ እንዳልተፈለገ ልብ ይሏል፡፡ በቃለ መጠይቁ ወቅት ጋዜጠኛዋ ጸሀፊዎቹ ምንም አይነት ክፍያ እልተሰጠንም እንዳሏት ገልጻ፣ ይህ ለምን እንደሆነ ጠይቃለች፡፡ በምላሹም ይህ ስህተት እንደሆነ እና ምንም እንኳን ፊልሙ ትምህርታዊ ፕሮጀክት ቢሆንም ጸሀፊዎቹ በስራ ወቅት ለሚያወጡት ወጪ እና ከሌላ ስራ ያገኙት የነበረዉን ገቢ በጥቂቱም ቢሆን ለማካካስ በየወሩ 2500 ብር ሲከፈላቸዉ እንደነበረ፣ ለትራንስፖርት እና ሌሎች ወጪዎችም ባቀረቡት ደረሰኝ መሰረት እንደተከፈላቸዉ ገልጻ ለዚህም በእጃችን የነበረዉን ማስረጃ አሳይተናል፡፡ ይሁን እና ጋዜጠኛዋ የእኛን መልስ እና ማስረጃ ወደጎን በመተዉ ይልቁንም ያቀረብነዉን ማስረጃ እነዚህ ግለሰቦች የሰጡትን የተሳሳተ ማስረጃ “የተከፈለን 2500 ብር ብቻ ነዉ” ወደሚል ማስተካከያ ለመቀየር ተጠቅማበታለች፡፡ አንድ ጋዜጠኛ የተሰጠዉ መረጃ ስህተት አንደነበረ የሚያረጋግጥ መረጃ ሲደርሰዉ ይህን እንዳላዩ ማለፍ እና ይበልጡንም የሀሰት ማስረጃ የሰጡትን ግሰቦች ቃል ለማስተካከል መጠቀሙ ወገንተኝነትን የሚያሳይ ከመሆኑም በላይ የጋዜጠኛዉን ሀቀኝነት እና ተአማኒነት ጥያቄ ዉስጥ የሚጥል ነዉ፡፡
በዘገባዉ የቀረበዉ የገንዘብ መጠንም እንዲሁ ገንዘቡ ወደብር ሲለወጥ በፊልሙ ዝግጅት ወቅት ከአንድ አመት ከሰባት ወር በፊት ባለው የምንዛሪ ሂሳብ ሳይሆን ዛሬ ባለዉ በመሆኑ ስህተት ነዉ፡፡ በዚህም መሰረት የገንዘብ መጠኑ እንደተባለዉ 360,400 ብር ሳይሆን 252,000 ብር ነው፡፡
ከላይ የተገለጻዉን ገንዘብ አጠቃቀም በተመለከተም ብሉ ናይል የፊልም እና ቴሌቪዥን አካዳሚ ከተቋቋመበት አላማም ሆነ “ከሆራይዘን ቢዩቲፉል” ትምህርታዊ የፊልም ፕሮጀክት አላማ አኳያ፤ ትምህርት ቤቱ ገንዘቡን በደሞዝ መልክ ማከፋፈል ሳይሆን ተጨማሪ ትምህርታዊ የፊልም ፕሮጀክቶችን በመስራት ነባር እና መጪ ተማሪዎች ክህሎታቸዉን እንዲያዳብሩ የማድረግ አቋም ያለዉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ከሰላምታ ጋር
ብሉ ናይል የፊልም እና የቴሌቪዥን አካዳሚ

ከአዘጋጁ፡- የድምፃዊ ኢዮብ መኮንን ድንገተኛ ህልፈትን ተከትሎ በፌስቡክ ላይ ከወጡ በርካታ አስተያየቶች ጥቂቶቹን እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡ ለባለቤቱ፣ ለቤተሰቡና ለወዳጅ ዘመዶቹ መፅናናትን እንመኛለን፡፡
ከጥቂት አመታት በፊት አንድ የበጎ አድራጎት ትርኢት ላይ ለመሳተፍ፣ ከዘፋኞች ጋር ወደ ደሴ ተጉዤ ነበር፡፡ የተሣፈርንበት አውቶብስ ጉንጫቸውን በጫት አሎሎ በወጠሩ ዘፋኞች ተሞልቷል፡፡ ዘፋኞቹ ሲሻቸው ይተራረባሉ፣ሲሻቸው ይጮሃሉ፣ይጨፍራሉ፡፡ የአውቶብሳችን ሽማግሌ ሹፌር ሳይቀር፣አልፎ አልፎ መሪውን እየለቀቀ በማጨብጨብ፣ በ ‹‹ቅወጣ›› ከዘፋኞች እንዳማያንስ በማሳየት ላይ ነበር፡፡ በጫቱም፣በጭፈራውም የሌለበት ድምጻዊ ኢዮብ መኮንን ብቻ እንደሆነ ተመለከትሁ፡፡ በእርጋታ ተቀምጦ፣ በአውቶብሱ መስኮት አሻግሮ የሚሮጡ የግራር ዛፎችን ይመለከታል፡፡ ልዩነቱ ግልጽ ነበር፡፡
ድሮ ድሮ፣ ኢዮብ መኮንን አቤሴሎም የሚዘናፈል ረጅም ጸጉር ያለው ጎልማሳ ነበር፡፡ ድንገት ጸጉሩን ተሸለተ፣ ከጸጉሩ ጋር የጥንት ባህርይውን አራገፈ። ጭምት፣ መንፈሳዊና በመጽሐፍ ቅዱስ ፍቅር የነደደም ምዕመን ሆነ፡፡
በተገናኘን ቁጥር፣ኢዮብ ስለእምነት እንድንወያይ ይፈልጋል፡፡ ብዙ ጊዜ እምነት የሚያጠብቅ ሰው አንዳች ችግር ይኖርበታል ብዬ አስብ ነበር፡፡ ኢዮብ ግን እጅግ መልካም ሊባል በሚችል ሕይወቱ፣ ይሄንን አመለካከቴን ውድቅ አድርጎብኛል፡፡
የዛሬ ሳምንት ገደማ ኢዮብ ዘፈን በመሥራት ላይ ነበር፡፡ እና ለአንድ ዜማው ግጥም እንድሠራለት ጋበዘኝ፡፡ ከዚህ በፊት የሞከርኳቸው የዘፈን ግጥሞች ስለከሸፉብኝ ግብዣውን ለመቀበል አመነታሁ፡፡ ግን ደሞ ወዲያው፣በኢዮብ ድምጽ ግጥሜ ተዘፍኖልኝ ለማየት ጓጓሁ፡፡ ውሀ ልማት አካባቢ፣ሌክስ ፕላዛ ሕንጻ ሥር መኪናው ውስጥ ቁጭ ብለን ዜማዎችን ማድመጥ ጀመርን፡፡ ዘፈኑ ውስጥ ያሉት ሐሳቦች አብዛኞቹ ወደ መዝሙር ያዘነብላሉ፡፡ ኢዮብ ዘፈኑን ለፈንጠዝያ ሳይሆን ለስነምግባር ግንባታ ሊጠቀምበት ፈልጓል፡፡ አንድ በጣም ልብ የሚበላ የሶማሌ ዘፈን አስደመጠኝ፡፡
‹‹ሶማሊኛ ትችላለህ እንዴ?>>
‹‹አዎ፣ትግርኛም አውቃለሁ!››
‹‹የት ተማርከው?>>
‹‹አስመራ፣ የወታደር ልጅ መሆኔን አትርሳ››
ከዘፈን ውጭ ምን ታደርጋለህ?
‹‹ኦን ላይን፣ጊታር እየተማርሁ ነው፡፡ ቆይ ላሳይህ››…ላፕቶፑን ለኮሰና ጥቂት አስጎበኘኝ፡፡ ከዛ ከመኪናው ስወርድ የመኪናው እጀታ ስለማይሠራ ወርዶ ከውጭ ከፈተልኝ፡፡ ኢዮብ ብዙ ብሮችን መቁጠር የሚችል ልጅ እንደሆነ መገመት ይቻላል፡፡ ይሁን እንጂ እንኳን መኪናውን የመኪናውን እጀታ ማስቀየር አልፈለገም፡፡ ምናልባት፣ዓመት በአልን ጠብቆ ልብስ የሚቀይር ብዙ ሰው ባለበት አገር ውስጥ፣መኪና መቀያየሩን እንደ ኃጢአት ቆጥሮት ይሆናል፡፡
ከጥቂት ቀናት በኋላ ልኡል የተባለ ዘፋኝ ጓደኛዬ፣ የኢዮብን በድንገት መውደቅ ሲነግረኝ ወደ ቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል ሄድኩ፡፡ ዘፋኞችና አዘጋጆች መጠበቂያው ክፍል ላይ ተደርድረው ይተክዛሉ፡፡ ዘሪቱ፣ ዳግማዊ አሊ፣ እቁባይ በርሄ፣ አጃቸውን አገጫቸው ላይ ጭነው፣ ተቀምጠዋል። የኢዮብ ባለቤት ወዲያ ወዲህ እየተንቆራጠጠች ታነባለች፡፡
ዛሬ ደግሞ ይሄው ሞቱን ሰማሁ፡፡ኢዮብ!!! በጠፈሩ ውስጥ፣ ያለግብ ከሚዞሩ ኮረቶች፣ ያለ ምክንያት ከሚበሩ ኮከቦች በቀር ምንም የለም ብዬ እንደማምን ታውቃለህ፡፡ ይሁን እንጂ ለዛሬ እንኳ፣ የኔ እምነት ከሽፎ ያንተ እምነት እውነት እንዲሆን እመኛለሁ፡፡ በምድር ለገጠመህ መራራ እጣ ሰማያዊ ካሳ (ጉማ) እንድታገኝ እመኛለሁ፡፡
(በዕውቀቱ ስዩም ከፌስ ቡክ)
ኢዮብ የስራ ባልደረባዬ ብቻ ሳይሆን የቅርብ ጓደኛዬም ነበር፡፡ ለሶስት ተከታታይ ዓመታት በፋራናይት ክለብ አብረን ሰርተናል፡፡ ይሄ ቅርብ ግንኙነት እንዲኖረን አድርጐናል፡፡
እኔና ኢዮብ የወንድማማቾች ያህል ነበር። የአስር ዓመት ጓደኝነት ከዚያ ውጭ ምን ሊሆን ይችላል? የኢዮብ ሞት ለእኔ ያልጠበቅሁትና በጣም አስደንጋጭ ነበር፡፡ ወደ ኬንያ ለህክምና ሲሄድ ተሽሎት ወደ አገሩ እንደሚመለስ ጽኑ እምነት ነበረኝ፡፡ ኢዮብ ከእንግዲህ አብሮን እንደማይኖር የሰማሁትን ዜና አሁንም ድረስ አምኖ መቀበል አዳግቶኛል፡፡ ኢዮብ የሚገርም ተሰጥኦ የታደለ ታላቅ አርቲስት ነበር፡፡ ይሄን ተሰጥኦውን ገና በቅጡ ሳይጠቀምበት ህይወቱ አለፈ፡፡ ብዙ አስደናቂ ችሎታዎቹን ለማየት በምንጠብቅበት ሰዓት ነው ሞት የቀደመው፡፡ አሁን ምን ማለት አይቻልም - እግዚአብሔር ነፍሱን በሰላም እንዲያሳርፍለት ከመፀለይ በቀር፡፡
(ድምፃዊ ሸዋንዳኝ ኃይሉ)
ይሄንን ባለተሰጥኦ ድምፃዊ ለማወቅና ለመተዋወቅ የቻልኩት አንድ ግሩም ወዳጄ ሥራውን በዳላስ፣ ቴክሳስ ሲያስተዋውቅለትና በመስከረም ወር 1997 ዓ.ም ለኮንሰርት ባመጣው ጊዜ ነበር፡፡ ኢዮብ ያኔ “እንደ ቃል” የተሰኘው አዲሱ አልበሙ ወጥቶ ስለነበር ዝናው መናኘት ጀምሯል፡፡ “ኢትዮ - ሬጌ” የተባለ አዲስ የሙዚቃ ዘይቤ ለኢትዮጵያ በተለይ ለዳያስፖራው ያስተዋወቀ አዲስ ዘፋኝ በሚል ነበር የሚታወቀው፡፡ ከዜማው የበለጠ የዘፈን ግጥሞቹ ማራኪ ነበሩ፡፡ ፍቅርን፣ መከባበርንና ትሁትነትን በዘፈኖቹ ሰብኳል፡፡ ኢዮብን በሞት ብናጣውም ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ባበረከተው ታላቅ አስተዋጽኦና በትሁት ባህርይው ዘላለም ሲታወስ ይኖራል፡፡
ዳኒ (ከዋሺንግተን ዲሲ)
ከሁለት ዓመት በፊት ኢዮብ በኒውዮርክ ያቀረበውን ኮንሰርት የመታደም ዕድል አግኝቼ ነበር። ገና በመጀመሪያውና ብቸኛ በሆነ አልበሙ ዝነኛ ለመሆን የበቃ አርቲስት ነው፡፡ ያለጊዜው ህይወቱ ማለፉ በጣም ያሳዝናል፡፡
ቢኒያም ጌታቸው (ከአሜሪካ)
የቅርብ ጓደኛው አልነበርኩም፡፡ እኔን ጨምሮ በአብዛኛው ሰው ዘንድ ይወደድ እንደነበር ግን አውቃለሁ፡፡ ኢትዮጵያ ተወዳጅ የነበረ ወጣት የሬጌ አቀንቃኝ አጥታለች፡፡ እግዚአብሔር ነፍሱን በመንግስተ ሰማያት ያኑርለት፡፡ ለቤተሰቡ መጽናናትን እመኛለሁ፡፡
ለማ ገብረማርያም (ከኢትዮጵያ)
ልብን የሚያላውስ ዘፋኝ ነበር፡፡ አዲስ አበባ እያለሁ ኮንሰርቶቹንና በምሽት ክለብ የሚያቀርባቸውን ሥራዎች ታድሜያለሁ፡፡ በተለይ በክለብ H20 እና በፋራናይት በሚያስገርም ድምፁ መድረኩን የቀወጠባቸውን ሌሊቶች ፈጽሞ አልረሳቸውም፡፡ የእሱ ሞት በተለይ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ትልቅ እጦት ነው፡፡ ሁላችንም አዲሱን አልበሙን እንጂ ሞቱን አልጠበቅንም ነበር፡፡ በጣም አስደንጋጭ ዜና ነው፡፡
አለማየሁ ጨቡዴ (ከኩዌት)
በአዲስ አበባ ኮንሰርቶቹን ተከታትያለሁ፡፡ በምሽት ክበቦች ሲዘፍን ታድሜያለሁ፡፡ ዘፈኖቹን በመኪና ውስጥ፣ እቤቴና ቢሮዬ እሰማቸዋለሁ። በዘፈኖቹ ተለክፌ ነበር ማለት እችላለሁ፡፡ ጂም አብረን ስንሰራ ከስፖርት በኋላ ስቲም ውስጥ እናወራለን፡፡ በጣም አሪፍ ሰው ነበር - ለጨዋታና ለጓደኝነት የሚመች፡፡ ሁላችንም ነን ያጣነው፡፡ የእሱ ሞት ለሁላችንም ትልቅ ጉዳት ነው፡፡
ብሩክ ኢትዮ (አዲስ አበባ)
አሁንም ድረስ ከድንጋጤ አልወጣሁም፡፡ እኔና ኢዮብ የፌስቡክ ጓደኛ የሆንነው ሙዚቃውን ከሰማሁ በኋላ ነው፡፡ የዓለም ተጓዦች የሆኑ ሰዎች ሲዲውን ይዘውት ስለነበር ከእነሱ ተውሼ ነው ያደመጥኩት፡፡
በቅርቡ ካሊፎርኒያ ለኮንሰርት በመጣ ጊዜ “All night pressure” የተባለው የእኔ ባንድ እንዲያጅበው ተስማምተን ነበር፡፡ እንዳለመታደል ሆኖ አልተሳካም፡፡ የሁለተኛ አልበም ቀረፃችንን ለመጨረስ ውጥረት ውስጥ ነበርን፡፡
ከኢዮብ ጋር ባወራንባቸው ጥቂት ጊዜያት ሃቀኛ ነፍስ እንደነበረውና ሲበዛ ደግ መሆኑን ለመገመት አልቸገረኝም፡፡ የግጥሞቹ ትርጉም ባይገባኝም ድምፁና አዘፋፈኑ ውብና አይረሴ ነበር፡፡ ሙዚቃ ክልልና ድንበር ተሻጋሪ ለመሆኑ ይሄም ተጨማሪ አብነት ነው፡፡ በዚህ ሰዓት በጣም አዝኛለሁ፡፡ ለባለቤቱና ቤተሰቦቹ መልካሙን ሁሉ እመኛለሁ። በዚህ የሀዘን ጊዜ በፀሎት ከጐናችሁ መሆኔን ለመግለፅ እፈልጋለሁ፡፡
ክሪስ ኤሊስ (ኦሬንጅ ካንቲ፣ ዩኤስኤ)

==============
ድምጻዊ እዮብ መኮንን ዘውዴ ከአባቱ ከአቶ መኮንን ዘውዴ ይመኑ እና ከእናቱ ወ/ሮ አማረች ተፈራ የምሩ ጥቅምት 12 ቀን 1967 ዓ.ም በጭናቅሰን ገብርኤል ጅጅጋ ከተማ ተወለደ፡፡ እድሜው ለትምህርት ሲደርስ የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በጅጅጋ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፤ከፊል የሁለተኛ ደርጃ ትምህርቱን ደግሞ ከወላጅ አባቱ ጋር ወደ አስመራ በመሄድ የተከታተለ ሲሆን፤ቀሪውን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ ወደ ጅጅጋ በመመለስ ተምሯል፡፡ በ1991 ዓ.ም. በአጋጣሚ ወደ አዲስ አበባ የሚያመጡ ፈቃደኛ ሰዎች በማግኘቱ እራሱን ያስተዳድርበት የነበረውን የፎቶግራፍ አንሺነት ሥራን ትቶ፣ በ24 ዓመቱ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ካዛንቺስ አካባቢ በሚገኘው የያኔው ፋልከን ክለብ ድምጻዊነቱን “ሀ” ብሎ ጀመረ።
ከ1991 ዓ.ም. ጀምሮ አልበሙን እስካወጣበት 2000 ዓ.ም ድረስ የሌሎች ድምጻውያንን ሥራዎች፣በዋነኝነት የአሊ ቢራን እና የቦብማርሊን ዘፈኖችን ሲያቀነቅን የቆየ ሲሆን በነዚህ ጊዜያት ከኢትዮጵያ ውጭ ወደ ዱባይም በመመላለስ በድምጻዊነቱ ሰርቷል፡፡ በጥቅምት 2000 ዓ.ም በአብዛኛው በሬጌ ስልት የተዘጋጀው “እንደቃል” የተሰኘው የመጀመሪያ አልበሙ ከተለቀቀ አጭር ጊዜ በኋላ፣ በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትን በማትረፍ እስካሁን ድረስ በከፍተኛ መጠን በመደመጥ ላይ ይገኛል፡፡ በአዲስ ጣዕም የመጣው “እንደቃል” አልበም በኢትዮጵያ ውስጥ የሬጌ ሙዚቃ ይበልጥ ይወደድ ዘንድ ከፍተኛ ተፅዕኖ ፈጥሯል።
ከዚህ አልበሙ በኋላ በሀገር ውስጥ እና ከሃገር ውጪ በአውሮፓ እና በአሜሪካ የሙዚቃ ዝግጅቶችን እያቀረበ ቆይቷል፡፡ በአዲስ አበባ የተለያዩ የሙዚቃ ቦታዎች ላይም ለረጅም ጊዜያት በቋሚነት የራሱን ዘፈኖች ለአድናቂዎቹ በመድረክ ሲያቀርብ ነበር፡፡ ሁለተኛ አልበሙንም በመሥራት ላይ የነበረ ሲሆን በድንገት እስኪታመም ድረስ ሙሉ ትኩረቱ በዚሁ ሥራው ላይ ነበር፡፡ ድምጻዊ እዮብ መኮንን ነሐሴ 7 ቀን 2005 ዓ.ም በድንገተኛ የስትሮክ ህመም መኖሪያ ቤቱ ደጃፍ ላይ የወደቀ ሲሆን፤ህመሙ ጠንቶ እራሱን ሳያውቅ በቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል የህክምና ክትትል ሲደረግለት ቆይቶ በወዳጅ ዘመዶቹ ርብርብ ለተጨማሪ ህክምና ወደ ናይሮቢ ኬንያ ሄዶ፣ በአጋካን ሆስፒታል ሕይወቱን ለማትረፍ ጥረት ቢደረግም በታመመ በአምስተኛ ቀኑ ነሐሴ 12 ቀን 2005 ዓ.ም. ምሽት በ38 ዓመቱ ሕይወቱ አልፏል፡፡
ድምጻዊ እዮብ መኮንን ባለትዳር እና የአንድ ልጅ አባት ነበር። የድምጻዊ እዮብ መኮንን የቀብር ስነ-ስርዓት ባለፈው ረቡዕ ነሐሴ 15 ቀን 2005 ዓ.ም ቤተሰቦቹ፣ወዳጅ ዘመዶቹ እና አድናቂዎቹ በተገኙበት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።

ኢ.ኤል ጄምስ ትባላለች፡፡ ፎርብስ መጽሔት ባወጣው የደራሲዎች አመታዊ ሽያጭ ዝርዝር አንደኛ ሆናለች - “50 ሼድስ ኦፍ ግሬይ” በተሰኘ መፅሃፏ፡፡ ከዚ መፅሃፍዋ ያገኘችው የገንዘብ መጠን 95 ሚሊዮን ዶላር ነው፡፡ መጽሐፉ በሦስት ተከታታይ ክፍል (Trilogy) የሚተረክ ሲሆን በስምንት ወር ውስጥ ሰባ ሚሊዮን ኮፒ ተሸጧል፡፡ መጽሐፏን ወደ ፊልም ለመቀየር በሲኒማ ሰሪዎች ተጠይቃ በመስማማቷ ተጨማሪ አምስት ሚሊዮን ብር ትርፏ ላይ ታክሎላታል፡፡ በ2014 ፊልሙ ሲኒማ ቤቶችን ያናውጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ከዚህች ሴት ደራሲ (ኢ.ኤል ጄምስ) ድንገተኛ ስኬት በፊት ከፍተኛ ሻጭ የነበረው ጄምስ ፓተርሰን ነበር፡፡ ዘንድሮ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል፡፡ ሴቷ ደራሲ በአራት ሚሊዮን ብር በልጣ አስከትላዋለች፡፡ ለአራት ተከታታይ አመታት የያዘውን ደረጃም ነጥቃዋለች፡፡ ጄምስ ፓተርሰንን “አሌክስ ክሮስ” እና “ማክሲመም ራይድ” በተሰኙ ድርሰቶቹ ድፍን አለም ያውቀዋል፡፡ በአመት አምስት መጽሐፍት ጽፎ (አምርቶ) ለማሳተም በመብቃቱ ይጠቀሳል፡፡ እሱን በመከተል ሶስተኛ ደረጃ ላይ ያለችው ሱዛን ኮሊንስ ናት፡፡ 55 ሚሊዮን ዶላር ትርፍ ከመጽሐፏ ሽያጭ አግኝታለች፡፡ መጽሐፏ “ዘ ሀንገር ጌምስ” ይሰኛል፡፡ ወደ ፊልምም ተቀይሯል፡፡ በዚሁ አመት የ”ሀንገር ጌምስ” ተከታይ የሆነው ፊልም “ዘ ሀንገር ጌምስ ካቺንግ ፋየር” የሲኒማን አለም እንደሚነቀንቅ ይጠበቃል፡፡