Administrator
በአፍሪካ ከአንድ በላይ ዋና ከተሞች ያሏቸው አገሮች
1. ደቡብ አፍሪካ (ሶስት ዋና ከተሞች)
ፕሪቶሪያ : የመንግሥት ሥራዎች እና ሚኒስቴሮች የሚሠሩበት የአስተዳደር ከተማ ናት።
ኬፕ ታውን: ፓርላማው የሚገኝበት እና ሕጎች የሚወጡበት የሕግ አውጪ ከተማ ናት።
ብሉምፎንቴን : የፍትህ ተቋማት እና ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሚገኙበት ከተማ ናት።
2. ኢስዋቲኒ (ሁለት ዋና ከተሞች)
ምባባኔ : የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የሚገኙበት ዋና ከተማ ናት።
ሎባንባ : ፓርላማው እና የንጉሣዊው ቤተሰብ መኖሪያ የሚገኙበት ከተማ ናት።
3. ቤኒን (ሁለት ዋና ከተሞች)
ፖርቶ ኖቮ : በሕገ-መንግሥቱ መሠረት ይፋዊዋ ዋና ከተማ እና ፓርላማው የሚገኝበት ቦታ ነው።
ኮቶኑ : አብዛኛዎቹ ሚኒስቴሮች፣ የንግድ ሥራዎች እና ኤምባሲዎች የሚገኙበት የሐገሪቱ የኢኮኖሚ ማዕከል ነው።
4. ኮት ዲቯር (ሁለት ዋና ከተሞች)
ያሙሶክሮ፣ በሕግ የተሰየመች ይፋዊ እና የፖለቲካ ዋና ከተማ ናት።
አቢጃን : አብዛኛዎቹ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች፣ የንግድ ድርጅቶች እና ኤምባሲዎች የሚገኙባት ዋና የኢኮኖሚ ከተማ ናት።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas
ናይጄሪያ በአንድ ዓመት ውስጥ 900 አዳዲስ ሚሊየነሮችን አፈራች
የአፍሪካ የሀብት ሪፖርት 2026 እንደሚያሳየው፤ ናይጄሪያ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ብቻ 900 የዶላር ሚሊየነሮችን ማፍራት ችላለች። ከሰኔ 2025 እስከ ሰኔ 2026 ባለው ጊዜ ውስጥ ከ1 ሚሊዮን ዶላር በላይ ሀብት ያላቸው ዜጎቿ ቁጥር ከ7,200 ወደ 8,100 አድጓል። ይህ አስደናቂ ለውጥ ከ2021 ወዲህ አገሪቱ ያስመዘገበችው የመጀመሪያው ትልቅ ዓመታዊ የሀብት ዕድገት ሆኗል።
ይህ አዲስ ስኬት የተመዘገበው በጠንካራው የናይራ ምንዛሬ፣ በአዳዲስ ቢዝነሶች ዕድገት እና በንብረት ዋጋ ማሻቀብ አማካኝነት ነው። ከዚህ ቀደም በገንዘብ አቅም መዳከም ምክንያት የደረሰባትን የኢኮኖሚ ኪሳራ መቀልበስ የቻለችው ናይጄሪያ፤ አሁን ላይ 8,100 የዶላር ሚሊየነሮችን በማፍራት ከአፍሪካ አራተኛዋ ትልቁ የሀብት ገበያ መሆን ችላለች።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas
ከህዳሴ ግድብ የሚመነጨው ሀይል የኢትዮጵያን ግማሽ የኤሌክትሪክ ፍላጎት ማሟላት ጀመረ
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በሙሉ አቅሙ 5 ሺህ 150 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ሀገሪቱን ከቀድሞው በበለጠ እየደገፈ ይገኛል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንዳስታወቀው፣ እየተጠናቀቀ ባለው የ2018 በጀት ዓመት ከተመረተው አጠቃላይ 35 ሺህ 671 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ውስጥ፣ ግማሽ ያህሉ ወይም 18 ሺህ 360 ጊጋ ዋት ሰዓት ከህዳሴው ግድብ ብቻ የተመረተ ነው።
ግድቡ በቂ ውሃ በመያዙ እና ተርባይኖቹ ሙሉ አቅማቸውን በመጠቀማቸው የኃይል ምርቱ ከአምናው በ23 በመቶ አድጓል። በዚህም ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ የኃይል ሽያጭ የተገኘው ገቢ ከቀድሞው 75 ቢሊዮን ብር ወደ 121 ቢሊዮን ብር ከፍ ማለቱ ተነግሯል።
ኢትዮጵያ እና ጆርዳን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስና በዲጂታል ሽግግር በጋራ ለመስራት ተስማሙ
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን የጎበኙት በአፍሪካ ኅብረት የጆርዳን ቋሚ መልዕክተኛ እና አምባሳደር አምጃድ አል ሞውማኒ፤ ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂው ዘርፍ እያስመዘገበችው ያለው እድገት አበረታች መሆኑን ገለጹ። የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) አምባሳደሩን አቀብለው አነጋግረዋል፤ እንዲሁም ተቋሙ አገር አቀፍ የቴክኖሎጂ ልማትን ለማፋጠን የሚያከናውናቸውን ሰፊ ሥራዎች አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
አምባሳደሩ ጆርዳን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ወዳጅነት ይበልጥ በማጠናከር በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ በአቅም ግንባታ እና በልምድ ልውውጥ ዘርፎች የሁለቱን አገራት ትብብር አጠናክሮ ለመቀጠል ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት አረጋግጠዋል።
ከ20 ሺህ በላይ ዜጎች የቤት ባለቤት ሊሆኑ ነው
የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ህጋዊ መሠረት ያሟሉ 901 የቤት ህብረት ስራ ማህበራት አባላት የብሎክ እጣ ማውጣት መርሐ-ግብር ማካሄድ ጀመረ። በአራት ሳይቶች (ወረብ፣ አዲስ ዓለም፣ መኮድ እና ሰልቸን) በ1045 ሄክታር መሬት ላይ በሚከናወነው በዚህ ግዙፍ ፕሮጀክት ከ19 ሺህ 6 በላይ አባላት የቤት መስሪያ ቦታ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው አስታውቀዋል።
የአማራ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ሓላፊ ሞላ መልካሙ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የለውጡ መንግስት የቤት ልማት ፖሊሲ ዘርግቶ በመሥራቱ ባለፉት አምስት ዓመታት በክልሉ ከ140 ሺህ በላይ ዜጎች በማህበር ተደራጅተው የቤት ባለቤት መሆናቸውን ገልጸዋል። ከተማ አስተዳደሩ ባህርዳርን ለኑሮ ምቹ ለማድረግና የዜጎችን መሠረታዊ የቤት እጥረት በዘላቂነት ለመቅረፍ መሰል ሰው ተኮር ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተረጋግጧል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas
አቶ አቤ ሳኖ ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት የዓመቱ ምርጥ “CEO” ተብለው ተሸለሙ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ በፋይናንስ ዘርፉ ባሳዩት የላቀ አመራር የዓመቱ ምርጥ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ (CEO of the Year) ሽልማትን ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት አሸንፈዋል።
ሽልማቱ የተበረከተላቸው ዓለም አቀፉ የስትራቴጂክ ጥምረት ማዕከል (ICSA) በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል ባካሄደው 29ኛው “Connected Banking Summit – Innovation & Excellence Awards 2026” መድረክ ላይ ነው። ይህ ታላቅ እውቅና አቶ አቤ የባንኩን ግዙፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና የፈጠራ ጉዞ በበላይነት ለመምራት ላበረከቱት አስተዋፅኦ የተሰጠ ነው።
ሽልማቱን ፕሬዚዳንቱን በመወከል የተቀበሉት የባንኩ ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አልሰን አሰፋ፣ እውቅናው የባንኩን ጠንካራ አመራር የሚያሳይ እና ለመላው ሰራተኞች እንዲሁም ደንበኞች የተበረከተ የጋራ ስኬት መሆኑን ገልፀዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas
የስፖርት ዘርፍ አክሳሪ ሳይሆን አትራፊ ነው - - ጥናት
ስህተት ለመንቀስ ሁሉም ፈጣን ነው...!
“ሳይንስ እና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ” ሊካሄድ ነው
ዋልያ መጻሕፍት “ሳይንስ እና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ” በሚል ርዕስ ከዘርፉ ምሁራን ጋር የሚደረግ አጓጊ የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል። በዕለቱ ታዋቂው ኢምሬተስ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ “ሳይንስ እና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ” በሚለው ርዕስ ላይ ጥልቅ ማብራሪያ የሚሰጡ ሲሆን፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር እና በናሳ ተመራማሪና የዶክትሬት ተማሪ የሆነው አቶ ተስፋዬ ማሞ መኮንን ደግሞ “ፊዚክስ በዕለት ተዕለት ሕይወታችን” በሚል ርዕስ ዙሪያ የዕውቀት ልውውጥ ያደርጋሉ።
ይህ ታላቅ የዕውቀት ማዕድ ነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ከሰዓት ከ8፡00 ጀምሮ በ4 ኪሎ ኢክላስ ሕንጻ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት አዳራሽ ይካሄዳል። ሁለቱን ታዋቂ ምሁራን በአንድ መድረክ በማግኘት አዳዲስ ሃሳቦችን ለመረዳት እና ከእለት ተእለት ሕይወት ጋር ለማገናኘት ይህንን ዕድል ይጠቀሙበት።
"ጦቢያ" በአውሮፓ ከተሞች ሥራዎቹን ሊያቀርብ ነው
በነፃ ሀሳብና በሰከነ መንፈስ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን በማድመቅ ላለፉት 14 ዓመታት የብዙዎችን ፍቅር ያተረፈው የ"ጦቢያ" መድረክ፣ በጀርመን መቀመጫውን ባደረገው "Hope for All" ግብረ ሰናይ ድርጅት አዘጋጅነት በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች አጓጊ ዝግጅቶቹን ሊያቀርብ ነው።
በገጣሚ ምስራቅ ተረፈ መስራችነት የሚመራው ይህ መድረክ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ኦገስት 9 በአምስተርዳም፣ ኦገስት 16 በኑረንበርግ፣ ኦገስት 23 ፍራንክፈርት፣ ኦገስት 30 ኮለን እንዲሁም ሴፕቴምበር 5 በሙኒክ ከተሞች ለታዳሚዎች ይደርሳል።
ይህ የኪነጥበብ ጉብኝት ከእጅግ ውብ መዝናኛ ባለፈ በትውልድ ሀገራቸው ለሚገኙ ወጣት ሴት ተማሪዎች የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ተደራሽ ለማድረግ ያለመ ትልቅ የበጎ አድራጎት ዓላማ ሰንቋል። አዘጋጆቹ በአውሮፓ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና የዝግጅቱ ታዳሚዎች እየተዝናኑ ለተቸገሩ ወገኖቻቸው እንዲደርሱ በህብረት እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።

