Administrator

Administrator

 
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 27ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ሊቨርፑል ኖቲንግሃም ፎረስትን 1 ለ 0 ሲያሸንፍ ቼልሲ ከብሬንትፎርድ ጋር 2 አቻ ተለያይቷል፡፡
 
የሊጉ መሪ ሊቨርፑል በዋንጫ ፉክክሩ ላይ ወሳኝ ሶስት ነጥብ ባገኘበት ጨዋታ ዳሪዊን ኑኔዝ ባለቀ ደቂቃ ቡድኑን አሸናፊ ማድረግ ያስቻለ ግብ አስቆጥሯል፡፡
 
በፕሪሚየር ሊጉ ምሽት 12 ሰዓት በተደረጉ ሌሎች ጨዋተዎች ቶተንሃም ክሪስታል ፓላስን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት ሲያሸንፍ፣ ኒውካስትል ዩናይትድ ዎልቭስን 3 ለ 0 ረትቷል፡፡

አንድ ታዋቂ የንጉሥ አጫዋች፤ የንጉሱ ባለሟሎች፣ መሣፍንቱና መኳንንቱ እንዲሁም ባለሌላ ማዕረግ ባለሥልጣናት በሚገኙበት፣ ከግብር በኋላ በሚካሄደው የመዝናኛ ሰዓት እንደ ሁልጊዜው ጨዋታ ያመጣል፡፡ ከመጠጡ ገፋ ተደርጎ የሚጠጣበት ሰዓት በመሆኑ ሳቁና ውካታውም ለከት የለውም፡፡ እንደልብ ይጮሃል፡፡ ከአፍ ለቀቅ ይባላል፡፡ ታዲያ ያ አጫዋች፣ በጥያቄ መልክ ነው ለዛሬ ቀልዱን ያቀረበው፡፡
አጫዋች፡- “ከዝቅተኛ መደብ ያለ ሰው ለምሳሌ ኩሊ፣ እንጨት - ፈላጭ፣ መንገድ - ጠራጊ ወዘተ ሲሰክር ምን ይባላል?” አንዱ ባለሟል ይመልሳል፡- “ጢምቢራው ዞረ! ተንጀባረረ ነዋ የሚባለው” ሁሉም ሳቀ፡፡
አጫዋች፡- “ትክክል ነው፡፡ እሺ፤ በመካከለኛው መደብ ያለ ሰው፤ ለምሳሌ ዝቅተኛ የመንግስት ሰራተኛ፣ ትናንሽ ነጋዴ፣ ወታደር ወዘተ ሲሰክር ምን ይባላል?”
አንዱ ይመልሳል፡- “ጣጥ አለ! ጢዝ አለ! ድብን አለ!” ይባላል አለ፡፡ ሁሉም ሳቁ፡፡
አጫዋቹም፡- “በትክክል ተመልሷል!” አለና ወደ ጥያቄው አመራ፡፡ “እሺ የመካከለኛው መደብ አባላት እንደ መካከለኛ ነጋዴ፣ መኮንኖች፣ የመ/ቤት የቢሮ ኃላፊዎች፣ ምሁራን ሲሰክሩስ ምን ይባላሉ?”
አንድ ትልቅ ሰው ይነሱና ይመልሳሉ፡- “ሙክክ ብሏል! እሳት ገብቶታል! እንግሊዝ ይደባልቃል!” አሉ፡፡
አጫዋቹም፡- “በትክክል ተመልሷል!” አለና ወደሚቀጥለው ጥያቄ ሄደ፡፡ “እሺ የከፍተኛው መደብ አባላት ማለትም መኳንንቱ፣ መሳፍንቱ፣ ሚኒስትሮቹ፣ ስመ-ጥሮቹ ነጋዴዎቹ ወዘተ ሲሰክሩ ምን ይባላሉ?”
ከመኳንንቱ አንዱ ተነሱና መለሱ፡- “ሞቅ ብሏቸዋል! ጨዋታ ጨዋታ ብሏቸዋል! ትንሽ ወሰድ አድርገዋል! ትንሽ መሸት አድርገው ነበር!” ይባላል አሉና ተቀመጡ፡፡ ሁሉም ሳቁ፡፡
አጫዋቹ፡- “ብራቮ! በትክክል ተመልሷል!  ወደ መጨረሻው ጥያቄ እንሄዳለን፡፡ ንጉሱ ሲሰክሩስ ምን ይባላሉ?”
ሁሉም ፀጥ አሉ፡፡ እጅ የሚያወጣ ሰው ጠፋ፡፡ “ሞክሩ! ሰዓት አላችሁ” ቢል ትንፍሽ የሚል ጠፋ፡፡ ስለዚህም አጫዋቹ፤
“እሺ፤ እኔ እራሴ እመልሰዋለሁ” አለና “ንጉሡ ሲሰክሩ ‘አልጠጡም፤ ግን ደስ ብሏቸዋል’ ነው የሚባለው” አለ፡፡ ሰው በሳቅ ሞተ፡፡
ንጉሡ ስለድፍረቱ ተናደው አጋፋሪው ፀጥታ እንዲያስከብር አዘዙ፡፡
ንጉሥ፡- “አሁን ላጠፋኸው ጥፋት የማያወላዳ ቅጣት ያስፈልግሃል!”
አጫዋች፡- “ምን አጠፋሁ ንጉሥ ሆይ?”
ንጉሥ፡- “አስቀህብኛል!”
አጫዋች፡- “የሳቁት የእርስዎ ሰዎች’ኮ ናቸው፣ የተሰበሰበው ህዝብ’ኮ ነው፤ ንጉሥ ሆይ?!”
ንጉሡ የባሰውን ስለተናደዱ ግንባራቸው ላይ ያሉ ስሮቻቸው ሁሉ እንደቀንድ ቆሙ፡፡ ማንም ያልገመተው ፍርድም ፈረዱ፡፡
“1ኛ ስለ አጫዋቼ - አሁን ላጠፋኸው ጥፋት ሞት ተፈርዶብሃል፡፡ ሆኖም የምትሞትበትን መንገድ የመምረጥ እድል ሰጥቼሃለሁ!
2ኛ የሳቃችሁ ባለሟሎቼና ሹማምንቶቼ በሙሉ፤ የንብረታችሁን አንድ አራተኛ ለእኔ ገቢ ታደርጋላችሁ!
አሁን አጫዋቼ፤ የምትመርጠውን አሟሟት ተናገር” አሉ፡፡ አጫዋቹም ተነስቶ፤
“ንጉሥ ሆይ፤ እኔ የምመርጠው አሟሟት አርጅቶ መሞትን ነው!”
ንጉሡ ከት ብለው ስቀው “የመረጥከው የሞት አይነት ተፈቅዶልሃል!” አሉትና ወደ መኳንንቱና መሳፍንቱ ሲዞሩ፤ ሁሉም ደንግጠውና አኩርፈው ቆመዋል፡፡ ንጉሡም “በዚህ በአሁኑ ቀልድ ከእኔ ጋር ባለመሳቃችሁ የንብረታችሁ ሩብ ይወረሳል ብዬ ፈርጄ የነበረው ተሻሽሎ ግማሽ ንብረታችሁን እንድትሰጡኝ ፈርጃለሁ!”
ሁሉም ለጥ ብለው እጅ ነሱ - አጫዋቹም ጭምር፡፡
***
ቢስቁበት የሚቆጣ፣ ቢስቁለትም የሚቆጣ ንጉሥ፣ የበላይ ኃላፊ፣ የፖለቲካ መሪ ወይም ግለሰብ አይጣል ነው፡፡ ከእኔ ጋር ካሳቅህ ትቀጣለህ፤ በራስህ ከሳቅህም ትቀጣለህ የሚል ደግሞ የበለጠ የከፋ ነው፡፡ ከቅኝቴና ከዜማዬ ውጪ የዘፈነ ወዮለት እንደማለት ነው፡፡ እንዲህ ያለ ፍርሃት በዳመነበት አካባቢ ልባዊ አስተያየት፣ ግልፅነት፣ ሀቀኛ ግምገማ፣ እውነተኛ ሪፖርት አይኖርም፡፡ ስቆ መጠራጠር፣ አልቅሶም መጠራጠር ይበዛልና፡፡ የበላይን ፈገግታ እያዩ መሳቅ አብዛኛው ማግጠጥ ነው! ራስን መሆን ያቅታል፡፡ በየትኛዋ ደቂቃ ከወንበሬ እነሳ ይሆን እያሉ መወያየት ከምንጩ የዲሞክራሲ አካለ - ጎደሎ ነው! ፍርሃት፣ ቂም፣ ተንኮል፣ ሤራ፣ አስቀድሞ - ፍርድ (prejudice) ባለበት ዲሞክራሲ አይኖርም፡፡ ዲሞክራሲ ከሌለ ደግሞ እውነተኛ ሰላም፣ እውነተኛ ፍትህ፣ እውነተኛ ልማት ማምጣት እጅግ ሩቅ ህልም ነው፡፡
ከንጉሡ ጋር የሚስቁ ምሁራንና ባለሟሎች፣ ከአለቃ ጋር የሚስቁ የበታች ኃላፊዎችና ምንዝሮች፡- ለጊዜው በአርጩሜነት ቢያገለግሉ እንጂ አገርን ከጥፋት፣ ኢኮኖሚን ከድቀት፣ ህዝብን ከመራቆት አያድኑም፡፡ ይልቁንም ራሳቸው በተሻለ አርጩሜ የሚቀጡበት ቀን ሊመጣ እንደሚችል ከላይ ካነበብነው የአጫዋቹ ታሪክ ለመገንዘብ አያዳግትም፡፡
 ማጫፈርና ማሟሟቅ ተስፋን አያመላክትም፡፡ መጠፋፋትን እንጂ ተደጋግፎ ማደግን አይጠቁምም፡፡ “በደህናው የማይጠቅም ሞቶ በህልም ይታያል” እንደሚባለው ካለፉ በኋላ ነበሩ ማለት ብቻ ይሆናል ትርፉ፡፡ ህዝብ ወይም ባለሟሉ ሲስቅ የሚስቅ ንጉሥ ወይም ባለስልጣን ማግኘት መታደል ነው፡፡ በእርግጥም በብዛት አያጋጥምም፡፡ አገራችን ለአቻ ሥራ አቻ ሰው (The Right Man at the Right Place) ዛሬም የተሳካላት አይመስልም፡፡ የሹም ሽር መብዛት፣ የእሥር መበርከት፣ የውይይት አለመቀጠል፣ የእቅዶች የአንድ ሰሞን ሞቅ ሞቅ ሆኖ መቅረት፣ የተወሰኑ ውሳኔዎ በቀላጤ መሻር፣ ባለሙያን አለማክበር፣ የበኩር ልጅን ምን ሰራህ አለማለት፣ የእንጀራ ልጅን የሰራውን አለማመስገን፣ ራስ ሳይጠና ጉተና ማሳደግ፣ ህዝቡን ለመለወጥ ከመጣር ይልቅ የራስን መንገድ ጥርጊያውን ማሳመር ወዘተ ሁሉ የሚያሳዩት ለአቻ ሥራ አቻ ሰው ማጣትን ነው፡፡ አለመታደልን ነው፡፡ “የምትኖር ሚስትና የሚያኖር ባል አንድ ገበያ እየዋሉ አይገኛኙም” እንደሚባለው ነው፡፡ እንዲህ ባለው ሰውና ሙያ ባልተገናኙበት አገር እበላ-ባዩ፣ አጫዋቹ፣ አንጓቹና አንጋቹ ይበዛል፡፡ በሥራ ከማገዝ ይልቅ በወሬ ማናቆር ይበረክታል፡፡ በእሾም ይሆናል ተስፋ ለራስም ለወገንም የማይበጅ የሲስቁ ልሳቅ ጥረት ይበዛል፡፡ “በጥገኝነት” እና በአድር - ባይነት “እኔ መንገዱን ላሳይ እችላለሁ” የሚሉ አብሪዎች አያሌ ይሆናሉ፡፡ ከጳጳሱ በላይ ካቶሊክ የሆኑት መንታ መንታ ይፈለፈላሉ፡፡ ይህም “ጥርስ የሌላት፣ ጥርስ ያላትን ነክሳ፣ አነካከስ ታስተምራለች” የሚለውን ተረት ያስታውሰናል፡፡ ዞሮ ዞሮ “የእናት ዓለም ጠኑ”ው ገራፊ ገብረየስ እንዳለው፤
“እድሜ ለእኔ፣ እኔ 40 ስገርፍ እያየ ከአንድ እስከ አርባ ቁጥር ተማረ!” መባሉ አይቀርምና አለመታደል ነው!
እንኳን ለ128ኛው የአድዋ ድል በዓል አደረሰን!!

Saturday, 02 March 2024 21:00

አ ድ ዋ 1 2 8

የፌደራል መንግስትና  የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ አደራዳሪዎች በተገኙበት   በቀጣይ ሳምንታት  በፕሪቶርያው ስምምነት ዙሪያ ዳግም ለውይይት ሊቀመጡ ነው ተባለ።  የካቲት 18 እና 19 ቀን 2016 ዓ.ም  የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ  መሰብሰቡንና የተለያዩ ውሳኔዎች ማሳለፉን የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ረዳኢ ሀለፎም ከትግራይ ቴሊቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ገልጸዋል። ካቢኔው ባካሄደው ስብሰባ፣ የአስተዳደሩን ስራዎች ለመስራት አስቸጋሪ የነበሩ መመሪያዎችን ማሻሻሉን ጠቁመዋል። በሁለቱ ወገኖች መካከል በፕሪቶርያ የተደረገው  ስምምነት ባለመተግበሩ ሣቢያ  የክልሉ ህዝብ ላይ የሚደርሰው መከራና ስቃይ ሊቆም አልቻለም ያሉት  የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ረዳኢ ሀለፎም፤  የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ከፌደራል መንግስቱና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በስምምነቱ አፈጻጸም ዙሪያ በተደጋጋሚ መምከሩን ገልጸዋል።
በፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ዙሪያ አደራዳሪ አካላት በተገኙበት በፌደራል መንግስትና በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር መካከል በቀጣይ ሳምንታት ውይይት እንደሚካሄድም አስታውቀዋል።
የአፍሪካ ህብረት፣ የመንግስታቱ ድርጅት፣ የአሜሪካንና የደቡብ አፍሪካ መንግስታት ተወካዮች ተሳታፊ የሚሆኑበት የፕሪቶርያውን ውል አፈጻጸም የተመለከተ ውይይት ለማካሄድ ቀጠሮ መያዙን የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ የካቲት 5 ቀን 2016 ዓ.ም ለክልሉ መገናኛ ብዙኃን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ መናገራቸው ይታወሳል።

የፒያሳ ነዋሪዎች በ3 ወራት ጊዜ ውስጥ አካባቢውን እንዲለቁ ተነግሯቸዋል

በአዲስ አበባ አስተዳደር አራዳ ክፍለ ከተማ፣ የፒያሳና አራት ኪሎ ነዋሪዎች ለልማት ከመኖሪያቸው እንደሚነሱ የክፍለ ከተማው አስተዳደር  ገልጿል።
አስተዳደሩ  በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ እንዳስታወቀው፤ ሁለቱን አካባቢዎች መልሶ በማልማትና ነዋሪዎችን በማስነሳት ዙሪያ ሰሞኑን  ከነዋሪዎች ጋር ውይይት አድርጓል። ውይይቱ፣ በንግድ የሚተዳደሩ ነዋሪዎች ንግዳቸውን በሚቀጥሉበትና ሌሎች ነዋሪዎች በመልሶ ማልማቱ ዕቅድ በሚስተናገዱበት ኹኔታ ላይ ያተኮረ ነበር ተብሏል።
ነዋሪዎችን ለልማት የማንሳቱን ሂደት የሚከታተል ከአመራሩና ከነዋሪዎች የተውጣጣ ኮሚቴም እንደተዋቀረ ተገልጧል። በተለይ የፒያሳ ነዋሪዎች በሦስት ወራት ውስጥ አካባቢውን እንዲለቁ እንደተነገራቸው ምንጮች ጠቁመዋል። ነባር ነዋሪዎቹን የማስነሣቱ ስራ በሦስት ወራት ውስጥ ተጠናቆ የግንባታ ስራው ይጀመራል ተብሏል።በተያያዘ ዜናም፣ ከቀበና እስከ አራት ኪሎ  እንዲሁም  ፒያሳ ደጎል አደባባይ ድረስ  የመንገድ ኮሪደር ግንባታ ሥራው ሠሞኑን  ተጀምሯል፡፡
 የከተማ አስተዳደሩ  ካቢኔ የካቲት 15 ቀን 2016 ዓ.ም ባካሄደው የ3ኛ ዓመት 8ኛ መደበኛ ጉባኤ፣ ግንባታቸው እንዲጀመር ውሳኔ ካስተላለፈባቸው አምስት  የከተማዋ የመንገድ ኮሪደሮች መካከል በአራዳ ክፍለ ከተማ የሚገኘውና  ከቀበና አደባባይ - አራት ኪሎ - ፒያሳ ደጎል አደባባይ ኮሪደር አንዱ ነው።
 የመንገድ ኮሪደር  ግንባታው በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገባ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የአራት ኪሎው  ባለፈው ረቡዕ  ተጀምሯል፡፡

የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ ”የሥራ መልቀቂያ አስገቡ“ በሚል የተሰራጨው መረጃ ሃሰተኛ መሆኑን የባንኩ ባለድርሻ አካላት ገለጹ፡፡

የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ቦሩ የሥራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን የሚገልጹ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች መሰራጨታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ሆኖም  መረጃው ሙሉ በሙሉ ሃሰተኛ ነው ብለዋል - ለባንኩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች፡፡

የባንኩ ፕሬዚዳንት የሥራ መልቀቂያ አስገቡ በሚል የተሰራጨው ሃሰተኛ መረጃ የባንኩን ጥቅም እንደሚጎዳ የጠቆሙት የባንኩ ባለድርሻ አካላት፤ ሃሰተኛ መረጃውን ያሰራጩ ማህበራዊ ሚዲያዎችንና ግለሰቦችን በህግ እንደሚጠይቁ አመልክተዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ  አዲሱ ገበያ ሸገር መናፈሻ አካባቢ የተገነባውና  ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ የግንባታ ወጪ  ተደርጎበታል የተባለው  ናሁሰናይ ኢንተርናሽናል ሆቴል፤ ከነገ ወዲያ  ቅዳሜ የካቲት 23 ቀን 2016 ዓ.ም ይመረቃል።

የሆቴሉ ባለቤቶች አቶ እሱባለው ናሁሰናይና  ባለቤታቸው ወ/ሮ ሒሩት ምህረቴ እንዲሁም የሆቴሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መላኩ ካሳሁን በጋራ በሰጡት መግለጫ፤ ሆቴሉ  ደረጃውን የጠበቀ፣ ምቹ ስፍራ ላይ የተገነባና ለደንበኞቹ የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት በሚያስችል መልኩ የተደራጀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሆቴሉ  46 የመኝታ ክፍሎች  ያሉት ሲሆን፤ እንግዶች ምግባቸውን እዚያው እያበሰሉ የሚመገቡበት የተሟላና የተደራጀ የገስት ሃውስ ክፍሎችንም ያካተተ ነው። አገልግሎቱንም  ከአካባቢው አንፃር ተመጣጣኝ በሆነ ዋጋ ለማቅረብ  በሚያስችል መልኩ መደራጀቱ ተጠቁሟል፡፡

የሆቴሉ ግንባታ  ሦስት ዓመታትን  እንደፈጀ የተገለፀ ሲሆን፤ ናሁሰናይ ኢንተርናሽናል ሆቴል ሙሉ በሙሉ ሥራ ሲጀምር ከ70 እስከ 100 ለሚሆኑ  ሠራተኞች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ተነግሯል፡፡

ሆቴሉ  ከነገ ወዲያ ቅዳሜ  የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት እንደሚመረቅ ተገልጿል።

በአዲስ አበባ ከተማ  አዲሱ ገበያ ሸገር መናፈሻ አካባቢ የተገነባውና  ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ የግንባታ ወጪ  ተደርጎበታል የተባለው  ናሁሰናይ ኢንተርናሽናል ሆቴል፤ ከነገ ወዲያ  ቅዳሜ የካቲት 23 ቀን 2016 ዓ.ም ይመረቃል።

የሆቴሉ ባለቤቶች አቶ እሱባለው ናሁሰናይና  ባለቤታቸው ወ/ሮ ሒሩት ምህረቴ እንዲሁም የሆቴሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መላኩ ካሳሁን በጋራ በሰጡት መግለጫ፤ ሆቴሉ  ደረጃውን የጠበቀ፣ ምቹ ስፍራ ላይ የተገነባና ለደንበኞቹ የተሟላ አገልግሎት ለመስጠት በሚያስችል መልኩ የተደራጀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሆቴሉ  46 የመኝታ ክፍሎች  ያሉት ሲሆን፤ እንግዶች ምግባቸውን እዚያው እያበሰሉ የሚመገቡበት የተሟላና የተደራጀ የገስት ሃውስ ክፍሎችንም ያካተተ ነው። አገልግሎቱንም  ከአካባቢው አንፃር ተመጣጣኝ በሆነ ዋጋ ለማቅረብ  በሚያስችል መልኩ መደራጀቱ ተጠቁሟል፡፡

የሆቴሉ ግንባታ  ሦስት ዓመታትን  እንደፈጀ የተገለፀ ሲሆን፤ ናሁሰናይ ኢንተርናሽናል ሆቴል ሙሉ በሙሉ ሥራ ሲጀምር ከ70 እስከ 100 ለሚሆኑ  ሠራተኞች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ተነግሯል፡፡

ሆቴሉ  ከነገ ወዲያ ቅዳሜ  የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት እንደሚመረቅ ተገልጿል።

•  የክ/ከተማው አመራሮች መርሃ ግብሩን አወድሰውታል

"ልምዴን ለወጣቱ" በሚል መሪ ቃል ዛሬ የካቲት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ሳኦል የኩነቶች አዘጋጅና ሌጀንድ ኢንተርናሽናል ፕሮ ቴኳንዶ፣ ከልደታ ክፍለ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር ባዘጋጁት የወጣቶች መድረክ ላይ ታዋቂው የህይወትና ስኬት አሰልጣኝና አማካሪው ዳዊት ድሪምስ ልምዱን አካፈለ።

ዳዊት ድሪምስ ከህይወት ተሞክሮውና ከንባብና ጥናቱ ልምዱን ባካፈለበት የልደታ ክፍለ ከተማ አዳራሽ፣ ወጣቶች ከአፍ እስከ ገደፉ ሞልተውት እንደነበር ተስተውሏል፡፡
   
በዛሬው መርሀ-ግብር ላይ ከዳዊት ድሪምስ ጋር ተገኝተው ልምዳቸውን እንደሚያካፍሉ ሲጠበቁ ከነበሩት ታዋቂ ግለሰቦች መካከል መንሱር ጀማል፣ ግራንድ ማስተር ሄኖክ፣ ማስተር በፍቃዱ (ኢሱ)፣ አቶ ሰኢድ፣ ዮኒ ቬጋስ እና ደራሲ መሐመድ ብርሀን ተጠቃሽ ሲሆኑ፤ በፕሮግራም መደራረብ ምክንያት መገኘት ያለመቻላቸውን ለማወቅ ተችሏል።

ለወጣቶቹ ልምድ ላከፈሉት ለዳዊት ድሪምስና ለሌሎች አካላትም ከአዘጋጆቹ ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።

የክፍለ ከተማው አመራሮችም ዝግጅቱን ላሰናዱት ሳኦል የኩነቶች አዘጋጅ እንዲሁም ልምዳቸውን ላካፈሉት ግለሰቦች ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፤ እንዲህ ዓይነቱ ወጣቱን የማነቃቃት ፕሮግራም መዘጋጀቱ ወጣቱን በስነ ልቡና ለማንቃትና ለስራ ለማነሳሳት ስለሚያግዝ በየጊዜው መዘጋጀት አለበት ብለዋል፡፡

“ትልቅ ህልም አለኝ” የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ ያበቃው ዳዊት ድሪምስ፤ “እኔ የህይወትና ስኬት ምስጢሮች ተመራማሪ፣ አማካሪና አሰልጣኝ ነኝ” ሲል ነው ራሱን የሚገልጸው፡፡

ስለ ህልሙ ሲናገርም፤ “የኔ ትልቁ ህልም ለዘመናት የተደበቁ የህይወትና ስኬት ምስጢሮችን በጥልቀት በማጥናት፣ በመጠቀምና በማስተማር ኢትዮጵያንና አፍሪካን መቀየር ነው” ይላል፡፡

በሚሰጣቸው ተከታታይ የስኬትና የሰብአዊ ግንባታ ሥልጠናዎች የበርካቶችን ህይወት እንደቀየረ የሚነገርለት ዳዊት ድሪምስ፤ በጥረታቸውና በትጋታቸው ለድል የበቁ ስኬታማ ሰዎችን እየጋበዘ ልምዳቸውን እንዲያጋሩና ሌሎችን እንዲያነቃቁ በማድረግም ይታወቃል፡፡

ዛሬ ደግሞ እርሱ በተራው በልደታ ክፍለ ከተማ ተገኝቶ ከልምዱ በማካፈል ወጣቶችን አነቃቅቷል፡፡

Page 13 of 704