Administrator

Administrator

በራሱ ስም በተሰየመው የመጀመሪያ አልበሙ የአፍሪካ ጃዝ አባት ከሆኑት  ከአንጋፋው ዶ/ር ሙላቱ አስታጥቄ ጋር በመጣመር “ዓይፈራም ጋሜ”ን ያስኮመኮመን አርቲስት ጀምበሩ ደመቀ፤ በቅርቡ “እሳቱ ሰ” የተሰኘ ሁለተኛ አልበሙን ለአድማጭ እንደሚያደርስ ተገለጸ፡፡

 ጀምበሩ በቅርቡ ከኡኖ ጋር ባቀነቀነው “ተፍ ተፍ” በተሰኘው ነጠላ ዜማው፣ ከፍተኛ ተቀባይነትን ማግኘቱ የሚታወቅ ነው፡፡  

በ21 አመቱ የመጀመርያውን አልበም በ2014 ዓ.ም ያወጣው ጀምበሩ ደመቀ፤ ወጣት የሂፕሆፕ አድናቂዎችን ልብ ለመግዛት ጊዜ አልፈጀበትም።
 
አርቲስቱ በሁለተኛው አዲስ አልበሙ  ከወጣት አቀንቃኞች ጋር የተጣመረባቸው ስራዎች የተካተቱ ሲሆን፤ ከባህር ማዶ ከኬንያው እውቅ አርቲስት ሬገን ዳንዲ እና ከትውልደ ብሩዎንዲ በዜግነት እንግሊዛዊው ሙቲ  እንዲሁም ከሀገር ውስጥ ከሌሎች ወጣት አርቲስቶች ጋር በአንድነት መሥራቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

አሚጎስ የገንዘብ'ና ብድር ህብረት ስራ ማህበር ለ4ኛ ዙር ስልሳ ዘጠኝ ዘመናዊ መኪኖችን በአሮጌ ላዳ ታክሲዎች ለማህበሩ ቆጣቢዎች'ና ብድር ተጠቃሚዎች ቀይሯል።

ይህ የገንዘብና ቁጠባ ብድር ህብረት ስራ ማህበር ላለፉት አስር ዓመታት ከሰባት ሺ በላይ አካላትን በማቀፍ እንዲሁም ለሶስት ሺ ሰዎች የብድር አገልግሎት በመስጠት በርካቶች ራሳቸውን'ና ቤተሰቦቻቸውን ወደ ተሻለ ህይወት እንዲቀይሩ የድርሻውን የተወጣ ማህበር ነው።

አሚጎስ በአዋጅ ቁጥር 147/91 እና ይሄንን አዋጅ ለማሻሻል በወጣ አዋጅ ቁጥር 402/96 መሰረት ተመዝግቦ የሚንቀሳቀስ ሲሆን ፤ዛሬ በጎልደን ቱሊፕ ሆቴል ስልሳ ዘጠኝ ዘመናዊ የታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ መኪኖችን የሚዲያ አካላት በተገኙበት ለተጠቃሚዎች አስረክቧል።

የአሚጎስ መስራች'ና የኮርፖሬት ሴልስ ኃላፊ የሆኑት አቶ እንዳልካቸው በሀይሉ እንደተናገሩት ከሆነ፡ድርጅታቸው አሁን ላይ ለግለሰቦች እስከ አስር ሚሊዮን ብር የሚደርስ ብድር የማቅረብ አቅም አለው ያሉ ሲሆን ፤በእስካሁኑ የስራ ቆይታቸውም አራት ቢሊዮን ብር ብድር እንዳቀረቡና አንድ ሺ አምስት መቶ መኪኖችንም በብድር መያዣቸውን አብራርተዋል።

ከስድስት ወር እስከ አስር ዓመት ድረስ ሊቆይ በሚችል የብድር አከፋፈል ስርዓት ማንኛውም ግለሰብ ሆነ ማህበራት ለመኪናም ሆነ ለቤት ግዥ የሚሆን የብድር አገልግሎት ከአንድ ወር እስከ ሶስት ወር ባለ ጊዜ ውስጥ ብድር ማግኘት ይችላል ብለዋል።

አሚጎስ ኦክሎክ ጀነራል ትሬዲንግ የሚያስመጣቸውን መኪኖች በብድር ተጠቃሚ ያደረጋቸው የታክሲ ማህበራት ፡አዲስ ምቾት ፡ሀገሬ የታክሲ ማህበር ፡ገፅታ የተሰኙ ሲሆን ሌሎች ማህበራትም የዚህ እድል ተጠቃሚ እንደሆኑ ጥሪ አቅርቧል።

ምሽት 5:00 ሰዓት ላይ በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ አስተናጋጇ ኮትዲቯር ናይጄሪያን 2 ለ 1 በማሸነፍ ዋንጫውን አንስታለች።

የኮትዲቯርን የማሸነፊያ ግቦች ፍራንክ ኬሲ እና ሴባስቲያን ሀለር  አስቆጥረዋል።ናይጄሪያን ከሽንፈት ያላዳነችውን ብቸኛ ግብ ደግሞ ዊሊያም ትሩስት ኢኮንግ አስቆጥሯል።
በዚህም ዝሆኖቹ የአፍሪካ ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ ማንሳት ችለዋል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ ጀግኖች አርበኞች፣ የኃይማኖት አባቶች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

10 አገር አቀፍ ኮንሰርቶችን ለማቅረብ ማቀዳቸውን ገልጸዋል

የሃይንከን ኢትዮጵያ ብሔራዊ ብራንድ የሆነው ዋልያ ቢራና ዝነኛው ኢትዮጵያዊ ሙዚቀኛ፣ ዜማ ደራሲና አቀናባሪ ሮፍናን ኑሪ፤ “ዘጠኝ” በተሰኘ የሙዚቃ አልበም ላይ አጋርነታቸውን በማራዘም፣ ከትላንት በስቲያ

ሐሙስ ስምምነት ፈጽመዋል፡፡
ዋልያ ቢራና ሮፍናን አጋርነታቸውን ለቀጣይ 18 ወራት እንደሚቀጥሉ የተጠቆመ ሲሆን፤ በዚህ ጊዜ ውስጥም 10 አገር አቀፍ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን በክልል ከተሞች ለማቅረብ ማቀዳቸውን ይፋ አድርገዋል -

በሰጡት መግለጫ፡፡
በቅርቡ የሚለቀቀው የሮፍናን አልበም፣ በሙዚቃና በኪነጥበብ የኢትዮጵያን ልዩ ታሪክና ባህል የሚገልጽ ነውም ተብሏል፡፡
በዋልያ ቢራና በሮፍናን መካከል “ስድስት” በተሰኘው አልበም በነበረው ጥምረት የክልል ቱሪዝምን ያደመቁ ስድስት ኮንሰርቶችን በማዘጋጀት ተመልካቾችን ከመሳብም አልፎ ብዙ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ባወጣው

መግለጫ ያስታወሰው  ዋልያ ቢራ፤ በተጨማሪም በሮፍናን ማስተርክላስ የሮፍናንን የሙዚቃ ዕውቀት መሰረት አድርጎ፣ ከአንጋፋ ባለሙያዎች ጋር በመተባበር፣ ከሙያዊ ሥነምግባር እስከ የራስን ብራንድ ፈጠራ

ድረስ ከዋልያ ጋር በመሆን ያለውን ልምድ ማካፈል እንደቻለ አመልክቷል፡፡ሙዚቀኛው ሮፍናን በ“ዘጠኝ” አልበሙ የያዛቸው “ሐራንቤ” እና “ኖር” የተሰኙ አልበሞች በአንድ ቀን እንደሚወጡ የጠቆመው የዋልያ

ቢራ መግለጫ፤ ይህም ሮፍናንን በኢትዮጵያ ሁለት አልበሞችን በአንድ ቀን ያወጣ የመጀመሪያው አርቲስት እንደሚያደርገው ጠቅሶ፣ ዋልያ ቢራም የዚህ ታሪክ አካል በመሆኑ ታላቅ ኩራት ይሰማዋል ብሏል፡፡
“ከሮፍናን ጋር ያለን ጥምረት የሙዚቃ ኮንሰርቶችን ከመሥራት ባሻገር የአገራችንን ባህል ማጎልበት፣ ዕምቅ የራስ ጥበብን ማውጣት፣ የሥራ ዕድል መፍጠርና መልካም አመለካከትንም መቅረጽ ነው፡፡” ብሏል -

ዋልያ በመግለጫው፡፡ 

ሕፃናት ጸሐፍት ዛሬ መጻሕፍቶቻቸውን በጋራ ያስመርቃሉ



በከተማችን በየዓመቱ በጉጉት የሚጠበቀው ንባብ ለሕይወት ለተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸው የሚያዘጋጀው ”ተማሪ ፌስት” የተሰኘ ትምህርታዊና አዝናኝ ፌስቲቫል ዛሬና ነገ በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል፡፡
“ተማሪ ፌስት” የተለያዩ ገፅታ ያላቸው ፕሮግራሞች ተቀናጅተው በአንድ መድረክ የሚቀርቡበት የቤተሰብ መርሃ ግብር ሲሆን፤ ከፕሮግራሞቹም መካከል የብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ከወዲሁ በቂ የሥነ-ልቦና ዝግጅት

እንዲኖራቸው የሚያግዝ ገለፃ በመስኩ ባለሙያዎች እንዲሰጣቸው ማድረግ ነው፡፡  
ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ለሚማሩ ተማሪዎችም “ልዩ ተሰጥኦ ያሸልማል” በሚል መሪ ቃል ነፃ የትምህርት ዕድልና የተለያዩ ሽልማቶች የሚያስገኙ የተሰጥኦ ማሳያ ልዩ መድረክ እንደሚጠብቃቸው ለማወቅ

ተችሏል፡፡
በተመሳሳይ በዚህ ዛሬ በሚከፈተው የተማሪዎች ፌስቲቫል ላይ ሰባት ሕፃናት ያዘጋጇቸውን ሰባት መጻሕፍት በጋራ እንደሚያስመርቁ ተጠቁሟል፡፡
ሰባቱ ሕፃናት ጸሐፍት የ“ማርካን እና ሪማስ” ደራሲ የ7 ዓመቷ የማርያም ብሩክ፣ የ“ሁለቱ ጓደኛሞች እና ቤተሰብ” ታሪክ ደራሲ የ10 ዓመቷ አሜን ልዑልሰገድ፣ የ“ቅቤ እና ቋንጣ” ደራሲ የ10 ዓመቷ

ሔመን ብሩክ፣ የ“ሁለቱ” መጽሐፍ ደራሲ የ11 ዓመቱ ቢኒያም መለሰ፣ የ“እርሳስ እና እስኪርብቶ” ደራሲ የ12 ዓመቱ ዮናታን ልዑልሰገድ፣ የ“ሳራ እና ቢታንያ” ደራሲ የ 11 ዓመቷ ፈርደውስ ሡልጣን እና የ

“ላሊበላ” ደራሲ የ14 ዓመቱ ዮሴፍ መለሰ ናቸው፡፡
ዛሬ ቅዳሜና ነገ እሁድ  ከጠዋቱ 4፡00 እስከ ምሽት 1፡00 በሚቆየው ፌስቲቫል ላይ ስመጥር ምሁራንና ተወዳጅ አንባቢያን እውቀትና ልምዳቸውን ለታዳሚያን የሚያጋሩ ሲሆን፤ ከዚሁ ጎን ለጎን በርካታ

የቤተሰብ ጨዋታዎች፤ የልደት ፕሮግራሞችና ቤተሰብን ከልጆቻቸው ጋር የሚያሳትፉ ልዩ ልዩ አዝናኝ ዝግጅቶች መሰናዳታቸው ተነግሯል፡፡
ንባብ ለሕይወት ከተለያዩ አጋር ተቋማት ጋር በመተባበር በሚሊኒየም አዳራሽ ባዘጋጀው በዚህ የተማሪዎች ፌስቲቫል ላይ ቤተሰቦች በተመጣጣኝ የመግቢያ ዋጋ ጥሩ ጊዜ እንዲያሳልፉ አክብሮታዊ ግብዣውን

አቅርቧል።

የዛሬ 100 ዓመት በነጋድራስ ገብረሕይወት ባይከዳኝ በተጻፈው “መንግሥት እና የሕዝብ አስተዳደር” መጽሐፍ ላይ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነጥበባት ማዕከልና ተወዳጅ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን  

የሚያስተባብሩት ውይይት እንደሚካሔድ፣ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነጥበባት ማዕከል አስታወቀ፡፡
ዛሬ ከቀኑ 8፡00  ጉለሌ ጳውሎስ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው ማዕከል በሚደረገው ውይይት ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገዳ ጋር ቆይታ የሚኖር ሲሆን፤ ውይይቱን ዶ/ር እንዳለጌታ ከበደ እንደሚመሩት ለማወቅ ተችሏል፡፡



በሃገራችን በጃዝ ሙዚቃ ዘርፍ ከ50 ዓመታት በላይ የሚታወቀው  አርቲስት ሙላቱ አስታጥቄ (የክቡር ዶ/ር)፣ ከአድናቂዎቹ ጋር የሚገናኝበትና እራት የሚበላበት ልዩ ምሽት መዘጋጀቱ ተገለጸ፡፡
የታዋቂ ኤቨንት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሳሙኤል አበራና የጃዝ ንጉስ ሙላቱ አስታጥቄ፣ የእራት ምሽቱን አስመልክቶ ባለፈው ሳምንት  ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫው ላይ እንደተብራራው፤ አርቲስት

ሙላቱ አስታጥቄ፣ የካቲት 9 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት፣ በግዮን ሆቴል በሚገኘው አፍሪካ ጃዝ መንደር፣ ከአድናቂዎቹ ጋር ተገናኝቶ ራት እንደሚበላና ፊርማውን እንደሚያኖር ታውቋል፡፡ የፎቶግራፍ መነሳት መርሃ

ግብር እንደሚኖርም ተነግሯል፡፡ በዝግጅቱ ላይ ተጋባዥ እንግዶችና ታዋቂ የኪነጥበብ ባለሙያዎች እንዲሁም የአርቲስቱ  አድናቂዎች ይገኛሉ ተብሏል፡፡
የተለያዩ ኹነቶችን በማዘጋጀት የሚታወቀው ታዋቂ ኤቨንት፣ ከዚህ ቀደም አርቲስት ሰላም ተስፋዬን በሸራተን አዲስ ሆቴል ከአድናቂዎቿ ጋር በማገናኘት፣ ራት የመብላትና የፎቶግራፍ መነሳት መርሃ ግብር በስኬት

ማካሄዱ ተመልክቷል፡፡  
በውጭው ዓለም ይህን መሰሉ ዝነኞችን ከአድናቂዎቻቸው ጋር የማገናኘትና አይረሴ ቅጽበቶችንና አጋጣሚዎችን የመፍጠር መርሃ ግብሮች በእጅጉ የተለመዱና የሚዘወተሩ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡
የጃዝ ንጉሱ አርቲስት ሙላቱ አስታጥቄ በአገሩ ብቻ ሳይሆን፣ በውጭው ዓለም  የሙዚቃ መድረኮችም ከፍተኛ አድናቆትንና ዕውቅናን ያተረፈ አንጋፋ  የሙዚቃ ባለሙያ  ነው፡፡