Administrator

Administrator

    ከዕለታት አንድ ቀን ሚያሚ ለሚባለው ጋዜጣ፣ የቀብር ሥነስርዓት ክፍል ስልክ ተደወለ አሉ፡፡
ደዋይዋ ሴት ናት፡፡
“የአንድን ሰው የህይወት ታሪክ በመቃብሩ ላይ ፅፎ ለመቅረፅ ምን ያህል ይፈጃል?” አለች ሴትዮዋ፡፡
የጋዜጣው ሠራተኛ በትህትና፤
“ለአንድ ቃል አምስት ዶላር ያስፈልጋል እመቤት”
“ጥሩ” አለችና ሴትዮዋ ከጥቂት ጊዜ እረፍት በኋላ፤
“እርሳስ ይዘሃል?”
“አዎን እመቤት”
“ወረቀትስ ከአጠገብህ አለ?”
“አዎን እመቤት”
“እሺ እንግዲያው የምታፅፊለትን ቃል ልምረጥ”
“መልካም”
“እንግዲያው የእኔ እመቤት፤ ቦጋለ ሞቷል” ብለህ ፃፍ፡፡
“ይኸው ነው? በቃ?” አለ ፀሐፊው ባለማመን፡፡
“አዎን ይሄው ነው” አለች ሴትዮዋ
“እመቤቴ በስህተት አንድ ቁም ነገር ሳልነግርዎ ዘንግቻለሁ”
“ምንድን ነው የዘነጋኸው?”
“ከአምስት ቃላት በታች መናገር ክልክል ነው፡፡ አምስት ወይም ከአምስት በላይ መጠየቅ ነበረብዎ”
“እሺ፤ ጥቂት ደቂቃ እንዳስብ ፍቀድልኝ” ብላ ፍቃዱን ጠየቀች፡፡”
ጥቂት ደቂቃ አሰበችና
“እሺ እርሳስና ወረቀት ይዘሃል?”
“አዎን፤ እመቤት፤ ይዣለሁ!”
“እንግዲያው ፃፍ”
“እሺ እመቤት”
“እንግዲያው ቦጋለ ሞቷል - የሚሸጥ ካዲላኩ መኪናው እንዳለ አለ - አሁንም አልተሸጠም” ብለህ አክልበት አለችው፡፡
*   *   *
እንደሁኔታው ተስተካክሎ ቀዳዳዎችን መጠቀም አስተዋይነት ነው፡፡ መንገዶች ሁሉ በአንድ በኩል ብቻ ነው የሚሄዱት ብሎ ግትር አለመሆን ታላቅነት ነው!
ዕውቀት እያነሰ በመጣ ቁጥር ሐሜትና ስለሰው መተቸት እጅግ የሚዘወተር ነገር እየሆነ ይመጣል፡፡ በዚህም ሳቢያ ችግርን በመላ ከመፍታት ይልቅ ከአፍ አፍ ማዛመት ዋና ሥራ እየሆነ ይሄዳል፡፡
“በነገር በተተበተበ ማህበረሰብ ውስጥ ለብልሆች ስድቦች የጋራ ይደረጋሉ፡፡ ሐሜትንም ከሰው ሰው ይለዋወጡታል፡፡ (insults are shared and gossip is exchange) ይሄ የሆነበት ምክንያት ሐሜትን ማዛመት ከመቅለሉም የበለጠ አዝናኝና አስደሳች በመሆኑ ሲሆን፣ መቼም ቢሆን መቼ የሌሎችን ስህተት መለየትና ታርጋ መስጠት የራስን ህፀፅ ከማየት የቀለለ በመሆኑ ነው” ይሉናል ፀሐፍት፡፡
በየጊዜው ስለሚዲያዎች ክፉ ክፉው ይወሳል፡፡ ሚዲያዎች እንደአስፈሪ ጠላቶች መታየታቸው በየትኛውም ሥርዓት የሚከሰት ጉዳይ ነው፡፡ ያለነገር አይደለም፡፡ መረጃዎች ህብረተሰብን ያነቃሉ፡፡ የአስተሳሰብ ለውጥ ሊያመጡ ይችላሉ፡፡ ይህ ግን በአዎንታዊም በአሉታዊም ውጤት ሊፈረጅ ይችላል፡፡
“ፈላጭ - ቆራጭ መንግሥታት ሁነኛ ጫና በግል ሚዲያዎች ላይ ማሳረፋቸው የአጋጣሚ ጉዳይ አይደለም፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት የህዝብ ፍላጐት ብዙውን ጊዜ የሚቀሰቀሰው በድራማዊ ክስተቶችና ስማቸው በገነነ የተከበሩ ሰዎች እንዲሁም ሚዲያውን እንደራሳቸው ቤት ርስተ - ጉልት ባደረጉ ግለሰቦች ነው ይለናል - ዳንኤል ካህኔማን (Thinking, Fast and Slow)”
የአዕምሮአችንን ውሱንነት መዘንጋት የሚከሰተው እናውቃለን ብለን ባመንበት ነገር ያለን ለከት የለሽ በራስ መተማመን እና የድንቁርናችንን ሙሉ ገጽታ ለመረዳት ብቃት ማጣት እንዲሁም የምንኖርበትን ዓለም በጥርጣሬ መሞላት ልብ አለማለት ነው! በመጨረሻ የአገራችን የኢኮኖሚ ጣጣ ዛሬም መንገድም ኖሮ፣ አበባም ኖሮ፣ ባቡርም ኖሮ፤ ምን ሆነ? የሚለው ነው፡፡ ሙሰኛና ሙሰኛ ጀርባቸውን በሚተሻሹበት አገር ልማት ይኖራል ወይ? የሚለው ጥያቄ መልሱ አንድና አንድ ነው
ሹም ለሹም ይጐራረሳሉ፤
ድሃ ለድሃ ይላቀሳሉ!!
የልማት መርሀ - ግብር ሙስናን አይሽረውም እንደማለት ነው!!

“ከ100% በላይ ተጠናቋል” … ምን ማለት ነው?

    አንድ ወዳጄ ሰሞኑን ስልክ ደወለልኝና፤ “ፋብሪካው ከ100% በላይ ተጠናቋል ይባላል ወይ?” አለኝ፤ የመገረም ቅላፄ በሚያስተጋባ ድምፅ፡፡
“ምን ማለት ነው? እንዴት?” አልኩት፤ በመገረም ሳይሆን ግራ በመጋባት፡፡
“የሆነ ዜና ላይ ሰምቼው እኮ ነው … የሶላር ማምረቻ ምናምን መሰለኝ”
እኔ ከመናገሬ በፊት ሌላ አስገራሚ መረጃ አከለልኝ፡፡
“ደሞ እኮ ገና ሥራ አልጀመረም!”
“ምኑ ነው ታዲያ ከ100% በላይ ተጠናቋል የተባለው?”
ለአፍታ ያህል በጥልቅ ሀሳብ ውስጥ ሰጠምኩ፡፡
“ግን የት ነው የሰማኸው…. ከየትኛው ሚዲያ?” ከጥልቅ ሃሳብ ውስጥ መንጥቆ ያወጣኝ ከአንደበቴ ያፈተለከው የራሴ ጥያቄ ነበር፡፡ ወዳጄ መለሰልኝ፡፡
“ከመንግስት ሚዲያ ነው … ኢዜአ ወይም ኤፍ ኤም …” (ያው የመንግስት ሚዲያ የመንግስት ነው ብሎ መለሰኝ!)
እኔ የምላችሁ ግን …  “ፋብሪካው ከ100% በላይ ተጠናቋል” ሲባል… እውነት ምን ማለት ነው? ኢህአዴግ ስንት በታማበት የግንቦቱ ምርጫ እንኳን ከ100 ፐርሰንት በላይ ውጤት አምጥቷል አልተባለም! (ቦርዱማ 100% የተባለውንም አስተባብሏል!)
አሁን እኔ ለማወቅ የጓጓሁት ምን መሰላችሁ? ፋብሪካ ወይም ኮሌጅ አሊያም ሆስፒታል… ከ100% በላይ ተጠናቋል ሲባል… ምን እንደሚመስል ነው፡፡
እውነቴን እኮ ነው የምላችሁ … ከ100% በላይ የተጠናቀቀ ምንም ነገር ገጥሞኝ አያውቅም፡፡ ቆይ ግን? በምርጫስ ቢሆን … እገሌ ፓርቲ ከ100% በላይ በሆነ ድምፅ (ከየት መጥቶ?) አሸነፈ ይባላል እንዴ? (እዚህም ባይሆን እነ ሰሜን ኮሪጠ አካባቢ!) እኔ እንግዲህ ከወዳጄ መረጃ የተረዳሁት ምን መሰላችሁ? ከ100% በላይ ተጠናቋል ከተባለ፣ (ጦቢያ ምድር ማለቴ ነው!) “ሥራ አልጀመረም” ማለት ነው፡፡ (በምን ቋንቋ እንዳትሉኝ!)
መቼም ይሄን ዜና ያጠናቀረው ጋዜጠኛ፣ ቢያንስ “ቅጥ አምባሩ የጠፋ ዘገባ” በሚል ዘርፍ ዕውቅና ሊሰጠው ይገባል፡፡ ለነገሩ እንዲህ አይነት ልማታዊ ጋዜጠኞች በሽበሽ ናቸው፡፡ ለምሳሌ የEBC ጋዜጠኞች፤ የመንግስትን የልማት ስራዎች ወይም ስኬቶች ያለ ቅጥ በማጋነን፣ በመለጠጥና በማስፋት … ማንም የሚያህላቸው እንደሌለ በአስር ጣቴ ልፈርምላችሁ እችላለሁ፡፡ (ኧረ ኢህአዴግም ይፈርምላቸዋል!) እኔ የምለው ግን… “የግነት ጋዜጠኝነት” የሚባል ኮርስ አለ እንዴ? የኢህአዴግ ካድሬዎች እንዲህ ያለውን የ“ልማታዊ ጋዜጠኞች” ግነት፣ ለልማት ካላቸው ውስጣዊ መነሳሳትና መቆርቆር የመነጨ ነው … በሚል ሊገመግሙት ይችላሉ፡፡ ግምገማቸው ትክክል ነው … አይደለም የሚለውን ለመወሰን ግን አስቸጋሪ ነው፡፡ (“ውስጣዊ መነሳሳት” እና “መቆርቆር” የሚሉት ሃሳቦች መለኪያቸው ምንድን ነው?)
በነገራችን ላይ በየዓመቱ መስቀል ሲመጣ ትዝ የሚለኝ ... EBC ለበዓሉ ከመጡ የውጭ ቱሪስቶች ጋር የሚያደርገው ኢንተርቪውና ከዚያ ውስጥ የሚሰራው ግነት የበዛበት ዜና ነው፡፡ ይሄ እንኳን ዓላማው የአገር ገፅ ግንባታ በመሆኑ ችግር የለውም፡፡ ግን እኮ ዓላማው እንደተባለው ከሆነ፣ መቅረብ ያለበት ለኛ ሳይሆን ለውጭ ሰዎች ወይም ለኢትዮጵያ ዳያስፖራዎች ነበር፡፡ (እኛማ አረረም መረረም እየኖርነው ነው!)
ወደ “ልማታዊነት” ጉዳይ ልመልሳችሁ፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በየሚዲያው ተከታትላችሁልኝ ከሆነ … ከመንግስት ባለስልጣናት እስከ ወረዳ አስተዳደር፣ ከከፍተኛ ባለሀብት እስከ ጥቃቅንና አነስተኛ ነጋዴዎች … ወዘተ ድረስ ምንም ሲናገሩ “… ልማታዊነት” የምትለዋን ቃል በግድ መደንገር አለባችሁ የተባሉ ይመስላሉ፡፡ “ልማታዊነት” ቃሉን ደጋግሞ በመጥራት ብቻ የሚመጣ ከመሰላቸው ቀለጡ፡፡ (አስማት እኮ አይደለም!)
እውነቱን ለመናገር ይሄ አካሄድ ግን ጤናማ አይደለም፡፡ ልማታዊ የመንግስት አመራሮችንም ሆነ ልማታዊ ባለሀብቶችን ፈፅሞ አይፈጥርልንም (ልማታዊ ደስኳሪዎችን እንጂ!)
ከዚያ ዘለል ካለም እንደ EBC ጋዜጠኞች ያሉ “የልማት ተቆርቋሪዎችን” ይፈጥርልን ይሆናል፡፡ ችግሩ ግን በአሁኑ ዘመን ጦቢያ የሚያስፈልጋት … በተግባር የሚሰራላት እንጂ የሚደሰኩርላት አሊያም የሚቆረቆርላት አይደለም፡፡ ልማታዊ ለመሆን ካድሬ መሆን አያስፈልግም (ለነገሩ ካድሬ ልማታዊ ሆኖ አያውቅም!) ልማታዊነት እኮ በተሰማራንበት ዘርፍ ውጤታማ ስራ ማከናወን ነው፡፡ ኪሳራ ሳይሆን ትርፍ ማስመዝገብ፡፡ ከመንግስትም ሆነ ከህዝብ የተሰጠንን ኃላፊነት በብቃት መወጣት ነው - ልማታዊነት!!
የተሰጣቸውን ትልቅ ኃላፊነት ሳይወጡ ቀርተው፤ “ልማቱ ወደፊት እንዲገሰግስ አስበን፣ ልማቱ እንዳይደናቀፍ ሰግተን፣ ልማቱ እንዳይቋረጥ ጓጉተን … ወዘተ” ሰበብ ድርደራ አያዋጣም፡፡
እንደውም ከተቻለ ከካድሬ በቀር ሌላው የመንግስት አገልጋይና ሹመኛ ሁሉ “ልማታዊ” የሚለውን ቃል ያለቦታው እንዳይደነጉር መመሪያ ቢጤ ቢወጣ ሸጋ ነበር፡፡ (በልማታዊነት ስም ሆድ አባብቶ ኃላፊነትን መሸሽ ተለምዷል!)
እናላችሁ … ሁሉም በተሰማራበት ሙያና በተሰጠው ኃላፊነት ቢለካ ነው የሚበጀው  “ልማታዊ …” የሚለውን ቃል በየንግግሩ መሃል በመሸጎጥ፣ እርስ በርስ መሸዋወድ ይብቃን! “ልማታዊ ነኝ” ያለ ሁሉ፤ ልማታዊነቱን በስራው ፍሬ፣ በውጤቱ ያስመዝን፡፡ ያኔ “ሀቀኛው ልማታዊ” እና “ሃሳዊው ልማታዊ” በግልፅ ይለያል፡፡ (ልማታዊነትን በመደስኮር የለማ አገር አላየንም!)
 ፖለቲካዊ ወጌን ከመቋጨቴ በፊት ሰሞኑን ለተለያዩ ሚዲያዎች ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የፀረሙስና ኮሚሽነሩ አቶ ዓሊ ሱሌይማን፤ ለአንድ ጥያቄ የሰጡትን ምላሽ እስቲ እንቆዝምበት፡፡
ከጋዜጠኛ የቀረበላቸው ጥያቄ እንዲህ ይላል፡- “ፀረሙስና ኮሚሽን፤ በከፍተኛ ባለስልጣናትና ባለሀብቶች ከሚፈፀሙ ሙስናዎች ይልቅ በትንንሽ ሙስናዎች ላይ የሚያተኩረው በፍራቻ የተነሳ ነው እንዴ?”
እሳቸውም እንዲህ ሲሉ መለሱ፤ “ሰው ይፈራል ባይባልም፣ የምንፈራበትም የማንፈራበትም ጉዳይ አለ፡፡ ትልቁ ነገር ግን ፍርሃቱ የግል ጉዳይ አይደለም፡፡ ልማት እንዳይደናቀፍ በመስጋት ነው፡፡ ልማቱን ላለማደናቀፍ በማለት ትንሹን ነገር አስበን፣ ትልቁ ነገር እንዳይሰናከል የምናደርገው ነገር ሊኖር ይችላል፡፡ በተረፈ ግን በራሳችን እንዲህ ብናደርግ እንዲህ ይመጣብናል የምንለው ነገር የለም፡፡”
እንዴ… ከዚህ በላይ ምን ይምጣ?! በትልቅ ስጋት … በከባድ ፍርሃት … እንዳሉ ያስታውቃሉ እኮ (ግን ያው ለልማቱ ሲሉ ነው!) “ልማቱ እንዳይደናቀፍ…” እየተባለ በሚደረገውም በማይደረገውም የተነሳ … አገሪቷ እንዳትደናቀፍ ሰጋሁ፡፡ (እንዴት አልሰጋ?!)
እኔ የምላችሁ… ቆይ ግን ልማት ምንድን ነው? ልማትና ሙስናስ? ትላልቆቹ ሙሰኞች በህግ ሲጠየቁ እንዴት ነው ልማቱ የሚደናቀፈው? ቁንጮዎቹ ሙሰኞች ይሄን ያህል አስፈሪ ሆነዋል ማለት ነው? በቁጥርስ ስንት ይሆናሉ? በመቶኛ ሲሰሉስ? ግን ግን እንዲህ የሚያስፈሩ እስኪሆኑ ድረስ ለምን ተጠበቁ? መቼ ነው “ልማቱ እንዳይደናቀፍ …” ከሚል ስጋት የምንወጣው?
ምናልባት እንዲህ ጉዳዩን እየበታተንን ስንፈትሸው አንዳች መላ፣ አንዳች ዘዴ ብልጭ ይልልን ይሆናል፡፡
በዚህ አንገብጋቢ ጉዳይ ላይ ጭንቅ ጥብብ ለማለት፣ የግድ የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር መሆን አይጠበቅብንም፡፡ ኢትዮጵያዊ መሆን ብቻ በቂ ነው፡፡ እናም እሳቸውንም ቢሆን ከሸክሙን እናግዛቸው (ለብቻቸውማ እዳ የለባቸውም!) መልካም ደመራ! መልካም መስቀል!

Saturday, 26 September 2015 08:01

የኪነት ጥግ

(ስለፊልም ስክሪፕት)
- ከጥሩ የፊልም ፅሁፍ መጥፎ
ፊልም መስራት እችላለሁ፤
ከቀሽም የፊልም ፅሁፍ ግን አሪፍ
ፊልም መስራት አልችልም፡፡
ጆርጅ ክሉኒ
አንድን ፊልም እሰራለሁ ወይም
አልሰራም ብዬ እንድወስን
የሚያደርገኝ የፊልም ፅሁፉ
አይደለም፡፡
ዣን ሉዊስ ትሪንቲኞንት
- አሁን አሁን የታሸገበትን ፖስታ
በማየት ብቻ የፊልም ፅሁፉ
አሪፍ መሆንና አለመሆኑን ማወቅ
እችላለሁ፡፡
ፒተር ኦ‘ቱሌ
- የፊልም ፅሁፍ ከማንበቤ
በፊት ምንም አይነት ውል
አልፈራረምም፡፡ ጥሩ ከሆነ
ደግሞ የ20 ዶላርም ይሁን የ1 ሚ.
ዶላር እሰራዋለሁ፡፡
ማርቲን ፍሪማን
- ልክ እንደ ፊልም ፅሁፍ ሁሉ፣
ለራስህ የቢዝነስ ዕቅድ ሊኖርህ
ይገባል፡፡
ፕሬይቲ ዚንታ
- ፀሐፊ ነኝ አልወጣኝም፤ በፊልም
ውስጥ ግን ለረዥም ጊዜ
ቆይቻለሁ፤ እናም የፊልም ፅሁፍ
መፃፍ እችላለሁ ብዬ አስባለሁ፡፡
ቤኒቺዮ ዴልቶሮ
- ፊልም ለመስራት ከመወሰኔ
በፊት እናቴ ሁል ጊዜ የፊልም
ፅሁፉን ታነበዋለች፡፡
ቼሎ ግሬስ ሞርቴዝ
- መፅሀፍ በእጄ መያዝ እወዳለሁ፡
፡ አንድ ሰው የፊልም ፅሁፍ
ሲልክልኝ ታትሞ እንዲሰጠኝ
እጠይቃለሁ፡፡
ማርዮ ካንቶኔ
- ሊፃፍ ወይም ሊታሰብ የሚችል
ከሆነ፤ ፊልምም መሆን ይችላል፡፡
ስታንሌይ ኩብሪክ
- ከተሰሩት ማናቸውም ፊልሞች
ላይ እሰርቃለሁ፡፡
ኳንቲን ታራንቲኖ
- ዘይቤ (style) ማለት፤ ሁሉንም
ዘይቤዎች መርሳት ነው፡፡
ጄሌስ ሬናርድ
- ሁልጊዜም ፊልም ሰሪ የመሆን
ፍላጎት ነበረኝ፤ የመጀመሪያ
ፊልሜን እስክሰራ ድረስ ግን
ምስጢር አድርጌ አቆይቸዋለሁ፡
አንግሊ


    ከስድስት አመታት በላይ በጠፈር ላይ የቆየቺው ሉናር ሪኮኔሳንስ ኦርቢተር የተባለች የናሳ የጠፈር መንኮራኩር፣ ይሄን አጀብ የሚያሰኝ ዜና ይፋ አድርጋለች - ጨረቃ እያደር መጠኗ እያነሰና እየተኮማተረች መሄዷን ቀጥላለች፡፡
የጠፈር መንኮራኩሯ በተገጠመላት የረቀቀ ካሜራ ያነሳቻቸው ፎቶግራፎች፣ የጨረቃ መጠን ከዚህ በፊት ከነበረው እያነሰ መምጣቱን አመላክተዋል ሲል የዘገበው ሮይተርስ ነው፡፡
የጨረቃን ሶስት አራተኛ ክፍል መሸፈን በቻለው በዚህ ካሜራ የተነሱት ጥራት ያላቸው ፎቶግራፎች፣ በጨረቃ ላይ ከ3ሺህ በላይ ሰፋፊ ስርጉድ ስፍራዎች እንዳሉ የጠቆሙ ሲሆን ከአምስት አመታት በፊት የተነሱ ፎቶግራፎች ግን፣ በጨረቃ ላይ የነበሩት ስርጉድ ስፍራዎች 81 ብቻ እንደነበሩና የቁጥራቸው መብዛት ከጨረቃ መጠን እየቀነሰ መምጣት ጋር የተያያዘ ነው መባሉን ዘገባው አስታውቋል፡፡
የናሳ የጠፈር ተመራማሪዎች የጨረቃ መጠን እያነሰ የመጣው ከመሬት  ስበት ጋር ተያይዞ በተፈጠረ ተጽዕኖ ነው ማለታቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ በራሷ በጨረቃ ውስጥ የሚታዩ የሙቀት መጠን ለውጦችም ለመጠኗ መቀነስ አስተዋጽኦ አበርክቷል ሲሉ መናገራቸውን አክሎ ገልጧል፡፡

    ከስድስት አመታት በፊት ለተካሄደው የ2009 የኖቤል ሽልማት የአመቱ ተሸላሚዎችን የመረጠውን የተቋሙ የሰላም ኮሚቴ በጸሃፊነት የመሩት ጌር ሉንደስታድ፣የአሜሪካውን ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማን ለኖቤል የሰላም ተሸላሚነት በመምረጣቸው መጸጸታቸውን እንደገለጹ ቢቢሲ ዘገበ፡፡በወቅቱ ኮሚቴው ኦባማን ለኖቤል የሰላም ሽልማት በዕጩነት ሲመርጣቸው፣ ለዚህ ትልቅ ሽልማት የሚያበቃ ጉልህ ስራ አልሰሩም በሚል ተቃውሞ ገጥሞት እንደነበር ያስታወሱት ሉንደስታድ፣ሽልማቱ መነቃቃትን ፈጥሮላቸው ተጨባጭ ስራ ይሰራሉ ብሎ በማመኑ ኦባማን ተሸላሚ እንዳደረጋቸው ሰሞኑን ለንባብ ባበቁት የግለ ታሪክ መጽሃፋቸው ገልጸዋል፡፡ ኦባማ ግን ኮሚቴው እንደጠበቀው ለአለም ሰላም ይህ ነው የሚባል ጉልህ ተግባር አልፈጸሙም ያሉት ሉንደስታድ፣ በወቅቱ ኦባማን የኖቤል የሰላም ተሸላሚ ለማድረግ በነበራቸው ተሳትፎ መጸጸታቸውን በግልጽ ጽፈዋል፡፡ኦባማ የ2009 የዓለም የኖቤል የሰላም ተሸላሚ መሆናቸውን በሰሙበት ቅጽበት ነገሩን ለማመን መቸገራቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ብዙዎቹ የኦባማ ደጋፊዎችም የሽልማቱን ዜና የተሳሳተ ሳይሆን አይቀርም ብለው ተጠራጥረውት እንደነበር ጠቁሟል፡፡
ጌር ሉንደስታድ እ.ኤ.አ ከ1990 እስከ 2015 መጀመሪያ በኖቤል የሽልማት ድርጅት የሰላም ኮሚቴ ጸሃፊ በመሆን ማገልገላቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ ተሸላሚዎችን በመምረጡ ሂደት ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደነበራቸው ጠቁሟል፡፡ የዘንድሮው የአለም የኖቤል የሰላም ተሸላሚ ከ20 ቀናት በኋላ ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

 የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት መፈንቅለ መንግስቱን አውግዘው፣የታሰሩ ባለስልጣናት እንዲፈቱ ጠይቀዋል
   የቡርኪናፋሶ የቤተ-መንግስት ጠባቂዎች ከትናንት በስቲያ ምሽት በመዲናዋ ኡጋዱጉ ባደረጉት መፈንቅለ መንግስት፣በፕሬዚዳንት ሚሼል ካፋንዶ የሚመራውን የአገሪቱን የሽግግር መንግስት በማፍረስ፣ ጄኔራል ጊልበርት ዴንድሬን በፕሬዚዳንትነት መሾማቸውን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
የቤተመንግስቱ ጠባቂዎች ባለፈው ረቡዕ በተከናወነ የካቢኔ ስብሰባ ላይ የሽግግር መንግስቱን ፕሬዚዳንት ሚሼል ካፋንዶ እና ጠቅላይ ሚኒስትሩን አይዛክ ዚዳን በቁጥጥር ስር በማዋል ማሰራቸውንና በነጋታውም መፈንቅለ መንግስቱን ማድረጋቸውን ዘገባው ገልጧል፡፡የአገሪቱን የቴሌቪዥን ጣቢያ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ ጠባቂዎቹ በምዕራብ አፍሪካዊቷ አገር የሰዓት ዕላፊ አዋጅ በማውጣትና የአገሪቱ የየብስና የአየር ክልሎች ሙሉ ለሙሉ እንዲዘጉ በማድረግ ባከናወኑት በተኩስ የታገዘ መፈንቅለ መንግስት፣ የሽግግር መንግስቱን ጊዚያዊ መሪ ፕሬዝዳንት ሚሼል ካፋንዶን ከስልጣን አውርደዋል፡፡
አገሪቱን ለ27 አመታት ያህል የመሩት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ብሌስ ኮምፓዎሬ፤ ባለፈው አመት ባጋጠማቸው የህዝብ ተቃውሞ ስልጣናቸውን መልቀቃቸውን ተከትሎ ስልጣኑን የተረከበውና በፕሬዝዳንት ሚሼል ካፋንዶ የሚመራው የአገሪቱ የሽግግር መንግስት በመጪው ጥቅምት ወር ይከናወናል ተብሎ በሚጠበቀው የአገሪቱ ምርጫ ለሚያሸንፈው አዲስ መንግስት ስልጣኑን ለማስረከብ አቅዶ የነበረ ቢሆንም፣ መፈንቅለ መንግስቱ ተካሂዶበታል፡፡የሽግግር መንግስቱ የቀድሞው የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ብሌስ ኮምፓዎሬ ታማኞች እንደሆኑ የሚነገርላቸውን ፖለቲከኞች በመጪው ምርጫ እንዳይሳተፉ መከልከሉንና የፕሬዚዳንቱ ጠባቂ ሃይል እንዲበተን መገፋፋቱን የጠቆመው ዘገባው፣በዚህ የተቆጡ የፕሬዚዳንቱ ጠባቂዎች መፈንቅለ መንግስቱን ማካሄዳቸውን አመልክቷል፡፡ አገሪቱን በቅኝ ግዛት ታስተዳድር የነበረችዋ ፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ፍራንኮይስ ሆላንዴ በበኩላቸው፣ መፈንቅለ መንግስቱን አውግዘው በእስር ላይ የሚገኙት የሽግግር መንግስቱ ፕሬዚዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡

   ዘላኖች (አርብቶ አደር የሚል መጠሪያ ተሰጥቷቸዋል) በተፈጥሮአዊ የአኗኗር ዘይቤያቸው የተነሳ በአንድ አካባቢ ወይም ቦታ ረግተው አይቀመጡም. . .አይቆዩም፡፡ በየጊዜው ጓዛቸውን ተሸክመውና  በግመል አሸክመው መሄድ ነው-- ...መሄድ...መጓዝ....፡፡ የበረሃውን ሀሩር ሽሽት፤ ምግብና ውሃ፣ ለከብቶቻቸውም መኖ ፍለጋ .....ይሄዳሉ፣ይጓዛሉ፡፡የአዲስ አበባ ቤት ተከራዮችም እንዲሁ ናቸው፡፡ በአንድ ቤት ወይም ሰፈር አይረጉም...አይቆዩም፡፡ በየጊዜው እቃቸውን በአይሱዙና በፒክአፕ ጭነው መሄድ...ነው----መሄድ..መሄድ...ብቻ፡፡ የኑሮ ውድነቱን ሽሽት፤ ዋጋው ጣራ ያልነካ ወይም ከጣራው በላይ ያልዘለለ ቤት ፍለጋ---መጓዝ፡፡
ዘላኖች ቋሚ መንደር ወይም ቀዬ አልባ ናቸው፡፡ የአዲስ አበባ ተከራዮችም ሰፈር አልባ ናቸው፡፡ የሥነልቦና ጫና ሰለባም ይሆናሉ፡፡ አንድ ቦታ ተረጋግቶ መኖር እንደማይቻል ማሰቡ የሚፈጥረው የስነልቦና ተፅእኖ፣ በየጊዜው እቃ ማስጫን ማስወረዱ፣ አዲስ ሰፈር የመላመዱ ፈተና፣ በተለይ ደግሞ ወላጆች ልጆቻቸውን በየጊዜው ከአንዱ የሰፈር ትምህርት ቤት ወደ ሌላ ሰፈር ትምህርት ቤት በማዘዋወር የሚያዩት ፍዳ ቀላል አይደለም፡፡
የአዲስ አበባ #ዘላኖች” ፤በአኗኗራቸው ሁኔታ ምክንያት ቤት ጎረቤት፣ እድርና  ማህበር አልባም ጭምር ናቸው፡፡ እነዚህ ሁሉ የማህበራዊ ህይወት ወጎች ለተከራይ ቅንጦት ናቸው፡፡
በነገራችን ላይ የቤት ተከራዮች ዋንኛ አመታዊ ጭንቀት፣ኪራይ ይጨምር ይሆን ወይንስ አይጨምር ይሆን የሚለው ሳይሆን ስንት ይጨምር ይሆን የሚለው ነው፡፡ መጨመሩማ አይቀሬ ነው፡፡ እንደውም በነጋ በጠባው ኪራይ አለመጨመር በህግ ያስቀጣል ተብሎ የተደነገገ ነው የሚመስለው፡፡ ቤቱ ምንም ሳይለወጥ በየጊዜው ኪስን የሚያራቁት ኪራይ መቆለል፣ ለአከራዮች ሙዝ የመላጥ ያህል ቀላል ነው፡፡
ቆዳህን የላጡህ ያህል የሚሰማህ ግን አንተ ነህ - ተከራዩ. . . የአዲስ አበባው ዘላን!!
ደግሞ ለምን እንደሁ እንጃ፣ አከራዮች ሲባሉ የቤት ኪራይ መጨመሩን የሚገልፁት ወይ ጠዋት አልያም ማታ ላይ ነው፡፡ ጠዋት ወይም ማታ ላይ በር አንኳኩተው ወይም ስልክ ደውለው ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ ይሄን ያህል ጨምሩ፡፡ አለቀ በቃ፡፡ ከቻልክ ትከፍላለህ፤ ካልቻልክ ትወጣለህ፡፡ ጭማሪው ከተሰማ በኋላ ቀኑ አንዴት እንደሚያልፍ ወይም ሌሊቱ እንዴት እንደሚነጋ አስቡት፡፡ ያው በጭንቀት ይዋላል፤በጭንቀት ይነጋል፡፡
ከገቢያችሁ በላይ የሆኑ  የቤት ኪራይና መሰል የኑሮ ጉዳዮች የሚፈጥሯቸው የወጪ ቀዳዳዎች መስፋት እንዴት ናላ እንደሚያዞር ለእናንተ መንገር ለቀባሪው እንደማርዳት ነው፤ ኑሯችሁን ታውቁታላችኋ፡፡
አንዳንድ አከራይ ደሞ አለ፡፡ መጨመሩ ላይቀር ከጭማሪው ጋር የሰበብ መዓት አግተልትሎ የሚመጣ፡፡ ትንሽ እያመመኝ ስለሆነ ለህክምና ብር ያስፈልገኛል ኪራይ ጨምር፤ ጤፍ፣ ምስር፣ ዘይትና በርበሬ ተወዷል ኪራይ ጨምር፤ እንዲህ ስለሆነ ነው ኪራይ ጨምሪ፣ እንዲያ ስለሆነ ነው ኪራይ ጨምሩ....ጨምሩ...ጨምሩ......፡፡ ኤዲያ ምንድነው በተከራይ ጫንቃ ላይ መወዘፍ (ጠብቆም ላልቶም መነበብ ይችላል) እኔ የህክምና ወጪ ደረሰኞቼን ባሳይ፣ የወሩን ኪራይ ይቀንሱልኛል? ጤፍ፣ ምስር፣ ዘይትና በርበሬ የሚጨምረውስ በአከራይ ላይ ብቻ ነው? ግርም እኮ ነው የሚለው፡፡
አንድ አከራይ ነበሩኝ፡፡ ግቢያቸው ተከራይቼ እንደገባሁ ከሰጡኝ ማስጠንቀቂያዎች መካከል መብራት እያበሩ (ቴሌቪዥን እያዩ፣ እያነበቡ ወይም ስራ እየሰሩ--) ማደር፣ ቤት ውስጥ ተጨማሪ ሰው ማስገባት አይደለም እግር የሚያበዙ ሌሎች ሰዎች መመላለስ ከጀመሩ ያለምንም ማስጠንቀቂያ የቤት ኪራይ እንደሚጨምር እወቅ-----የሚሉት ይገኙባቸዋል፡፡ ማስጠንቀቂያውን ሰጥተውኝ፣ ዱሮ ጠዋት ጠዋት በሬዲዮ በምንሰማው የቡናና ሻይ ማስታወቂያ ዜማ ስልት፤
የኢኮኖሚ ዋልታ ኪራይ ኪራይ
የገቢ ምንጫችን ኪራይ ኪራይ ...
የእድገታችን ገንቢ ኪራይ ኪራይ ..... እያሉ በኪራይ ሰብሳቢነታቸው እየተኩራሩ ወደ ቤታቸው ገቡ፡፡ እኔም ማስጠንቀቂያውን በሚገባ ነበር ተግባር ላይ ያዋልኩት፡፡  ሌሊት ማንበብ ካለብኝ በሞባይል ባትሪዬ፤ ፊልምም ካየሁ በላፕቶፕ፣ ጓደኞቼም ካስፈለጉኝ፣ ሄጄ ቤታቸው ነበር የማገኛቸው፡፡
ሰውየው ኪራይ መጨመራቸው ላይቀር ሰበብ ይፈልጉ ነበርና አንድ ቀን ማታ ከስራ ስገባ ሳሎን ቤታቸው አስጠሩኝ፡፡ አየኸው!?»
ወደ 32 ኢንች ቴሌቪዥናቸው ዞር ስል፣ በቅርቡ የተመረቀ አንድ ትልቅ ህንፃ ማስታወቂያ ይተላለፋል፡፡ እሳቸው ቀጠሉ ማብራሪያቸውን፡-
«አለም አቀፉ የምጣኔ ሀብት ቀውስ በሁሉም ሀገራት ላይ ተፅእኖውን እያሳደረ ነው፡፡ ሰሞኑን ዜናው ሁሉ እሱ ነው፡፡ እውነቱን እኮ ነው፡፡... የኑሮ ወድነቱማ ሀገራችን ከገባ ቆይቷል፡፡ የሰሞኑ ደሞ ባስ ያለ ነው፡፡ አሁን በቀደም ዕለት ለልጆቼ ጫማና ልብስ ልገዛ መርካቶ ሄጄ . . . . . . »
ሰውየው ይሄን ሁሉ ለምን እንደሚነግሩኝ ቢያንስ ለጊዜው አልገባኝም ነበር፡፡ ድክም ብሎኝ ስለነበር ወሬያቸውም ከኑሮው ጋር ተዳምሮ ስልችት ስላለኝ ከልቤ አልነበረም የማዳምጣቸው፡፡ መጨረሻ ላይ ግን ያሉት ነገር የመጀመሪያውን አሰልቺ ልፍለፋቸውን ዳርዳርታ ግልፅ አደረገልኝ፡፡ በል እስኪ ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ ኪራይ ጨምር፡፡ ከገባሁ ገና 3 ወር እንኳን አልሞላኝም ብዬ ለመከራከር ባስብም የትም እንደማያደርሰኝ ስለገባኝ  እሺ ብዬ ወጣሁ፡፡
አስቡት እስኪ ኪራይ ለመጨመር ከምዕራቡ አለም የኢኮኖሚ ቀውስ እስከ መርካቶ የልጆች ልብስ ገበያ የሚደርስ ኢኮኖሚያዊ ትንታኔን ያዘለ ሰበብ፡፡
ከጨመሩ ዝም ብለው አይጨምሩም፡፡ ተከራይ እንደሁ ከመክፈል አልያም እቃውን ሸክፎ ቤት ፍለጋ ከመሰደድ ውጪ አማራጭ እንደሌለው ያውቁታል፡፡ ሀይ ባይ የለማ፡፡ ማን የሚጠይቃቸው አለ፡፡ ከሚመለከተው አካል የሚጠበቀው የአከራይ ተከራይ መመሪያ እንደሆነ የውሃ ሽታ ሆኗል፡፡ የከተማውን ነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት ችግር የሚፈታ የተባለለት የቤቶች ልማትም፣ ችግሩን ማቃለል አባይን በጭልፋ ሆኖበታል፡፡ በዚያ ላይ የኮንዶሚኒየም ቤት ገዝቶ አትርፎ መሸጡ የደራ ቢዝነስ ሆኗል፡፡
በአንድ በኩል በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ለህዝብ በእጣ ይከፋፈላሉ፣ በሌላ በኩል ደግሞ እነ አጅሬ (የከተማይቱ ሀብታም የቤት ነጋዴዎች) ወደድ ሲል ለመሸጥ አልያም በውድ ለማከራየት በርካታ ቤቶችን ከህዝቡ ላይ ይገዛሉ፡፡
ሰው ስንት አመት ሲጠብቅ የኖረውን ቤት የማግኘት እድል ሲደርሰው እልል ብሎ በመቀበል ፈንታ የሚጠበቅበትን ክፍያ ለማሟላት ጭንቀት በጭንቀት መሆን ከጀመረ ከራረመ፡፡ ኮንዶምንየም ቤት ደርሷቸው ቅድሚያ ክፍያውን ለመክፈል ስንት እናቶችና አባቶች ልመና እንደወጡ፣ እራሱ ኮንዶምንየም ቤቱ ይቁጠራቸው፡፡ ይሄን ማድረግ ባለመፍቀዳቸው ወይም እርዳታ ለምነውም ስላልተሳካላቸው የመጣላቸውን እድል በውክልና ስም ለነጋዴ የሸጡትን ደግሞ ውልና ማስረጃ ይቁጠራቸው፡፡
እነዚህ ሰዎች የመክፈል አቅም አንሷቸው የሸጡትን ቤት ነገ መልሰው በውድ ዋጋ ተከራይተው ለመኖር ይገደዳሉ፡፡ አንዱ ሰፈር ሲወደድባቸው ወደ አንዱ፣ከዚያም ወደ ሌላው እያሉ እንዲሁ እንደ ዘላን ሲንከራተቱ ይኖራሉ፡፡
አንዱ የቤት ችግር ከአንዱ ሰፈር ወደ አንዱ ሰፈር የሚያላጋው አርቲስት፤ #ለምን ልጅ አትወልድም?; ተብሎ ሲጠየቅ፤ “እኔ ሰፈር የሌለው ልጅ መውለድ አልፈልግም” አይደል ያለው፡፡ ሸጎሌ ይረገዛል፣ ኮልፌ ይወለዳል፣ ሳሪስ ያድጋል (ቤተሰቦቹ ኪራዩን መቋቋም ከቻሉ እስከ 2 አመቱ)፣ ከዚያ አሁን ባለው ሁኔታ ጭማሪውን ችሎ አንድ ሰፈር ውስጥ ከሁለት አመት በላይ መቆየት ስለማይቻል ከቤተሰቡ እቃዎች ጋር በአይሱዙ እየተጫነ የዘላን ኑሮውን ይገፋል፡፡ ይሄንን ልጅ ሰፈርህ የት ነው ብሎ መጠየቅ፣ ውጤቱ ልጁን ማወዛገብ ብቻ ነው የሚሆነው፡፡ ምን ብሎ ሊመልስ ይችላል?
እንደው ግን ለአዲስ አበባ ተከራይ የዘለቄታ መፍትሄው ምን ይሆን? አብረን የምናየው ይሆናል፡፡ እኔ ግን በቀጣዩ የአዝማሪዎች የቅብብሎሽ ግጥም ልሰናበታችሁ፡-  
ፈረንሳይ ባስጠይቅ ገባች አሉኝ አስኮ
ምን ታርግ ትልቀቅ እንጂ....
የዘንድሮ ኪራይ ያሳቅቃል እኮ
አስኮ ላይ ባስጠይቅ ገባች አሉኝ ገርጂ
መንግስትና አከራይ ለሰው እዘኑ እንጂ
ገርጂ ላይ ባስጠይቅ ሄዳለች አቡዋሬ
እዛ ይቀንሳል የሚል ሰምታ ወሬ
አቡዋሬ ባስጠይቅ ሄደች አሉ ሰሚት
ኮንዶሚኒየም ግቢ ይሻላል ብለዋት
ሰሚት ላይ ባስጠይቅ ሄዳለች ኮተቤ
እንክርቱዋን ሲያስብ ተሰበረ ልቤ
ኮተቤ ባስጠይቅ ገባች አየር ጤና
የገቢዋን እጥፍ ክራይ ከወሰደው ምን ሰላም አለና
አየር ጤና ስደርስ ሄዳለች ሰበታ
ከራቀ ቅናሽ ነው የሚል ወሬ ሰምታ
ሰበታ ባስጠይቅ ሄደች አሉኝ ገላን
መቼም ቋሚ የለው የከተማ ዘላን፡፡

የአንጋፋው ደራሲ የአበራ ለማ አዲስ ስራ የሆነው “ቅንጣት የኔዎቹ ኖቭሌቶች” አዲስ መጽሐፍ ዛሬ ከቀኑ 8፡00 -10፡30 ሰዓት በኢትዮጵያ ቤተ መፃሕፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ይመረቃል፡፡ በአግዮስ ህትመትና ጠቅላላ ንግድ ኩባንያ የታተመው መጽሐፉ በምረቃው እለት በታዋቂው ሃያሲ አብደላ ዕዝራ ዳሰሳዊ ግምገማ እንደሚቀርብበትም ለማወቅ ተችሏል፡፡

ባቡሩ ነገ ማለዳ ስራውን ይጀምራል
   በነገው ዕለት ስራ ለሚጀምረው የአዲስ አበባ የቀላል ባቡር ፕሮጀክት የሃይል አቅርቦት የማሟላት ሃላፊነቱን የወሰደው “ቻይና ኤሌክትሪክ ፓዎር ኢኩፒመንት ኤንድ ቴክኖሎጂ” የተባለው ኩባንያ የሃይል አቅርቦቱን ያልተቆራረጠና አስተማማኝ አደርጋለሁ ሲል ቃል መግባቱን ዥንዋ ዘገበ፡፡
የኩባንያው ምክትል ጄኔራል ማናጀር ቼን ዊ፤ ኩባንያው በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ አምስት ቦታዎች የገነባቸውን የቀላል ባቡሩ የኤሌክትሪክ ሃይል ማስተላለፊያ ንኡስ ጣቢያዎች ባስጎበኙበት ወቅት እንዳሉት፣ ምንም እንኳን ኩባንያው የጊዜ መጣበብና በአገር ውስጥ ገበያ የቁሳቁስ አቅርቦት እጥረት ቢያጋጥመውም ንኡስ ጣቢያዎቹን በወቅቱ ገንብቶ የጨረሰ ሲሆን፣ የባቡር ኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦቱን አስተማማኝ ለማድረግ በቻለው አቅም ሁሉ መዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡ቻይና ኤሌክትሪክ ፓዎር ኢኩፒመንት ኤንድ ቴክኖሎጂ ኩባንያ በአዲስ አበባ ያስገነባቸው የቀላል ባቡር የኤሌክትሪክ ሃይል ማስተላለፊያ ንኡስ ጣቢያዎች አምስት ሲሆኑ በቃሊቲ፣ አያት፣ ሚኒልክ፣ መስቀል አደባባይ፣ እግዚያብሄርአብ ቤተ ክርስቲያንና በጦር ሃይሎች አካባቢ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በሌላ በኩል ተሳፋሪዎች በጉዞ ወቅት እስከ 10 ኪሎ የሚመዝን እቃ ብቻ ይዘው ለመጓዝ እንደሚፈቀድላቸው የተገለፀ ሲሆን አንዳንድ በባቡሩ ላይ እንዳይጫኑ የሚከለከሉ እቃዎች እንደሚኖሩ ታውቋል፡፡
የባቡር ትራንስፖርቱ ክፍያ እስከ 4 ኪሎ ሜትር ሁለት ብር፣ እስከ 8.8 ኪሎ ሜትር 4 ብር እንዲሁም ከመነሻ እስከ መጨረሻ ፌርማታ 6 ብር ነው ተብሏል፡፡ ትኬት ሳይዙ መጓዝ ከፍተኛ ቅጣት እንዳለውም ተጠቁሟል፡፡

  መመሪያ ያልተሰጠበት የደብሩ የሚሊዮን ብሮች የበጀት ጥያቄ እንዲዘገይ አዟል
 •  የሀገረ ስብከቱን ሥራ አስኪያጅና ምክትላቸውን እያወዛገበ ነው


    የአራዳው መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደብር፣ እያሠራው የሚገኘው የሁለገብ ሕንፃ ግንባታ፣ ተደርጎለታል ባለው የዲዛይን ማሻሻያ ሳቢያ በልዩነት የሚያስፈልገው ከመቶ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪና ከባለሀብቶች ጋር በመተባበር ለማስገንባት ያቀዳቸው የሌሎች ሁለት ሕንፃዎች ግንባታና በጀት እንዲጸድቁለት ያቀረባቸው ጥያቄዎች፣ ለፓትርያርኩ ቀርበው መመሪያ ያልተሰጠባቸው በመሆናቸው “በአሉበት ሁኔታ እንዲቆዩ” የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት አዘዘ፡፡
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳደር ጉባኤ፣ በደብሩ ግንባታዎችና የበጀት ይጸደቅልኝ ጥያቄዎቹ ላይ ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር መጨረሻ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች ለአፈጻጸም ወደ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤቱ ሳይላኩለት የቆዩበት ምክንያት እንዲብራራለትም ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ከትላንት በስቲያ ለሀገረ ስብከቱ በጻፈው ደብዳቤ ጠይቋል፡፡
የደብሩ ሰበካ ጉባኤ፣ የልማት ዕቅዶቹ በሀገረ ስብከቱ በኩል እንዲጸድቁለት ባለፈው ዓመት ሚያዝያ 16 ቀን 2007 ዓ.ም. መጠየቁን ጠቅላይ ጽ/ቤቱ ባስታወሰበት ደብዳቤው፤ ዲዛይኑ ለተሻሻለው ሁለገብ ሕንፃ ማሠሪያ እንዲሁም በስተምሥራቅ የሚገኙት ሱቆች ፈርሰው በምትካቸው ባለሁለት ፎቅ ሕንፃ መሥራት ይቻል ዘንድ የብር 6 ሚሊዮን በጀት በደብሩ እንደተመደበ፣ በጥያቄው ላይ ለመወሰን ሰኔ 25 ቀን 2007 ዓ.ም. ከተሰበሰበው የሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ቃለ ጉባኤ መረዳቱን ጠቅሷል፡፡
በዕለቱ፣ በምክትል ሥራ አስኪያጁ መጋቤ ብሉይ አእመረ አሸብር በተመራው የአስተዳደር ጉባኤው ስብሰባ፣ በደብሩ የቀረበው የበጀት ይጸድቅልኝ ጥያቄ፣ “ከባድና ከሀገረ ስብከቱ አቅም በላይ” ሊሆን እንደቻለ ተጠቁሟል፡፡ ወጪው ከ61 ሚሊዮን ወደ 152 ሚሊዮን ያደገው የዲዛይን ክለሳ ጥናት፤ በገለልተኛ ባለሞያዎች ተገምግሞ፣ ውጤቱ ለጠቅላይ ቤተ ክህነቱ እንዲላክና በዚያው በኩል እንዲጸድቅ፤ የሁለት ተጨማሪ ሕንፃዎች ግንባታ ውሎችም ለአስተዳደር ጉባኤው ቀርበው እንዲታዩና የውሳኔው ቃለ ጉባኤም በምክትል ሥራ አስኪያጁ ሸኚ ደብዳቤ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እንዲላክ ከስምምነት ተደርሶበት እንደነበር ጠቅላይ ጽ/ቤቱ አውስቷል፡፡
ይኹንና ውሳኔዎቹም ኾኑ የውሳኔዎቹ ቃለ ጉባኤ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤቱ እንዳልተላከ ጠቅሶ፣ ለሦስት ወራት ሳይላክ የዘገየበት ምክንያት ከተጨባጭ ማስረጃ ጋር እንዲብራራለት የሀገረ ስብከቱን ጽ/ቤት አዟል፤ የመናገሻ ገነተ ጽጌ ደብርን ጨምሮ የ48 አድባራትን የመሬትና የገቢ ማስገኛ ተቋማት አጠቃቀምና የኪራይ አፈጻጸም ያጣራው አጥኚ ኮሚቴም፣ ጉዳዩን ተከታትሎ እንዲያስፈጽም በደብዳቤው ግልባጭ መታዘዙን ጠቅላይ ጽ/ቤቱ አስታውቋል፡፡
በቤተ ክርስቲያኒቱ የቃለ ዐዋዲ ድንጋጌ አንቀጽ 12 ንኡስ አንቀጽ 8፣ ቋሚ ንብረትንና ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቁ ጉዳዮች በሥራ ላይ ሊውሉ የሚችሉት ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ፈቃድ ሲያገኙ ብቻ ነው፡፡ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት፣ ከረዳት ሊቀ ጳጳሱ አልፎ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ልዩ ሀገረ ስብከት እንደመኾኑ፣ በአጥቢያ ሰበካ ጉባኤያቱ ለሀገረ ስብከቱ የሚቀርቡ ጥያቄዎች በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤቱ አማካይነት ለፓትርያርኩ እየቀረቡ አመራር ሲሰጥባቸው፣ ጠቅላይ ጽ/ቤቱ በመመሪያው መሠረት ማስፈጸም ይኖርበታል፡፡
በዚሁ አግባብ፣ በሀገረ ስብከቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ሰብሳቢነት የተላለፈው ውሳኔ፣ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤቱ አማካይነት ለፓትርያርኩ ቀርቦ መመሪያ እስከሚሰጥበት ድረስ የደብሩ የግንባታና የበጀት ይፅደቁልኝ ጥያቄዎች በአሉበት ሁኔታ እንዲቆዩ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ሀገረ ስብከቱን አዟል፡፡
ጠቅላይ ጽ/ቤቱ ይህን ይበል እንጂ፤ ደብሩ በጥያቄው መሠረት ግንባታውን እንዲቀጥል የሚገልጽ ነው የተባለ ደብዳቤ፤ በሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ባለፈው ዓመት መጨረሻ ለደብሩ አስተዳደር አስቀድሞ መጻፉን የሀገረ ስብከቱ ምንጮች ተናግረዋል፡፡ ዋና ሥራ አስኪያጁ የደብሩም ዋና ጸሐፊ እንደኾኑ የጠቀሱት ምንጮቹ፣ በአንድ በኩል ጥያቄ አቅራቢ በሌላ በኩል ውሳኔ ሰጪና አፅዳቂ በመኾን የፈጸሙት ተግባር የተጠያቂነት መርሆዎችንና የአስተዳደር ጉባኤውን ውሳኔ ከመፃረሩም በላይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከምክትል ሥራ አስኪያጁ ጋር እየተካረሩ ለመጡት አለመግባባቶችም አንድ መንሥኤ መኾኑን አስረድተዋል፡፡
የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደብር፣ በሕንፃዎች፣ በሱቆችና በባዶ መሬት አጠቃቀምና የኪራይ አፈጻጸም፣ የአሠራር ችግር እንዳለባቸው ከተዘረዘሩት 15 ገዳማትና አድባራት አንዱ እንደኾነ፣ በፓትርያርኩ ትእዛዝ የተሠየመው ኮሚቴ ባካሔደውና በጠቅላይ ጽ/ቤቱ አማካይነት ለቋሚ ሲኖዶስ በቀረበው ጥናታዊ ሪፖርት ተጠቅሷል፡፡
እንደ ሪፖርቱ፣ የደብሩ ሁለገብ ሕንፃ፣ የዲዛይን ማሻሻያ በሚል ወጪው ከ61 ወደ 171 ሚሊዮን ብር ያደገ ሲኾን አዲስ ተቆጣጣሪ መሐንዲስም በደብሩ ዋና ጸሐፊ ጠቋሚነት ያለጨረታ ተቀጥሯል፡፡ ሀገረ ስብከቱና ሊቀ ጳጳሱ ለአዲሱ የዲዛይን ጥናትና ከብር 110 ሚሊዮን በላይ ላሳየው የዋጋ ጭማሪ ዕውቅናና ፈቃድ ባልሰጡበት ሁኔታ ግንባታው መቀጠሉም አግባብነት እንደሌለው በሪፖርቱ ተገልጧል፡፡
ቋሚ ሲኖዶስ፣ ጥናታዊ ሪፖርቱን ሙሉ በሙሉ በመቀበል ውሳኔዎችን ማሳለፉን ጠቅላይ ጽ/ቤቱ በደብዳቤው ገልጾ÷ የመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደብርን ጨምሮ በተዘረዘሩት 15 ገዳማትና አድባራት ተፈጸመ በተባለው ኢ-ፍትሐዊ አሠራር፣ በተናጠልም ኾነ በጣምራ ተጠያቂ የሚኾኑ የአመራር አካላት ከተሰበሰቡት ማስረጃዎች ጋር በንጽጽር እንዲቀርቡለት፤ የሕንፃዎቹ፣ የሱቆቹና የባዶ መሬቶቹ የኪራይ አፈጻጸምና የመካናተ መቃብሩ አጠቃቀም የሚመሩበት መተዳደርያ ደንብ፣ የጨረታ ደንብ፣ የአከራይና ተከራይ የውል ሰነድ በማእከላዊነት በባለሞያዎች ተዘጋጅቶ እንዲቀርብ፤ ጥናቱ ባልሸፈናቸው ሌሎች ገዳማትና አድባራት ላይም እንዲቀጥል መታዘዙንም አስታውቋል፡፡