በሰለሞን ተሾመ ባዬ የተዘጋጀው “ፎክሎር ምንነቱና የጥናቱ የትኩረት አቅጣጫ” የተሰኘ መፅሃፍ የፊታችን ሐሙስ ከቀኑ 10 ሰዓት በብሄራዊ ሙዚየም እንደሚመረቅ ተገለፀ፡፡ በምረቃ ሥነ - ሥርዓቱ ላይ የተለያዩ ምሁራን የውይይት ሃሳብ የሚያቀርቡ ሲሆን ምሁራኑ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ፣ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዘሪሁን አስፋው፣ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራና አቶ እንዳለ ጌታ ከበደ እንደሆኑ ታውቋል፡፡ የመፅሀፉ ይዘት፡- የፎክሎር ፅንሰሀሳብን በሳይንሳዊ መንገድ ማብራራት፣ በአገራችን የሚገኙ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ያላቸውን ቃላዊ፣ ቁሳዊና መንፈሳዊ ባህሎችን መሰረት ያደረገ ትንተና መስጠት እና ሌሎችን ያካትታል ተብሏል፡፡ በ335 ገፆች የተዘጋጀው መፅሀፉ፤ በ120 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

ነፃነት ኪዳነማርያም የተፃፈው “የአሥመራው ታዳኝ” የተሰኘ ታሪካዊ ልብወለድ መፅሃፍ በነገው ዕለት ከጠዋቱ 3 ሰዓት ላይ መስቀል አደባባይ በሚገኘው ኢዮሐ ሲኒማ ይመረቃል፡፡ የመፅሀፉ ዋጋ 60 ብር እንደሆነ ታውቋል፡፡ ደራሲው ከዚህ ቀደም “ዋሻው” የተሰኘ ለአገሪቱ የመጀመሪያ የሆነውን የአኒሜሽን ፊቸር ፊልም ሰርቶ ለተመልካች ማቅረቡ ይታወሳል፡፡  

   በእስራኤል በዶክትሬት ዲግሪ የተመረቁ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ናቸው
    ኢትዮጵያዊው ምሁር ዶ/ር አንበሴ ተፈራ በእስራኤል የመጀመሪያው ከፍተኛ የዩኒቨርሲቲ መምህርና የፋካልቲ አባል በመሆን በቴል አቪቭ ዩኒቨርሲቲ ስራ መጀመራቸውን ጂዊሽ ኒውስ ድረገጽ ሰሞኑን ዘገበ፡፡
ዶ/ር አንበሴ በቴል አቪቭ ዩኒቨርሲቲ የእብራይስጥ ባህል ጥናት የትምህርት ክፍል የሴሜቲክ ቋንቋዎች ከፍተኛ መምህር ሆነው እያስተማሩ እንደሚገኙ የጠቆመው ዘገባው፣ ምሁሩ ከ15 አመታት በፊት የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ሲያገኙም በእስራኤል የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ እንደነበሩ አስታውሷል፡፡
በ1962 የተወለዱት ዶ/ር አንበሴ፤ የመጀመሪያና የሁለተኛ ዲግሪያቸውን በሊንጉስቲክስ በተቀበሉበት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለአምስት አመታት ያህል በመምህርነት ማገልገላቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ እየሩሳሌም ውስጥ ከሚገኘው ሂብሩ ዩኒቨርሲቲ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን መቀበላቸውንና በዩኒቨርሲቲው አማርኛ ቋንቋን ሲያስተምሩ እንደቆዩም አክሎ ገልጿል፡፡  
ዶ/ር አንበሴ፤ ሶስት መጽሃፍትንና ከ20 በላይ ጥናታዊ ጽሁፎችን ለህትመት ያበቁ ሲሆን፣ ከማስተማርና ከጥናትና ምርምር በተጨማሪም ለ13 አመታት ያህል ለእስራኤላውያን የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች አማርኛ ቋንቋን በማስተማርና በትምህርት ሚኒስቴር የአማርኛ ጥናቶች ብሄራዊ ሱፐርቫይዘር ሆነው በማገልገል እንደሚታወቁ ዘገባው ጠቁሟል፡፡

Published in ዜና
Saturday, 01 August 2015 14:06

በሚቀጥለው ቅዳሜ …

ወደ ኢትዮጵያ ጠቅልዬ ልመለስ ነው ስል በአሜሪካ ያሉ ሚዲያዎች መጥተው ነበር ቺካጐ ትሪቡን “አዲስ አበባ ዎን፤ ቺካጐ ሎስት” ብሎ ፅፏል በኢትዮጵያ በደቡብ በሸዋ፣ በጐንደር ገጠሮች 30 ት/ቤቶች አሠርቷል
በአያት አካባቢ ሪል ኢስቴት እየሠራ ነው “አይዞን” የተባለ 12 ዘፈን የያዘ አዲስ አልበሙን በቅርቡ ያወጣል
ጋንግስተሮች በ30 ሞተርሳይክሎች እያባረሩ ሊገሉት ሲሉ አምልጧልከአርቲስት ዘለቀ ገሠሠ ጋር ያደረግነውን ግሩም ቃለ ምልልስ በሚቀጥለው ሳምንት ያንብቡት  

Published in ጥበብ
Page 19 of 19