“በጣም የተደበላለቀ ስሜት ነው የተሠማኝ፤ ለረጅም ጊዜ አብረናቸው የቆየናቸው ወዳጆቻችን ሳይወጡ ምንም አይነት ዝግጅት ሳይኖረንና አስቀድሞ ሳይነገረን ድንገት ውጡ ስንባል ማመን ያቅታል፣ ያስደነግጣል፤ ስሜቱ ደስታም አለበት፡፡ የቀሪዎቹም ወዳጆቻችን ጉዳይ ያሳስበኛል፤ ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ነው የተሠማኝ፡፡ እኛ የተፈታነው የውጭውን አየር መተንፈስ ችለናል፣ ቤተሰቦቻችንን ማግኘት ችለናል፣ ጓደኞቻችንን አግኝተናል፡፡ በዚህ ሁሉ መሃል የቀሩት ጓደኞቻችን ስላሉ ደስታችን ሙሉ አይደለም፡፡ እንግዲህ የቀሩት ጓደኞቻችን ይፈታሉ የሚል ተስፋ ነው የሰነቅነው፡፡
በታሰርንበት ወቅት በሃገር ውስጥና በመላው አለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያንም ሆኑ የኛን ጉዳይ ሠምተው ከጐናችን ሆነው ሲያበረታቱን ነበሩ የሌላ ሀገር ዜጐች ሁሉ ከልብ የመነጨ አክብሮታችንና ምስጋናችንንና እናቀርባለን፡፡ ለቀሩት ጓደኞቻችንም ሆነ በእስር ላይ ላሉት የሙያ አጋሮቻችን ድጋፋቸውን እንዲያሳዩ ልመናዬን አቀርባለሁ”

መንግሥት ከአንድ ዓመት በፊት በሽብር ጠርጥሬያቸዋለሁ ብሎ ክስ ከመሰረተባቸው ጋዜጠኞችና ጦማሪያን መካከል የአምስቱን ክስ አንስቶ ሰሞኑን ከእስር የለቀቀ ሲሆን ቀሪዎቹ ክሳቸው ይቀጥላል ብሏል፡፡ በሌላ በኩል ሽብርተኛ ድርጅትን በሙያ በመርዳት በሚል 5 ዓመት የተፈረደባት ጋዜጠኛና መምህርት ርዕዮት አለሙ ከ4 ዓመት ከ1 ወር እስር በኋላ ከትናንት በስቲያ በአመክሮ ደብዳቤ ከእስር ተለቃለች፡፡
ረቡዕ አመሻሽ ላይ በድንገት ከእስር የተለቀቁት ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ፣ አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሣዬ እንዲሁም ጦማሪያኑ ማህሌት ፋንታሁን እና ዘላለም ክብረት ሲሆኑ ጦማሪያኑ አቤል ዋበላ፣ በፍቃዱ ሃይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና አጥናፍ ብርሃኔ ክሳቸው ይቀጥላል ተብሏል፡፡
ከተለቀቁት ጋዜጠኞች አንዱ የሆነው ተስፋለም ወልደየስ፤ መለቀቁ ቢያስደስተውም ቀሪ ወዳጆቹ አሁንም እስራቸው መፅናቱ ብዥታ እንደፈጠረበት ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡ “ደስታችን ሙሉ አይደለም፣ የተደባለቀ ስሜት ነው እየተሰማን ያለው” ብሏል ጋዜጠኛ ተስፋለም፡፡
በመንግስት አሸባሪ ተብለው ከተሰየሙ የተለያዩ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት ፈጥረዋል የሚል የሽብር ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት ጋዜጠኞቹ፤ አቃቤ ህግ ማስረጃ አቅርቦ በማስረጃውና በክሱ ቀጣይ ሂደት ላይ ፍ/ቤት ብይን ለመስጠት ለሐምሌ 13 ቀን 2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቶ እንደነበር ይታወሳል፡፡
በሌላ በኩል ሽብርተኛ ድርጅቶችን በሙያ መርዳት በሚል ክስ ከ15 ዓመት የእስራት ፍርድ በይግባኝ ወደ 5 ዓመት እስር ዝቅ የተደረገላት ጋዜጠኛና መምህርት ርዕዮት አለሙ፤ የአመክሮ ጊዜዋ ቢጠበቅላት ኖሮ ባለፈው ጥቅምት ወር ትፈታ እንደነበረ ጠቁማ “ጥፋትሽን እመኚ” ተብላ እሺ በማለቷ፤ ሙሉ የእስራት ጊዜዋን ጨርሳ ልትወጣ 11 ወራት ሲቀራት ከትላንት በስቲያ በድንገት ከእስር መለቀቋን ለአዲስ አድማስ ገልፃለች፡፡
በሌላ በኩል ከአዲስ አበባ እና የፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ከተሞች ማስተር ፕላን ጋር በተገናኘ ተቃውሞ አስነስተዋል የተባሉ 6 የኦሮምያ ክልል የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችም ከ1 አመት ከ3 ወር እስር በኋላ ሰሞኑን እንደተለቀቁ ታውቋል፡፡
ከዩኒቨርሲቲዎቹ በፖሊስ ተወስደው ታስረው ከነበሩት ተማሪዎች መካከል አዱኛ ፌሶ፣ ቢሊሱማ ዳመና፣ ሌንጂሣ አለማየሁ፣ አብዲ ከማል፣ የአገር ሰው ወርቁ እና ቶፊክ ራሺድ ከ1 አመት በላይ በወህኒ ቤት ቢቆዩም በብዙዎቹ ላይ ክስ አልተመሰረተም ተብሏል፡፡
የጋዜጠኞቹ ጦማሪያኑ መፈታት ከህግ አንፃር
የጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ የህግ አማካሪና ጠበቃ የሆኑት የህግ ባለሙያው አቶ አመሃ መኮንን፤ በ5ቱ ታሳሪዎች መፈታት ጉዳይ ላይ ለአዲስ አድማስ በሰጡት ማብራሪያ፤ በህጉ ፍትህ ሚኒስቴር በማንኛውም ሰአት የጀመረውን ክስ የማቋረጥ ስልጣን እንዳለው ጠቅሰው፣ በፊት በነበረው አሰራር የወንጀለኛ መቅጫ ህጉን መነሻ በማድረግ፣ ክስ ለማንሳት ፍ/ቤትን ማስፈቀድ ይጠየቅ እንደነበረ ተናግረዋል፡፡ ፍ/ቤቱ ካመነበት ብቻ ክሱን ያነሳ ነበር ያሉት የህግ ባለሙያው፤ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ የወጡት አዳዲስ ህጎች የቀድሞውን ሽረው ለፍትህ ሚኒስቴር ክስ የማንሳት ስልጣን ሰጥተውታል ይላሉ፡፡
አዲሱ አዋጅ፣ የፍትህ ሚኒስትሩ ካመነበት ክሱን ያነሳል ብሎ ክስ የማንሳትን ስልጣን ለሚኒስትሩ ይሰጣል የሚሉት አቶ አመሃ፤ በተቃራኒው ፍ/ቤት “ክሱን ለምን አነሳህ?” የሚል ጥያቄ ፍትህ ሚኒስቴርን እንዲጠይቅ አለመደረጉን ይገልፃሉ፡፡ ሙሉ ለሙሉ ክስ የማንሳት ስልጣን ለፍትህ ሚኒስቴር የመሰጠቱ ጉዳይ በሚገባ መተርጎም ያስፈልገዋል ያሉት አቶ አመሃ፤ ሚኒስቴሩ በፈለገ ሰአት ክስ እያነሳና በፈለገ ጊዜ ደግሞ ክሱን እንደገና እያንቀሳቀሰ ዜጎችን መብት የማሳጣት አቅም ሊሰጠው አይገባም የሚል አተያይ አለኝ ብለዋል፡፡
ፍትህ ሚኒስቴር ይሄን ስልጣን ተጠቅሞ “ከዚህ ቀደም ለጊዜው ክሳችንን አንስተናል” ካለ በኋላ፣ በድጋሚ ክሱን የቀጠለበትን የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የክስ ሂደት ያስታወሱት የህግ ባለሙያው፤ “በወቅቱ ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግና ጠንካራ ክስ ለማደራጀት የሚል ምክንያት አቅርቦ አቃቤ ህግ ክሱን አንስቶ የነበረ ቢሆንም ኋላ ላይ ያንኑ ክስ በድጋሚ ሊያቀርብ ችሏል” ሲሉ ያስረዳሉ፡፡ “አዋጁ አላግባብ እየተተረጎመ በመሆኑ ነው እንጂ ፍትህ ሚኒስቴር ሲያሻው ክስ አቋርጦ ሲፈልግ ክሱን ማንቀሳቀስ አይችልም፤ ክሱን ሲያቋርጡ ምክንያታቸውን እንዲያቀርቡም በፍ/ቤት መጠየቅ አለባቸው” ብለዋል - ጠበቃው፡፡
የጋዜጠኞቹና ብሎገሮቹም ጉዳይ የአቃቤ ህግን ማስረጃ ይከላከሉ ወይስ በነፃ ይሰናበቱ በሚለው የህግ ሂደት ላይ ብይን ለመስጠት ለሐምሌ 13 ቀን 2007 ዓ.ም ተቀጥሮ ሳለ በድንገት 5ቱ ሲለቀቁ፣ የተለቀቁበት ምክንያት በግልፅ አልተብራራም ያሉት ጠበቃው፤ በዚህም የተነሳ ጋዜጠኞቹና ብሎገሮቹ ላይ በፈለጉት ጊዜ ክሱን ሊያንቀሳቅሱ ይችላሉ የሚል ስጋት ይፈጥራል፤ ክሱ የተነሳበት ምክንያት ባልታወቀበት ሁኔታ መተማመኛ ማግኘት አይቻልም ብለዋል፡፡
“መንግስት በፈለገ ሰአት አስሮ ባሻው ጊዜ መልቀቁ እስከመቼ ይቀጥላል” ሲል የሚጠይቀው ጋዜጠኛው፤ የተፈቱት ልጆች በአሁን ሁኔታው ነገ ተመልሰው እስር ቤት የማይገቡበት ምክንያት አይኖርም ብሎ ሙሉ ለሙሉ መተማመን አይቻልም” ብሏል፡፡
የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችም የህግ ባለሚያውን ስጋት ይጋራሉ፡፡ የመላ ኢትዮጵያውያን አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሃሪ፤ “የጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ መለቀቅ መልካም ቢሆንም ከእስር የተለቀቁበት መንገድ መንግስት ባሻው ጊዜ መልሶ ስላለማሰሩ ዋስትና አይሆንም” ብለዋል፡፡
የኢዴፓ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ወንደወሰን ተሾመ በበኩላቸው፤ ጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ መፈታታቸው መልካምና አስደሳች መሆኑን ጠቅሰው፣ የቀሩትም ቢሆኑ መፈታት አለባቸው የሚል አቋም አለን ብለዋል፡፡ “የኦባማ ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት ማቀድ በራሱ ተፅዕኖ ሳይፈጥር እንደማይቀር ጥርጣሬ አለን” ያሉት አቶ ወንድወሰን፤ የዳያስፖራው ሰሞነኛ ተፅዕኖም ቀላል ግምት የሚሰጠው አይደለም ይላሉ፡፡
የፖለቲካ ሳይንስ መምህሩና የመድረክ አመራር ዶ/ር መረራ ጉዲና በሰጡት አስተያየት፤ “የጦማሪያኑና የጋዜጠኞቹም ሆነ የሌሎች ፖለቲከኞች እስር በምዕራባውያኑ ሚዲያዎች መነጋገሪያ መሆኑን ተከትሎ እዚህ ያሉት የአሜሪካ አምባሳደር በመንግስት ላይ ተፅዕኖ ሳያሳርፉ አይቀርም የሚል ግምት አለኝ” ብለዋል፡፡
“ጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ በመፈታታቸው ደስ ብሎኛል፤ እንኳን ደስ ያላችሁ የሚል መልዕክቴ ይድረሳቸው” ያሉት ዶ/ር መረራ፤ “መንግስት ምንም እንኳ እነሱን ቢፈታም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች በኦሮሚያ ክልል ያሉ ወጣቶችን እያሰረ ነው” ብለዋል፡፡ “ወከባና እንግልቱም ከምርጫው በኋላ ተጠናክሮ ቀጥሏል” የሚሉት ምሁሩ፤ “አንዱን መፍታት አንዱን ማሰር የኢህአዴግ ባህሪ ነው” ይላሉ፡፡ “የጦማሪያኑና ጋዜጠኞቹ ከእስር መለቀቅን እንደ ቋሚ የፖሊሲ ለውጥ ማየት አያሻም” የሚሉት ምሁሩ፤ ለኦባማ እጅ መንሻ የተደረገም ሊሆን ይችላል ብለዋል፡፡
የፍትህ ሚኒስቴር የ5ቱን ጋዜጠኞችና ጦማሪያን ከእስር መለቀቅ አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ፤ በህግ በተሰጠው ክስን የማቋረጥ ስልጣን የጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ፣ አስማማው ሃ/ጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሣዬ እንዲሁም የጦማሪያኑ ማህሌት ፋንታሁን እና ዘላለም ክብረት ክስን ማቋረጡን ጠቅሶ፣ የቀሪዎቹ 4 ተከሳሾች ክስ ይቀጥላል ብሏል፡፡
አለማቀፍ ሚዲያዎችን ጨምሮ የተለያዩ አስተያየት ሰጪዎችና ፖለቲከኞች፤ የጋዜጠኞቹ መፈታት በቅርቡ ኢትዮጵያን ይጐበኛሉ ተብሎ የሚጠበቁት የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ተፅዕኖ ውጤት መሆኑን እየገለፁ ሲሆን መንግስት በበኩሉ፤ የክሱ መቋረጥና የታሣሪዎቹ መፈታት የፕሬዚዳንቱ ተፅዕኖ ውጤት አይደለም ብሏል፡፡
የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ እውነቱ ብላታ፤ የፍትህ ሚኒስቴር በህግ በተሰጠው ስልጣን በፈለገው ጊዜ ክስ ማቋረጥ እንደሚችል ጠቅሰው፤ “ለፍትህ ሚኒስቴር ክስ የማቋረጥ ስልጣን የሰጠው ህግ የወጣው ኦባማ ስለሚመጣ አይደለም፤ አስቀድሞም ያለ ነው” ብለዋል፡፡ አክለውም፤ “መንግስት በየትኛውም መንገድ ቢሆን የሀገር ሉአላዊነትን ጉዳይ ለድርድር አያቀርብም፤ ክሱ የተነሳው በማንም ተጽእኖ አይደለም፤ ፍትህ ሚኒስቴር ባለው ስልጣን ብቻ የተነሳ ነው” ብለዋል - ሚኒስትሩ ለአዲስ አድማስ በሰጡት ማብራሪያ፡፡

• መንግስት የክሱ መቋረጥ የኦባማ ተጽዕኖ ውጤት አይደለም አለ
• ለክሱ መቋረጥ ምክንያት አለመቅረቡ መልሶ ለመክሰስ ያመቻል ተባለ
• 6 የኦሮሞ ተወላጅ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም ሰሞኑን ተፈተዋል

     መንግሥት ከአንድ ዓመት በፊት በሽብር ጠርጥሬያቸዋለሁ ብሎ ክስ ከመሰረተባቸው ጋዜጠኞችና ማሪያን መካከል የአምስቱን ክስ አንስቶ ሰሞኑን ከእስር የለቀቀ ሲሆን ቀሪዎቹ ክሳቸው ይቀጥላል ብሏል፡፡ በሌላ በኩል ሽብርተኛ ድርጅትን በሙያ በመርዳት በሚል 5 ዓመት የተፈረደባት ጋዜጠኛና መምህርት ርዕዮት አለሙ ከ4 ዓመት ከ1 ወር እስር በኋላ ከትናንት በስቲያ በአመክሮ ደብዳቤ ከእስር ተለቃለች፡፡
ረቡዕ አመሻሽ ላይ በድንገት ከእስር የተለቀቁት ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ፣ አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሣዬ እንዲሁም ጦማሪያኑ ማህሌት ፋንታሁን እና ዘላለም ክብረት ሲሆኑ ጦማሪያኑ አቤል ዋበላ፣ በፍቃዱ ሃይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና አጥናፍ ብርሃኔ ክሳቸው ይቀጥላል ተብሏል፡፡ ተለቀቁት ጋዜጠኞች አንዱ የሆነው ተስፋለም ወልደየስ፤ መለቀቁ ቢያስደስተውም ቀሪ ወዳጆቹ አሁንም እስራቸው መፅናቱ ብዥታ እንደፈጠረበት ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡ “ደስታችን ሙሉ አይደለም፣ የተደባለቀ ስሜት ነው እየተሰማን ያለው” ብሏል ጋዜጠኛ ተስፋለም፡፡ በመንግስት አሸባሪ ተብለው ከተሰየሙ የተለያዩ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት ፈጥረዋል የሚል የሽብር ክስ ቀርቦባቸው የነበሩት ጋዜጠኞቹ፤ አቃቤ ህግ ማስረጃ አቅርቦ በማስረጃውና በክሱ ቀጣይ ሂደት ላይ ፍ/ቤት ብይን ለመስጠት ለሐምሌ 13 ቀን 2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቶ እንደነበር ይታወሳል፡፡ በሌላ በኩል ሽብርተኛ ድርጅቶችን በሙያ መርዳት በሚል ክስ ከ15 ዓመት የእስራት ፍርድ በይግባኝ ወደ 5 ዓመት እስር ዝቅ የተደረገላት ጋዜጠኛና መምህርት ርዕዮት አለሙ፤ የአመክሮ ጊዜዋ ቢጠበቅላት ኖሮ ባለፈው ጥቅምት ወር ትፈታ እንደነበረ ጠቁማ “ጥፋትሽን እመኚ” ተብላ
እሺ ባለማለቷ፤ ሙሉ የእስራት ጊዜዋን ጨርሳ ልትወጣ 11 ወራት ሲቀራት ከትላንት በስቲያ
በድንገት ከእስር መለቀቋን ለአዲስ አድማስ ገልፃለች፡፡በሌላ በኩል ከአዲስ አበባ እና የፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ከተሞች ማስተር ፕላን ጋር በተገናኘ ተቃውሞ አስነስተዋል የተባሉ 6 የኦሮምያ ክልል የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችም ከ1 አመት ከ3 ወር እስር በኋላ ሰሞኑን እንደተለቀቁ ታውቋል፡፡ ከዩኒቨርሲቲዎቹ በፖሊስ ተወስደው ታስረው ከነበሩት ተማሪዎች መካከል አዱኛ ፌሶ፣ ቢሊሱማ
ዳመና፣ ሌንጂሣ አለማየሁ፣ አብዲ ከማል፣ የአገር ሰው ወርቁ እና ቶፊክ ራሺድ ከ1 አመት በላይ በወህኒ ቤት ቢቆዩም በብዙዎቹ ላይ ክስ አልተመሰረተም ተብሏል፡፡የጋዜጠኞቹ ጦማሪያኑ መፈታት ከህግ አንፃር
የጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ የህግ አማካሪና ጠበቃ የሆኑት የህግ ባለሙያው አቶ አመሃ መኮንን፤ በ5ቱ
ታሳሪዎች መፈታት ጉዳይ ላይ ለአዲስ አድማስ በሰጡት ማብራሪያ፤ በህጉ ፍትህ ሚኒስቴር በማንኛውም ሰአት የጀመረውን ክስ የማቋረጥ ስልጣን እንዳለው ጠቅሰው፣ በፊት በነበረው አሰራር የወንጀለኛ መቅጫ ህጉን መነሻ በማድረግ፣ ክስ ለማንሳት ፍ/ቤትን ማስፈቀድ ይጠየቅ እንደነበረ ተናግረዋል፡፡ ፍ/ቤቱ ካመነበት ብቻ ክሱን ያነሳ ነበር ያሉት የህግ ባለሙያው፤ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ የወጡት አዳዲስ ህጎች የቀድሞውን ሽረው ለፍትህ ሚኒስቴር ክስ የማንሳት ስልጣን ሰጥተውታል ይላሉ፡፡ አዲሱ አዋጅ፣ የፍትህ ሚኒስትሩ ካመነበት ክሱን ያነሳል ብሎ ክስ የማንሳትን ስልጣን ለሚኒስትሩ ይሰጣል የሚሉት አቶ አመሃ፤ በተቃራኒው ፍ/ቤት “ክሱን ለምን አነሳህ?” የሚል ጥያቄ ፍትህ ሚኒስቴርን እንዲጠይቅ አለመደረጉን ይገልፃሉ፡፡ ሙሉ ለሙሉ ክስ የማንሳት ስልጣን ለፍትህ ሚኒስቴር የመሰጠቱ ጉዳይ በሚገባ መተርጎም ያስፈልገዋል ያሉት አቶ አመሃ፤ ሚኒስቴሩ በፈለገ ሰአት ክስ እያነሳና በፈለገ ጊዜ ደግሞ ክሱን እንደገና እያንቀሳቀሰ ዜጎችን መብት የማሳጣት አቅም ሊሰጠው አይገባም የሚል አተያይ አለኝ ብለዋል፡፡ ፍትህ ሚኒስቴር ይሄን ስልጣን ተጠቅሞ “ከዚህ ቀደም ለጊዜው ክሳችንን አንስተናል” ካለ በኋላ፣ በድጋሚ ክሱን የቀጠለበትን የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የክስ ሂደት ያስታወሱት የህግ ባለሙያው፤ “በወቅቱ ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግና ጠንካራ ክስ ለማደራጀት የሚል ምክንያት አቅርቦ አቃቤ ህግ ክሱን አንስቶ የነበረ ቢሆንም ኋላ ላይ ያንኑ ክስ በድጋሚ ሊያቀርብ ችሏል” ሲሉ ያስረዳሉ፡፡ “አዋጁ አላግባብ እየተተረጎመ በመሆኑ ነው እንጂ ፍትህ ሚኒስቴር ሲያሻው ክስ አቋርጦ ሲፈልግ ክሱን ማንቀሳቀስ አይችልም፤ ክሱን ሲያቋርጡ ምክንያታቸውን እንዲያቀርቡም በፍ/ቤት መጠየቅ አለባቸው” ብለዋል - ጠበቃው፡፡ ጋዜጠኞቹና ብሎገሮቹም ጉዳይ የአቃቤ ህግን ማስረጃ ይከላከሉ ወይስ በነፃ ይሰናበቱ በሚለው የህግ ሂደት ላይ ብይን ለመስጠት ለሐምሌ 13 ቀን 2007 ዓ.ም ተቀጥሮ ሳለ በድንገት 5ቱ ሲለቀቁ፣ የተለቀቁበት ምክንያት በግልፅ አልተብራራም ያሉት ጠበቃው፤ በዚህም የተነሳ ጋዜጠኞቹና ብሎገሮቹ ላይ በፈለጉት ጊዜ ክሱን ሊያንቀሳቅሱ ይችላሉ የሚል ስጋት ይፈጥራል፤ ክሱ የተነሳበት ምክንያት ባልታወቀበት ሁኔታ መተማመኛ ማግኘት አይቻልም ብለዋል፡፡ “መንግስት በፈለገ ሰአት አስሮ ባሻው ጊዜ መልቀቁ እስከመቼ ይቀጥላል” ሲል የሚጠይቀው ጋዜጠኛው፤ የተፈቱት ልጆች በአሁን ሁኔታው ነገ ተመልሰው እስር ቤት የማይገቡበት ምክንያት አይኖርም ብሎ ሙሉ ለሙሉ መተማመን አይቻልም” ብሏል፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችም የህግ ባለሚያውን ስጋት ይጋራሉ፡፡ የመላ ኢትዮጵያውያን አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሃሪ፤ “የጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ መለቀቅ መልካም ቢሆንም ከእስር የተለቀቁበት መንገድ መንግስት ባሻው ጊዜ መልሶ ስላለማሰሩ ዋስትና አይሆንም” ብለዋል፡፡ የኢዴፓ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ወንደወሰን ተሾመ በበኩላቸው፤ ጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ መፈታታቸው መልካምና አስደሳች መሆኑን ጠቅሰው፣ የቀሩትም ቢሆኑ መፈታት አለባቸው የሚል አቋም አለን ብለዋል፡፡ “የኦባማ ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት ማቀድ በራሱ ተፅዕኖ ሳይፈጥር እንደማይቀር ጥርጣሬ አለን” ያሉት አቶ ወንድወሰን፤ የዳያስፖራው ሰሞነኛ ተፅዕኖም ቀላል ግምት የሚሰጠው አይደለም ይላሉ፡፡ የፖለቲካ ሳይንስ መምህሩና የመድረክ አመራር ዶ/ር መረራ ጉዲና በሰጡት አስተያየት፤ “የጦማሪያኑና የጋዜጠኞቹም ሆነ የሌሎች ፖለቲከኞች እስር በምዕራባውያኑ ሚዲያዎች መነጋገሪያ መሆኑን ተከትሎ እዚህ ያሉት የአሜሪካ አምባሳደር በመንግስት ላይ ተፅዕኖ ሳያሳርፉ አይቀርም የሚል ግምት አለኝ” ብለዋል፡፡ “ጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ በመፈታታቸው ደስ ብሎኛል፤ እንኳን ደስ ያላችሁ የሚል መልዕክቴ
ይድረሳቸው” ያሉት ዶ/ር መረራ፤ “መንግስት ምንም እንኳ እነሱን ቢፈታም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች በኦሮሚያ ክልል ያሉ ወጣቶችን እያሰረ ነው” ብለዋል፡፡ “ወከባና እንግልቱም ከምርጫው በኋላ ተጠናክሮ ቀጥሏል” የሚሉት ምሁሩ፤ “አንዱን መፍታት አንዱን ማሰር የኢህአዴግ ባህሪ ነው” ይላሉ፡፡ “የጦማሪያኑና ጋዜጠኞቹ ከእስር መለቀቅን እንደ ቋሚ የፖሊሲ ለውጥ ማየት አያሻም” የሚሉት ምሁሩ፤ ለኦባማ እጅ መንሻ የተደረገም ሊሆን ይችላል ብለዋል፡፡ የፍትህ ሚኒስቴር የ5ቱን ጋዜጠኞችና ጦማሪያን ከእስር መለቀቅ አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ፤ በህግ በተሰጠው ክስን የማቋረጥ ስልጣን የጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ፣ አስማማው ሃ/ጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሣዬ እንዲሁም የጦማሪያኑ ማህሌት ፋንታሁን እና ዘላለም ክብረት ክስን ማቋረጡን ጠቅሶ፣ የቀሪዎቹ 4 ተከሳሾች ክስ ይቀጥላል ብሏል፡፡ አለማቀፍ ሚዲያዎችን ጨምሮ የተለያዩ አስተያየት ሰጪዎችና ፖለቲከኞች፤ የጋዜጠኞቹ መፈታት በቅርቡ ኢትዮጵያን ይጐበኛሉ ተብሎ የሚጠበቁት የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ተፅዕኖ ውጤት መሆኑን እየገለፁ ሲሆን መንግስት በበኩሉ፤ የክሱ መቋረጥና የታሣሪዎቹ መፈታት የፕሬዚዳንቱ ተፅዕኖ ውጤት አይደለም ብሏል፡፡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ እውነቱ ብላታ፤ የፍትህ ሚኒስቴር በህግ በተሰጠው ስልጣን በፈለገው ጊዜ ክስ ማቋረጥ እንደሚችል ጠቅሰው፤ “ለፍትህ ሚኒስቴር ክስ የማቋረጥ ስልጣን የሰጠው ህግ የወጣው ኦባማ ስለሚመጣ አይደለም፤ አስቀድሞም ያለ ነው” ብለዋል፡፡ አክለውም፤ “መንግስት በየትኛውም መንገድ ቢሆን የሀገር ሉአላዊነትን ጉዳይ ለድርድር አያቀርብም፤ ክሱ የተነሳው በማንም ተጽእኖ አይደለም፤ ፍትህ ሚኒስቴር ባለው ስልጣን ብቻ
የተነሳ ነው” ብለዋል - ሚኒስትሩ ለአዲስ አድማስ በሰጡት ማብራሪያ፡፡

Published in ዜና

     የአመራር ሽኩቻው በምርጫ ቦርድ እልባት አግኝቶ ወደ ምርጫ ውድድር የገባው የመላ ኢትዮጵያውያን አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፤ በድጋሚ የአመራር ውዝግብ የተነሳበት ሲሆን ፕሬዚዳንቱ አቶ አበባው መሃሪ ስልጣናቸውን እንዲለቁ ተጠይቀዋል፡፡ አቶ አበባው በበኩላቸው፤ “አሁን ጠቅላላ ጉባኤ የመጥራት እቅድ የለኝም፤ መሪ የሚመርጠው ጠቅላላ ጉባኤው ብቻ ነው” ብለዋል፡፡ “መኢአድን በቁርጠኝነት እንታደግ” በሚል የተቋቋመው ኮሚቴ፣ የማዕከላዊ ም/ቤት አባል የሆኑትን አቶ ፀጋዬ እሸቴ፣ አቶ ይርዳው ሽፈራው እና አቶ መላኩ መሰለን በዋና ሰብሳቢነት፣ ም/ሰብሳቢነትና ፀሐፊነት ያካተተ ሲሆን ፓርቲው ከ1997 ወዲህ ከገባበት የአመራር ችግርና ድክመት ለማላቀቅ ቆርጦ የተነሳ ኮሚቴ መሆኑን የኮሚቴው ፀሐፊ አቶ መላኩ መሰለ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡ በአመራር ችግር ምክንያት የሚጠበቅበትን ውጤት ማስመዝገብ አልቻለም የሚሉት አቶ መላኩ፤ “በተለይ ፕሬዚዳንቱ በ2007 ምርጫ የፓርቲውን መሰረታዊ አቋም የሚገዳደሩ ግድፈቶችን ፈፅመዋል፣ በግድ ወደ ምርጫው ውድድር እንድንገባም አድርገዋል” ይላሉ፡፡ በዚህም የተነሳ ፕሬዚዳንቱ በመኢአድ አላማ ሙሉ ለሙሉ አምነው እየተጓዙ ስለመሆናቸው ጥርጣሬ አለን ያሉት አቶ መላኩ፤ ሐምሌ 14 ቀን 2007 ዓ.ም ስልጣን ከያዙ ሁለተኛ አመታቸው ስለሆነ ፓርቲውን እንዲለቁ የላዕላይ ምክር ቤት አንድ ሶስተኛ የሚሆኑ አባላት ተፈራርመው ጠቅላላ ጉባኤ ለመጥራት ወስነዋል ብለዋል፡፡ “መኢአድን በቁርጠኝነት እንታደግ” በሚል የተቋቋመው ኮሚቴም በዋናነት ግብ አድርጎ የተነሳው ድርጅቱን ለማዳንና ወደ ቀድሞ አቋሙ ለመመለስ ነው ብለዋል፡፡ ፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሃሪ፤ ጠቅላላ ጉባኤውንም ሆነ ስራ አስፈፃሚውን ሳያማክሩ በግላቸው ከኢራፓና ኢዴፓ ጋር የሚያደርጉትንም እንቅስቃሴ በፅኑ እንደሚቃወሙ የኮሚቴው አባላት ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ አቶ አበባው በበኩላቸው፤ የሥልጣን ፍላጎትና ጥመኝነት እንደሌላቸው ጠቁመው፣
ሥልጣን መልቀቅ ካለብኝ የፓርቲው ደንብ በሚያዘው መንገድ ብቻ እለቃለሁ ሲሉ አስረድተዋል፡፡ ሐምሌ 14 ጠቅላላ ጉባኤ ለመጥራት ፓርቲው እንዳላቀደ የጠቀሱት ፕሬዚዳንቱ፤ ጉባኤው መቼ ይጠራ የሚለውን ስራ አስፈፃሚው ገና እየተወያየበት ነው ብለዋል፡፡  ከኢዴፓ እና ኢራፓ ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ላይ አለመድረሳቸውን የገለፁት አቶ አበባው፤ አንዳንድ የጋራ የሆኑ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ያወጣነው ስራ አስፈጻሚው በወሰነው መሰረት እንጂ በኔ የግል ውሳኔ አይደለም ሲሉም አስተባብለዋል፡፡

Published in ዜና

    የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ አመራሮች በገንዝብ ምዝበራ፣ በህገ ወጥ ሰነዶች ዝግጅትና በፓርቲ ስም ግለሰቦችን ወደ ውጭ ሃገር ልኮ ጥገኝነት በማመቻቸት እርስ በርስ እየተወነጃጀሉ ሲሆን የፓርቲው ላዕላይ ም/ቤት፣ ዋና ፀሐፊውን እና የህግ ክፍል ኃላፊ የነበሩትን አመራሮች ከፓርቲው ባሯል፡፡
ባለፈው ሰኔ 22 የላዕላይ ም/ቤት ባደረገው ስብሰባ፣ ከፓርቲው ተባረዋል የተባሉት የፓርቲው ዋና ፀሐፊ አቶ ሳሳሁልህ ከበደ እና የፓርቲው የህግ ክፍል ኃላፊ አቶ ሲራክ መኮንን፤ የፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ አየለ ጫሚሶ በአመራር ዘመናቸው በፓርቲው ስም ፈፅመዋል ያሏቸውን ህገ ወጥ ተግባራት ለአዲስ አድማስ ዘርዝረዋል።ፕሬዚዳንቱ ፈፅመውታል ከተባሉት ወንጀሎች መካከል ፓርቲው ለዋና ፅ/ቤትነት የተከራየው ቤት በወር 660 ብር የሚከፈልበት ቢሆንም ፕሬዚዳንቱ በወር 1790 ብር እንደሚከፈልበት አስመስለው በማጭበርበር በ7 ዓመት ውስጥ ከ144ሺህ ብር በላይ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል የሚለው ይገኝበታል፡፡ የፓርቲው ፕሬዚዳንት አቶ አየለ ጫሚሶ በበኩላቸው፤ የቀረበባቸው ውንጀላ ሃሰተኛ መሆኑን ጠቅሰው መዝገብ ቤት፣ ሂሳብ ሹምና ዋና ጸሃፊው አቶ ሳሳሁልህ እንደሆኑና ድርጊቱን የፈፀሙትም እሳቸው መሆናቸውን በመግለፅ በጉዳዩ ላይም ፓርቲው ክስ መስርቶ በህግ ሂደት ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡አመራሮቹ በሀሰተኛ ሰነድ ዝግጅት ላይም እርስ በርሳቸው እየተወነጃጀሉ ነው፡፡ በተገኙ ሃሰተኛ ሰነዶች ክስ ለመመስረት በዝግጅት ላይ እንደሚገኙም ጠቁመዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ በታገዱ ሰዎችና በሞተ ሰው ስም በተለያዩ ጊዜያት ወደ 17 ሺህ 500 ብር ገደማ ወጪ አድርገው ለግል ጥቅማቸው አውለዋል በሚል ቅሬታ የተወነጀሉ ፕሬዚዳንቱ በበኩላቸው፤ “ውንጀላው ሃሰተኛ ነው፤ በህይወት ያሉ ሰዎችና የፓርቲው አባላት ለሚያስፈልጋቸው ወጪዎች የተሰጠ ገንዘብ ነው፤ የሞቱ ተብለው የተዘረዘሩ ግለሰቦችም የፓርቲው አመራር ሆነው እየሰሩ ያሉ ናቸው” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ የፓርቲው ህጋዊ ማህተም የፓርቲው ፀሐፊ እጅ ተቀምጦ ሳለ ፕሬዚዳንቱ የራሳቸውን ህገ ወጥ ማህተም አስቀረፅው ይጠቀማሉ የሚለውን በተመለከተ ሲመልሱም ማህተም የሚቀመጠው ዋና ፀሐፊው ጋር ነው እንጂ እኔ ጋር አይደለም፤ ህገ ወጥ ማህተምም አላስቀረፅኩም ቢሉም ሆኖም ህጋዊውን የፓርቲ ማህተም ዋና ፀሐፊው ከፓርቲው ሲባረሩ ለማስረከብ ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ፓርቲው ለሚመለከታቸው የህግ አካላት አሳውቆ አዲስ ማህተም ማስቀረፁን አምነዋል፡፡ፕሬዚዳንቱ አቶ አየለ ጫሜሶ ፓርቲውን በመሪነት ከያዙ ጀምሮ የገዛ ልጆቻቸው እና 37 የሚሆኑ ግለሰቦች ከአገር እንዲወጡና ጥገኝነት እንዲያገኙ፣ መንግስት ግለሰቦቹ ላይ የሰብአዊ መብት ጥሰት እንደፈፀመባቸው አድርገው ሰነዶች አዘጋጅተዋል የሚል አቤቱታ የቀረበባቸው ሲሆን አቶ አየለ በበኩላቸው፤ “ስለ ቤተሰቦቼ እነዚህ ግለሰቦች አይመለከታቸውም፤ እኔ በፓርቲው ስም ማንንም በዚህ መንገድ ወደ ውጪ አልኩም” ብለዋል፡፡ አክለውም ዋና ጸሐፊው አቶ ሳሳሁልህ በዋና ፀሐፊነታቸው ስልጣን ተጠቅመው፣ የፓርቲውን ማህተም በመጠቀም ለበርካቶች ተመሳሳይ የድጋፍ ሰነድና የፓርቲ አባልነት መታወቂያ ፓርቲው ሳያወቅ ሲሰጡ እንደከረሙ ማስረጃ አሰባስበናል
ብለዋል፡፡ ጉዳዩንም በቅርቡ በፍ/ቤት ክስ መስርተው በህግ እንደሚፋረዷቸው አቶ አየለ ገልፀዋል፡፡
በአጠቃላይ የፓርቲው ፕሬዚዳንት የተለያዩ የተጭበረበሩ ሰነዶችን በመጠቀም በድምሩ በመቶ ሺህ
የሚቆጠር ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል፣ ህገ ወጥ ማህተም አስቀርፀው ሰዎችን ወደ ውጭ ሲልኩ ነበር የሚል ውንጀላ ከእነ አቶ ሲራክ መኮንን ቢሰነዘርባቸውም ፕሬዚዳንቱ በበኩላቸው፤ ዋና ፀሐፊው አቶ ሳሳሁልህ እና ባልደረባቸው አቶ ሲራክ በመመሳጠር ፓርቲውን መዝብረዋል እንጂ በኔ ላይ ያቀረቡት ውንጀላዎች ሃሰተኛ ናቸው፣ ማስረጃ ካላቸው በህግ ይፋረዱኝ ብለዋል፡፡

Published in ዜና

- ለስዊድኑ “ሲዳ” የላቀ አገልግሎት ሽልማት ይሰጣል
- ዩኒቨርሲቲው ከአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች በ9ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ 97 ተማሪዎችን በድህረ ምረቃ ፕሮግራም አስመርቋል
               
 
    የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ 9851 ተማሪዎችን በመጀመሪያ፣ በሁለተኛና በሦስተኛ ዲግሪ በሚሌኒየም አዳራሽ ከ2፡00 ጀምሮ እንደሚያስመርቅ የዩኒቨርሲቲው የህዝብ ግንኙነት ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡
የጽ/ቤቱ ዳይሬክተር አቶ አሰማኸኝ አስረስ በተለይ ለአዲስ አድማስ በሰጡት መግለጫ፤ ዩኒቨርሲቲው ዘንድሮ በ10 ኮሌጆችና በ12 ኢንስቲትዩቶች ያስተማራቸውን 9851 ተማሪዎች እንደሚያስመርቅ ጠቅሰው፤ እነዚህ ተመራቂዎች ዓመቱን ሙሉ በመስከረም፣ በታኅሣሥ፣ በየካቲትና በሐምሌ ወር ትምህርት ያጠናቀቁትን እንደሚያካትት ገልጸዋል፡፡
የዛሬ ተመራቂዎች በመደበኛ ፕሮግራም 5920፣ በመደበኛ የዶክትሬት (PHD) ትምህርት 228 (ከዚህ ውስጥ 8 በመቶ ሴቶች ናቸው)፣ በዩኒቨርሲቲው የሚያስተምሩ መምህራን ሁሉ በሚያስተምሩት ትምህርት መሰልጠን አለባቸው በሚለው አዲስ ፕሮግራም የሠለጠኑ 233 መምህራን፣ 1930 በማታው ክፍለ ጊዜና 1540 በክረምት ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው ብለዋል፡፡
ከዘንድሮ ተመራቂዎች ውስጥ 6469 ተማሪዎች በመጀመሪያ ዲግሪ (ሴት 1774፣ ወንድ 4695) በሁለተኛና በሦስተኛ ዲግሪ (ፖስት ግራጁየት) 2658 ወንዶችና 724 ሴቶች እንደሆኑ ዳይሬክተሩ ጠቅሰው፣ ከዚህ ውስጥ 228ቱ ዶክተሮች እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡ ይህን ያህል ቁጥር ያላቸው ዶክተሮች በማስመረቅ አአዩ ከአፍሪካ ቀዳሚ መሆኑንና አንዳንድ ድረ ገፆች በሚያወጡት መረጃ መሰረት፤ ከአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች በ9ኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ እንደሆነ አመልክተዋል፡፡
በየጊዜው የምናከናውነውን ሥራ ስለማናስተዋውቅ ነው እንጂ ደረጃችን ከዚህም ከፍ እንደሚል እናምናለን ያሉት አቶ አሰማኸኝ፣ በቅርብ ካሉ አገሮች የሚበልጡን የግብፅ፣ የኬንያ የታንዛኒያና የደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ናቸው፡፡ እየሰራንባቸው ያሉትን ፕሮግራሞች በመፈተሸ (በመከለስ) የሚቀሩትን አስወግደን የሚጨመሩ አዳዲስ ፕሮግራሞች ለማካተት አቅደናል፡፡ አዳዲሶቹን ፕሮግራሞች ስንጀምርና ሥራዎቻችንን ስናስተዋውቅ ደረጃችን ከፍ ይላል፡፡ በአሁኑ ወቅት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በስተቀር ከ100 የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ስም ዝርዝር ውስጥ የተጠቀሰ አንድም ኢትዮጵያዊ ዩኒቨርሲቲ የለም በማለት አስረድተዋል፡፡
በዘንድሮው የምረቃ ሥነ-ሥርዓት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለማንም የክብር ዶክትሬት እንዳልሰጠ ዳይሬክተሩ ጠቅሰው፤ ዓለም አቀፉ የስዊድን የልማት ድርጅት (Sewden International Development Association – SIDA ሲዳ) እ.ኤ.አ ከ1980 ዓ.ም አንስቶ በተለያዩ ማህበራዊ ዘርፎች በእርሻ በትምህርት፤ በጤና… ላበረከታቸው ድጋፎች እውቅና ለመስጠት ዩኒቨርሲቲው ሲዳ በአገሪቷ ትምህርት እንዲዳብር የአንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች በመገንባት ለተጫወተው ሚና የተለየ የአገልግሎት ሰርቪስ (Special Service Award) ይሰጣል ብለዋል፡፡
ከዘንድሮ ተመራቂዎች ከፍተኛውን ቁጥር (763) በመያዝ ሲቪል ኢንጂነሮች ቀዳሚ ናቸው፡፡ 380 ተማሪዎች ዘንድሮ ስለማይመረቁ ነው እንጂ ቀጥራቸው ከሺህ በላይ ይሆን ነበር ብለዋል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ በ70/30 ቅበላ መሰረት ከ70 በላይ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በመሆናቸው ነው፡፡
የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚዎች 12 ሲሆኑ አራቱ ሴቶች ናቸው ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ከፍተኛውን 4 ነጥብ ያመጣው አንድ ተማሪ ከተፈጥሮ ሳይንስ ኮሌጅ ነው ብለዋል፡፡ በዛሬው ምረቃ ለየት ያለው ነገር ሁለት ሴት የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚዎች ለመለየት አለመቻል ነው፡፡ ኤልሳ ኪሮስ ወልዱና ኤልሳቤጥ ደሳለኝ ረጋሳ ያመጡት ነጥብ እኩል 3.64 ሆነ፡፡ በተለያዩ መመዘኛዎች ለመለየት ቢሞከርም አልተቻለም፡፡ ኤግዚቢሽን ወይም ሴሚናር አዘጋጅተው ገለጻ ያድርጉ፣ … የሚሉ ሀሳቦች ቀርበው ነበር፡፡ ግን ጊዜው ስላጠረ ይህም አልተቻለም፡፡ በመጨረሻ ሴኔቱ ሁለቱም ሴቶች የወርቅ ሜዳሊያ ይሸለሙ በማለት መወሰኑን አቶ አሰማኸኝ ገልፀዋል፡፡ ከ10    ኮሌጆችና ከ12 ኢንስቲትዩቶች ሴቶች ብቻ ተወዳድረው የተሻለ ነጥብ ያመጡ (Top Scorers) 12 ሴቶችም የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ናቸው፡፡     
በሌላ በኩል ጅማ ዩኒቨርሲቲ በማስተር ኦፍ ቢዝነስ አድሚኒስትሬሽንና በማስተር ኦፍ ፐብሊክ ሄልዝ ያስተማራቸውን 97 ተማሪዎች ከትናት በስቲያ በሸራተን ሆቴል አስመርቋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በአዲስ አበባ በኤቢኤች ካምፓስ በሁለቱ የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ካስመረቃቸው 97 ተማሪዎች መካከል 24ቱ ሴቶች ናቸው፡፡

Published in ዜና

ከ13 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ ሆኖበታል ተብሏል
ኮሪያ ሆስፒታል ከ13 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ በማድረግ የሰራው የሆስፒታሉ የማስፋፊያ ፕሮጀክት በትላንትናው ዕለት ተመረቀ፡፡ ሆስፒታሉ በኮሪያ ዘመቻ ላይ የተሳተፉ ኢትዮጵያውያን ዘማቾች ላደረጉት አስተዋፅኦ እንደ ምስጋና ሆኖ እንዲሰራና አገልግሎት እንዲሰጥ ታስቦ እ.ኤ.አ በህዳር ወር 2004 ዓ.ም መመስረቱን የገለፁት የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ኪም ቹልሱ፤ዛሬ በአገሪቱ በህክምናው ዘርፍ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሱ የህክምና ባለሙያዎችና ዘመናዊ መሳሪያዎች የሚገኙበት ታላቅ ሆስፒታል ለመሆን መብቃቱን ገልፀዋል፡፡ እስከአሁን በአገሪቱ ውስጥ የማይሰጡ የተለያዩ የህክምና አይነቶችን ጨምሮ ከ20 በላይ ዲፓርትመንቶችን ያቀፈው አዲሱ የማስፋፊያ ፕሮጀክት፣እጅግ ዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎችና ከ60 በላይ VIP አልጋዎችን መያዙን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ ሆስፒታሉ ሲቋቋም ይዞት ከነበሩ ዕቅዶች ሁለተኛው ሲሆን ተግባራዊ መሆን ከሚገባው ጊዜ በጥቂት አመታት መዘግየቱ ተጠቁሟል፡፡ ቀጣዩ የሆስፒታሉ ዕቅድ (Third phase) መንትያ ህንፃዎችን መገንባትና የሆስፒታሉን አስተዳደርና ስራውን ሙሉ በሙሉ ለኢትዮጵያውያን ማስረከብ እንደሆነም በዚሁ ወቅት ተገልጿል፡፡

Published in ዜና

ሆስፒሉ ቅሬታውን አስተባብሏል

   የሚዮንግ ስንግ አጠቃላይ ሆስፒታል (ኮሪያ ሆስፒታል) በአገልግሎት አሰጣጡና በሰራተኞች አያያዙ
ላይ ችግሮች እንዳሉበት የገለፁ የሆስፒታሉ ሰራተኞች፤ በኢትዮጵያውያን ሰራተኞች ላይ የሚፈፀሙ በደሎችና አድልዎችን የሚቃወሙ ሰራተኞች ከስራቸው እንደሚባረሩ ተናገሩ፡፡ በሆስፒታሉ ውስጥ
የሚከናወኑ ህገ ወጥ ስራዎችን የሚቃወሙ ሰራተኞችም ከስራ ይወገዳሉ ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን ዘማቾች በኮሪያ ዘመቻ ወቅት ያደረጉትን አስተዋፅኦ ለማሰብ እ.ኤ.አ በ2004 ዓ.ም በደቡብ ኮሪያውያን የተመሰረተው ሆስፒታሉ፤ በዘመናዊ መሳሪያዎችና ከፍተኛ ዕውቀት ባላቸው ባለሙያዎች እየታገዘ አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱን ሰራተኞቹ ያስታውሳሉ፡፡ ሆኖም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ችግሮች እየታዩ መምጣታቸውን የሚናገሩት ሰራተኞቹ፤ ተገልጋዩ ህብረተሰብ ከፍተኛ ዋጋ ከፍሎ ለሚያገኘው የህክምና አገልግሎት ምንነቱን ለመረዳት የማይቻልና በኮሪያ ቋንቋ የተፃፉ መርፌና መድኀኒቶች እንደሚታዘዙለት ይናገራሉ። ይህንን ለመቃወም የሞከረ ታካሚ፤ “ምን ዓይነት ህክምና መስጠት እንዳለብን ካወክ ለምን መጣህ” የሚል ጥያቄ በማንሳት፣ ህክምናውን ከእነአካቴው ይነፈጋል ብለዋል፡፡በሆስፒታሉ የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች በደቡብ ኮሪያውያኑ የሥራ ኃላፊዎች አድልዎና ጫና ይደረግባቸዋል የሚሉት ሰራተኞቹ፤ ለመብታቸው ለመከራከር የሚሞከሩ ኢትዮጵያውያን ራተኞችም ከስራ እንደሚባረሩ ተናግረዋል፡፡በሃይማኖት ልዩነት ሳቢያ በሰራተኞች ላይ አድልዎና መገለል እንደሚፈፀም የሚናገሩት  ሰራተኞቹ፤ ሰራተኛው ያለፍላጎቱ የእነሱን ሃይማኖት እንዲከተል መገደዱንም ገልፀዋል፡፡ በሆስፒታሉ የሰራተኞች ማህበር የሚባል ነገር እንደሌለም ተናግረዋል፡፡ ሆስፒታሉ በምግብ መድኀኒትና ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን ታውቀውና  ተመርምረው ወደአገር ውስጥ እንዲገቡ ከሚፈቀድላቸው መድኀኒቶች ውጪ ሌሎች መድኀኒቶችን ወደ አገር ውስጥ እንደሚያስገባ
የጠቆሙት ሰራተኞቹ፤ መድኀኒቶቹ ሙሉ በሙሉ በኮሪያ ቋንቋ የተፃፉና ምንነታቸው የማይታወቅ
ሲሆን በከፍተኛ ዋጋ ለህመምተኞች የሚሸጡና በሃኪሞች የኮድ ትዕዛዝ የሚሰጡ ናቸው ብለዋል፡፡ ጠቅላላ የቀዶ ጥገና ስፔሻሊስትና የሆስፒታሉ ምክትል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ሰለሞን በቀለ በሆስፒታሉ አሰራር ላይ የሚነሱ አቤቱታዎችን አስመልክተው ሲናገሩ፤ በሆስፒታሉ አልፎ አልፎ የሚነሱ አንዳንድ ቅሬታዎች መኖራቸውን ጠቁመው፣ እነዚህ ቅሬታዎች ግን የሆስፒታሉን የአሠራር ሥርዓት ካለመገንዘብ የተነሳ የሚከሰቱ ናቸው ብለዋል፡፡ ለዚህም እንደምሳሌ የሚጠቅሱት በሆስፒታሉ የሚሰጠውን የፈጣን ክሊኒካል አገልግሎት ነው፡፡ በዚህ አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን የሚፈልግ ሰው ከመደበኛው የካርድ አገልግሎት ሦስት እጥፍ ያህል ከፍሎ ተራ ሳይጠብቅ በቀጥታ ወደ ሃኪሙ የሚገባበት አሠራር መኖሩን ጠቁመው፣ አሠራሩ ለሁሉም ታካሚ በግልፅ የሚነገርበት መንገድ ባለመኖሩ ቅሬታዎች ሲፈጠሩ ተመልክተናል ብለዋል፡፡ ሆስፒታሉ አሠራሩን የማስተካከል እርምጃ እንደሚወስድና ሁሉም ተገልጋይ አሠራሩን በግልጽ አውቆ እኩል የሚስተናገድበት መንገድ እንደሚመቻችም ምክትል ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ በሠራተኞች አስተዳደር ላይ የተነሱ ቅሬታዎችን በተመለከተም ችግሮች ሙሉ በሙሉ የሉም
ለማለት እንደሚቸገሩ የገለፁት ኃላፊው፤ በሆስፒታሉ ውስጥ ለተቋቋመው የዲሲፒሊን ኮሚቴ ቅሬታዎችን በማቅረብ የእርምት እርምጃ ማስወሰድ ይቻላል ብለዋል፡፡ በሆስፒታሉ ውስጥ በሃይማኖት ልዩነት ሳቢያ ይፈፀማል የተባለውን አድልዎ በተመለከተም፤ የሆስፒታሉ ሠራተኞች በሃይማኖት ሳቢያ አድልዎና መገለል ይፈፀምባቸዋል የሚለውን ቅሬታ በተደጋጋሚ የሚሰሙ ቢሆንም በግልጽ ሲፈፀምያዩት አድልዎ አለመኖሩን ተናግረዋል፡፡ ቀደም ሲል የሆስፒታሉ ሠራተኞችም ሆኑ ለአገልግሎት የሚመጡ ህሙማን የሃይማኖት ትምህርትና ሰበካ ይደረግላቸው እንደነበር ያስታወሱት ዶክተሩ፤ አሁን ግን ሙሉ በሙሉ መቅረቱንና በሳምንት አንድ ቀን ቅዳሜ ቅዳሜ ለሚፈልግ ሠራተኛ ብቻ በፍላጎት ትምህርትና ሰበካው እንደሚሰጥ አስረድተዋል፡፡ ከመድሃኒት አቅርቦት ጋር በተያያዘ የተነሳውን ችግር በተመለከተ ሲናገሩም፤ በሆስፒታሉ የአገልግሎት ጊዜያቸው ያለፉ መድሃኒቶችን እንደማይጠቀሙ ገልፀው፣ በኮሪያ ቋንቋ የተፃፉ
መድሃኒቶች አገልግሎት ላይ የሚውሉበትን አግባብ አብራርተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ እንደልብ
ተፈልገው የማይገኙ መድሃኒቶች ሲሆኑ ጥቅም ላይ ይውላሉ በማለት፡፡ እሱም ቢሆን የምግብ መድሃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደር ቁጥጥር ባለስልጣን ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ስለተሰጠ ከመጠቀም መታቀባቸውን ገልፀዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብ፣ መድሃኒትና ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን፤ በሆስፒታሉ ውስጥ ይከናወናሉ የተባሉ ህገወጥ ተግባራትንና ከባለስልጣን መ/ቤቱ ዕውቅናና ፈቃድ ውጪ ወደ አገር ውስጥ ገብተው ጥቅም ላይ ይውላሉ የተባሉትን መድሃኒቶች በተመለከተ ለሆስፒታሉ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያዎችን እንደፃፈ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ሆስፒታሉ የጤና አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ የተቋቋመ እንደመሆኑ፣ ከጤና አገልግሎቶች ውጪ ለተገልጋዩ ህብረተሰብ የሃይማኖት ሰበካ መተላለፍ እንደማይገባው ጠቁሞ፣ ይህ ህገወጥ ተግባርም በአስቸኳይ እንዲቆም በፃፈው ማስጠንቀቂያ አስታውቋል፡፡ ሆስፒታሉ በመድሃኒት አገልግሎት አሰጣጡ ላይ ተገቢውን ቁጥጥርና ክትትል አያደርግም ያለው የባለስልጣን መ/ቤቱ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ፤ በመድሃኒቶቹ ላይ ስለመድሃኒቱ የሚገልፁ ጽሑፎች በኮሪያ ቋንቋ የተፃፉ መሆናቸው ስለመድሃኒቱ አገባብና ጥራት በቂ መረጃ እንዳይኖር አድርጓል ብሏል፡፡ አንዳንድ የመድሃኒት ማዘዣ ወረቀቶች በኮድ መፃፋቸው ከሆስፒታሉ መድሃኒት ለመግዛት የማይፈልጉ ወይም የማይችሉ ታካሚዎችን ችግር ውስጥ እንደሚጥላቸውና ወደ ሃኪማቸው ጋ ተመልሰው በድጋሚ ለማፃፍ እንደሚገደዱ ጠቅሶ፣ ይህም ትክክለኛ አሠራር አለመሆኑን በመግለጽ አፋጣኝ የማሻሻያ እርምጃዎች ሊወስዱ እንደሚገባ ባለስልጣን መ/ቤቱ በማስጠንቀቂያ ደብዳቤው ገልጿል፡፡    

Published in ዜና

    መኖሪያ ቤቶችንና ንብረቶችን በኢንተርኔት መሸጥና መግዛት የሚያስችል ዘመናዊ የግብይት ሥራ
የሚያከናውን “ላሙዲ” የተባለ አለምአቀፍ የኦንላይን ሪልስቴት ኩባንያ ሥራ ጀመረ፡፡ደንበኞች ንብረታቸውን በቀላሉ ለመሸጥና ለመግዛትያስችላቸዋል የተባለው ዘመናዊው የኢንተርኔት መገበያያበኢትዮጵያ ሥራ መጀመሩን አስመልክቶ ከትናንት በስቲያበኩባንያው ቢሮ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይእንደተጠቆመው፤ በአገሪቱ ሪልእስቴቶች ከጊዜ ወደ ጊዜእያደጉና እየሰፉ የመጡ ሲሆን በዚህም የተነሳ ደንበኞችስለ መኖሪያ ቤቶች በቂና ጥልቀት ያለው መረጃ ለማግኘትየሚችሉበት መንገድ በስፋት ሊኖር ይገባል፡፡ ኩባንያውገዢና ሻጭ በኦንላይን ተገናኝተው መኖሪያ ቤታቸውንናሌሎች ንብረቶች እንዲገበያዩ ያስችላል ተብሏል፡፡ኩባንያው ኢንተርኔት ለማይጠቀሙ ደንበኞቹዳያል 4 ሆም የተሰኘ የስልክ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆንደንበኞች ስልክ በመደወል የሚፈልጉትን መኖሪያ ቤትበተመለከተ ዝርዝር መረጃና አገልግሎት እንደሚያገኙተገልጿል፡፡ እስካሁን ከተለያዩ ሪል እስቴቶችና ወኪሎችያገኛቸውን 20ሺ ገደማ መኖርያ ቤቶችና ንብረቶችበድረገፁ ላይ እንዳቀረበም ለማወቅ ተችሏል፡፡ላሙዲ በተለያዩ ዘርፎች የኦንላይን አገልግሎትየሚሰጥ ሲሆን በኬንያ፣ ታንዛኒያ፣ ናይጀሪያ፣ ጋና፣ኡጋንዳና ሩዋንዳ ቢሮዎቹን ከፍቶ ተመሳሳይአገልግሎቶችን በመስጠት ላይ የሚገኝ ኩባንያ እንደሆነታውቋል፡፡

Published in ዜና

ተልዕኮው በአልሻባብ ላይ ጥቃት መሰንዘር ነው ተብሏል

ከባድ መሳሪያ የታጠቁ 3ሺህ ያህል ወታደሮችን የያዘ የኢትዮጵያ ጦር፣ በአልሻባብ ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ባለፈው ሰኞ ወደ ሶማሊያ መግባቱን ዘ ኔሽን ጋዜጣ ከትናንት በስቲያ ዘገበ፡፡ከሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ በ450 ኪሎ ሜትሮች ርቃ በምትገኘዋ ዶሎ ከተማ የሚኖሩ የአይን እማኞችን በመጥቀስ ዘገባው እንዳለው፣ ከባድ መሳሪያ የታጠቁና በታንክ የታገዙ የኢትዮጵያ ወታደሮች ወደ ሉኩ ከተማ ሲጓዙ የታዩ ሲሆን የአካባቢው ነዋሪዎችም ወታደሮቹ የሚያመሩት በአልሻባብ ቁጥጥር ስር ወደምትገኘው ባርዴሬ ከተማ ሳይሆን አይቀርም ሲሉ ግምታቸውን ሰጥተዋል፡፡ባርዴሬ በሶማሊያ ጌዶ ክልል ውስጥ ከሚገኙ ከተሞች በአልሻባብ ቁጥጥር ስር የምትገኝ ብቸኛዋ ከተማ ናት ያለው ዘገባው፤ አልሻባብ በተለይም በተያዘው የረመዳን ጾም ወቅት በሶማሊያ መንግስትና በአሚሶም ጦር ላይ የሚፈጽመውን ጥቃት አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል፡፡የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ በበኩሉ፤ የኢትዮጵያ ጦር እ.ኤ.አ በ2006 አሸባሪውን አልሻባብ ለመደምሰስ ወደ ሶማሊያ መግባቱን አስታውሶ፣ ከዚያ በኋላ ባሉት ጊዜያትም የኢትዮጵያ ጦር በተደጋጋሚ የሶማሊያን ድንበር አልፎ መግባቱን ገልጧል፡፡አልሻባብ በሶማሊያ ውስጥ ይዟቸው ከነበሩ አብዛኞቹ አካባቢዎች ቢለቅም መጠነ ሰፊ ጥቃት መሰንዘሩን ገፍቶበታል ያለው ዘገባው፤ ባለፈው ማክሰኞ በሰሜን ምስራቅ ኬንያ በፈጸመው ጥቃት 14 ሰዎችን መግደሉንም አክሎ አስታውሷል፡፡

Published in ዜና

  ዛሬ በአቡነ ጴጥሮስ አደባባይ ይጀመራል
   የክረምቱን መግባት ተከትሎ በመዲናዋ ታላቅ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም ዘመቻ አርሴማ በሚል የተዘጋጀ ሲሆን ዛሬ በአቡነ ጴጥሮስ አደባባይ አካባቢ ተከላው ይጀመራል፡፡  
 ወደ 150 ሰው ገደማ ይሳተፍበታል ተብሎ በሚጠበቀው የችግኝ ተከላ ፕሮግራም፤ከአቡነ ጴጥሮስ እስከ ፖሊስ ክበብ ባለው የዋናው መንገድ አካፋይ ላይ ወደ 280 የተለያዩ የዛፍ ዝርያዎች እንደሚተከሉ ፕሮጀክቱን የሚመራው ኤልፍሬዝ ፕሬስ ስራዎች ኃላ.የተ.የግ. ማህበር አስታውቋል፡፡
የችግኝ ተከላ አስተባባሪዋ አርሴማ በቀለ፤ከዛሬው ፕሮግራም በተጨማሪ ከሐምሌ 4-9  ለ 5 ቀናት የሚዘልቅ ታላቅ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም በመዲናይቱ መዘጋጀቱን ለአዲስ አድማስ ገልጻለች፡፡  የችግኝ ተከላው ሐምሌ 4 በሚኪላንድ አካባቢ የሚጀመር ሲሆን በሌሎች በተመረጡ አካባቢዎችም ይከናወናል ተብሏል፡፡
የችግኝ ተከላው የሚካሄደው በበጐ ፍቃደኛ ወጣቶችና የህብረተሰቡ ክፍሎች መሆኑን የጠቆመችው አስተባባሪዋ፤የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ችግኞችን በጉዲፈቻ (በአደራ) እንደሚሠጥና ተካዩ አመቱን ሙሉ የመንከባከብ ግዴታ እንደሚጣልበት ተናግራለች፡፡  
የአካባቢ መራቆት በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የገለጸችው አስተባባሪዋ፤ድርጅቷ እየጠፋ ያለውን የደን ሃብት የመታደግ አላማ አንግቦ መርሃግብሩን ለማከናወን እንዳቀደ ገልፃለች፡፡ በየአመቱም የችግኝ ተከላና እንክብካቤ በመዲናዋና ከመዲናዋ ውጪም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ገልፃለች፡፡
ኤልፋሬዝ ፕሬስ ስራዎች “አርሴማ” የተሰኘች ጋዜጣ የሚያሣትም ሲሆን ላለፉት 7 አመታት በማህበራዊና በሴቶች ጉዳይ ላይ አተኩራ ስትታተም ቆይታለች፡፡

Published in ዜና
Page 12 of 17