የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በሆነው ሀብታሙ አያሌው የተፃፈው “ሀገርና ፖለቲካ” የተሰኘ መፅሀፍ ሰሞኑን  ለንባብ በቃ፡፡ በ18 ምዕራፍና በ272 ገፆች የተቀነበበው መፅሀፉ፤ ስለ ኢትዮጵያ አመሰራረት፣ ስለ ኢትዮጵያ ስያሜ፣ ስለ ፖለቲካና ሃይማኖት፣ ስለ ቀደምት ኢትዮጵያ አፄዎችና ሌሎች በርካታ ርዕሰ ጉዳዮች ተነስተውበታል፡፡ የመፅሀፉ አዘጋጅ አቶ ሃብታሙ አያሌው፤ የኢህአዴግ መንግስት ለታሪክና ለሀገር ያለው እጅግ የመረረ ጥላቻና አፍራሽ ተልዕኮ መፅሀፉን ለመፃፍ እንዳነሳሳው በመግቢያው ላይ ገልጿል፡፡ መፅሀፉ በ54 ብር ከ99 ሳንቲም እየተሸጠ ነው፡፡

Saturday, 05 July 2014 00:00

ቪያግራና ‘ምስር’…

እንዴት ሰነበታችሁሳ!
ስሙኝማ…እንግዲህ ጨዋታን ጨዋታ ያነሳው የለ…መቼም ምዕራባውያኑ እንደ ሩስያዎች መቀለጃ ያላቸው አይመስልም፡፡ ይቺን ስሙኝማ…በአንድ ወቅት የሩስያ መሪ የነበሩት ብሬዥኔቭ አንድ ስነ ስርአት ላይ ረዘም ያለ ንግግር ያደርጋሉ፡፡ ከዚያ ንግግሮችን የሚጽፍላቸውን ሰው ይጠሩና “ጻፍልኝ ያልኩህ የአሥራ አምስት ደቂቃ ንግግር ነበር፡፡ ለምንድነው የአርባ አምስት ደቂቃ ንግግር የጻፍክልኝ?” ሲሉ ያፈጡበታል፡፡ ንግግር ጸሃፊውም “ጌታዬ፣ የአሥራ አምስት ደቂቃ ንግግር ነው የሰጠሁዎት…” ይላል፡፡ ብሬዥኔቭም “ታዲያ ለምን አርባ አምስት ደቂቃ ፈጀብኝ?” ሲሉት ሲፈራ፣ ሲቸር ምን ብሎ ቢመልስ ጥሩ ነው…“ጌታዬ የንግግሩን ሦስት ቅጂ ነው የሰጠሁዎት፡፡”
ልቤ ጠረጠረ…የምር ልቤ ጠረጠረ! እኛ ዘንድ አንዳንድ ተናጋሪዎች አምስቱንም ቅጂ ነው እንዴ የሚያነቡልን! እንዲህ አይነት ነገር መኖሩን መች አወቅንና!  ለነገሩ ያንን ሁሉ ለማንበብም ‘አቅም’ ያስፈልጋል፡፡
ክፋቱ ዘንድሮ አቅም ጠፋ፡፡ አቅም ሲጠፋ ደግሞ ‘ጉልቤ’ በዛ!
ስሙኝማ…ሆሊዉድ እስከዛሬ ‘ኸልፕለስ’ ምናምን የሚል ፊልም አልሠራ ከሆነ እነስፒልበርግ እኛ ዘንድ ቢመጡ አሪፍ ነው፡፡ አምስት መቶ ምናምን ክፍሎች ያሉት…አይደለም የፈጠራ ሥራ፣ ‘ሪያሊቲ ሾው’ ምናምን የሚሉትን ሊሠሩ ይችላሉ፡፡
የምር…አቅመ ቢስነት ጨረሰንማ! ምን አቅመ ቢስ ያልሆንንበት ነገር አለ! ለነገሩ ሰባ ስድስት ሚሊዮናችንን አይደል “ድሆች ናቸው” ያሉን፡፡ አቅም ብናጣ ምን ይገርማል! ኮሚክ እኮ ነው…በድሆች ብዛት የሚቀድሙን አምስት አገሮች ናቸው አሉ!
ስሙኝማ…እንግዲህ ጨዋታም አይደል…ይሄ ክሊኒኩና የባህል መድሀኒት አዋቂው ሁሉ “ለስንፈተ ምናምን’ መፍትሄ አለን…” የሚሉት…አለ አይደል… በነገርዬው በኩል ያለው ‘አገር አቀፍ’ አቅም ይሄን ያህል ወርዷል ማለት ነው!
እኔ የምለው…ነገርን ነገር ያነሳዋል አይደል የሚባለው…ይሄ ቪያግራ የሚሉት ነገርዬ መጀመሪያ የታሰበው ለ‘ሲኒየር ሲቲዘንስ’ አልነበረም እንዴ! (ለነገሩ ምን መሰላችሁ…ይሄ ‘ጂም’ የሚሉት ነገር በዛና ‘ሲኒየሩ’ን ሁሉ ‘ጁኒየር’ እያደረገው ነው አሉ! እነሆ በረከት ምነው አይበዛሳ! ስሙኝማ…እንትናና እንትናዬዎች ፍለጋ በየሁለትና በየሦስት ወሩ ‘ጂም’ የሚለዋውጡ አሉ የሚባለው እውነት ነው እንዴ!) በአንድ ወቅት “ረጅም ዘመን ያገለገለ አሮጌ ካሚዮን ሞተር በማኖቬላ ነው የሚነሳው…” ያልከኝ ወዳጄ…ጥሬ ሥጋ በሚጥሚጣ ሞክረሀል፡ ያው እሱም የማኖቬላ (ጣልይንኛውን ምናምነኛ አደረግሁት እንዴ!) አገልግሎት ይሰጥ እነደሁ ብዬ ነው፡፡
እናላችሁ…የከተማው ወጣት ሁሉ (ከአንዳንደ ‘ጩጬዎች’ ጭምር)  ‘ቪያግራ’ ቃሚ ሆነና አረፈው!
ስሙኝማ...እንደው ‘የፈረንጅ ነገር’ ሆኖብን እንጂ አሁን ቪያግራን የሚተካ አገር በቀል ብልጠት ጠፍቶ ነው! ደግሞ ላልጠፋ ምስር፡፡ ከነተረቱ እኮ “ምስር…ይቀስር” ይባላል! ቂ…ቂ…ቂ….
በሁሉም ነገር አቅም የሚጨምር ‘ምስር’ ይላክልንማ!
የምር ግን፣ እንግዲህ ጨዋታን ጨዋታ ያነሳው የለ… ጥያቄ አለን…በተለምዶ ምስር ከምግብነት ውጪ “አለው” የሚባለው ጥቅም ያው የታወቀ ነው፡፡ ምን ግርም ይልሀል አትሉኝም… እንደው አንድ እንኳን ተመራማሪ “ይህ ነገር እውነት ይሆን እንዴ!” ብሎ ምርምር አደረገ ወይ እያደረገ ነው ሲባል የማንሰማሳ!! ልክ ነዋ…እንዲሀ አይነት ‘ወሬ’ እኮ ከትውልድ ትውልድ እየተላለፈ የሚመጣው ዝም ብሎ (‘ከመሬት ተነስቶ’ እንደማለት) አይደለም፡፡
እኔ የምለው… ቪያግራ የደም ዝውውርን አፋጥኖ ምናምን (‘ደም አፍልቶ’ እንደማለት) ‘ቁልቁል’ ይሰደዋል አይደል የሚባለው?
ልጄ፣ ዘንድሮ በሌላ ሌላ ‘ብሮባጋንዳችንን’ ያፍርሱብን እንጂ ‘ደም በሚያፈሉ’ ነገሮች እጥረት እንኳን አንታማም፡፡ አይደለም ለእኛ ለእነሱም እንተርፋለን፡፡ ክፋቱ ‘ደማችን ሲፈላ’ የሚወጣው ሽቅብ ሆነ እንጂ! ቢቻል ‘መንገዱ ዝግ ነው’ የሚል ለጥፎ ወደ ቁልቁል የሚመለስበትን ዘዴ ቢፈጥሩልን አሪፍፈ ነበር፡፡  እሱን ዘዴ ብንደርስበት የቪያግራ ገበያ በዘጠና አምስት በመቶ ይቀንስ ነበር፡፡
ደግሞላችሁ… ጠጅ አለ…ደግሞ ዳግም አረቄ አለ…ደግሞ የሆነ ስራ ስርም አለ አሉ…ደግሞ አዋቂ ዘንድ ሄዶ ማስተበተብ አለ…ምን የሌለን ‘መፍትሄ’ አለ! እኔ የምለው…መፋቂያና ነገርየውን ምን እንደሚያገናኛቸው የመፋቂያውን ጥቅም የሚያብራሩልን ሻጮቹ ብቻ ናቸው የሚያውቁት፡፡ ‘መፋቂያ’ን እንሰማ የነበረው እንደ ‘መስተፋቅር’ ነው እንጂ እንደማይዋጠው ቪያግራ አልነበረም! ቂ…ቂ…ቂ…
እናላችሁ… ‘በስንፈተ ምናምን…’ ብቻ ሳይሆን በሁሉም ነገር አቅም አነሰን፡፡
ባለገንዘቦች፣ ባለጊዜዎች፣ ባለወንበሮች የስሙኒ ኳስ ነገር ሲያደርጉን… “እንዲህ ልታደርጉኝማ አትችሉም!” ለማለት አቅም አነሰን፡፡ “…አገር ይሸፍታል እንኳን ሰው ሲበደል…” የሚለው አትንኩኝ ባይነት ከታሪክነት ወደ አፈ ታሪክነት እየተለወጠ ነው፡፡
የተሰመረላቸውን ድንበር አልፈው፡ በግምጃ ቤትነት ሹመት የንጉሠ ነገሥትነት ስልጣን ሲያሳዩን “እንዲህ የመወሰን ስልጣን የላችሁም…” ለማለት አቅም እያነሰን…መጫወቻ ሆነን ቀረን!
በሁሉም ነገር አቅም የሚጨምር ‘ምስር’ ይላክልንማ!
የፈራንካና የወንበር ‘ጉልቤዎቹ’ በስንት ልፋት ያገኘናቸውን (ቂ…ቂ…ቂ…) እንትናዬዎቻችንን ከዓይናችን ስር ‘ነጥቀው’ ሲወስዱብን…“በህግ አምላክ፣” “ወድቃ በተነሳችው ባንዲራ፣” የማለት አቅም እንኳን አነሰን፡፡ “በአባት አገርና በሚስት የለም ዋዛ…” የሚለው በዘመኑ አገር ያቀና አባባል ቀርቶ…አለ አይደል… አሁን ነገርዬው “ከብት እነዳ በዬ፣ ልጅ አሳድግ ብዬ… ሚስቴን ዳርኩለት እህቴ ናት ብዬ፣” ሆኗል፡፡ አቅመ አነሰና! “አደባለቀውና እርጥቡን ከደረቅ…” አይነት መብት ማስከበር ‘የአባቶች ታሪክ’ ብቻ ሆነኣ!
በሁሉም ነገር አቅም የሚጨምር ‘ምስር’ ይላክልንማ!
…“መብቴንማ ስትንዱ አላይም…” አይነት ነገር…አፍ አውጥቶ መናገር እንኳን እየፈራን ነው፡፡ አቅመ አነሰና! ለ‘ስንፈተ እንትን’ እንደሚሆነው ቪያግራ ከአጠቃላይ አቅመ ቢስነት የሚያወጣን ‘አገር በቀል ምስር እንኳን አጣና! (ቂ…ቂ…ቂ…) ዘንድሮ…አለ አይደል… ካለመናገር ከሚቀር ደጃዝማችነት ይልቅ ነገርዬው “በአፍ ይጠፉ በለፈለፉ…” እየሆነ አቅም አነሰን፡፡
ስሙኝማ…የፈረደባት ሩስያ ነው አሉ፣ ሰውዬው በቀቀኗ፣ ማለት ሰው የሚናገራቸውን ነገሮች ደግማ የምትናገር ወፍ፣ የት ትግባ የት ትሰወርበታለች፡፡ እናላችሁ…ትንፋሽ እያጠረው ኬ.ጂ.ቢ. ቢሮ ይሄዳል፡፡ እዛም ሲደርስ “ተናጋሪ ወፌ ጠፋችብኝ፣” ሲል ያመለክታል፡፡ የኬጂቢ ሰዎችም “ይሄ እኛን አይመለከትም፣ ሄደህ ለፖሊስ አመልክት” ይሉታል፡፡ እሱ ሆዬም “እሺ ለፖሊስ አመለክታለሁ፣ ግን ለእናንተ ልናገር የምፈልገው ነገር አለ፣” ይላል፡፡ እንዲናገርም ይፈቅዱለታል፡፡ እሱም “እዚህ የመጣሁት ተናጋሪ ወፏ በምትናገረው ማንኛውም ነገር እንደማልስማማ ለማሳወቅ ነው፣” ብሎ አረፈላችሁ፡፡
በቀቀን ባይኖረንም… አይደለም የተናገርነው ያሰብነው እንኳን በ‘ሹክ፣ ሹክ’ ጣጣ ያመጣል በሚል “መከበር በከንፈር” እያልን ነው፡፡ አቅም አነሰና!
በሁሉም ነገር አቅም የሚጨምር ‘ምስር’ ይላክልንማ!
መብራት እንዳሰኘ ሲጠፋ “ግብሬን እየከፈልኩ፣ ወርሀዊ ግዴታዬን እየተወጣሁ እንዲህማ ልታደርጉኝ አትችሉም!” ማለት እንኳን እያቃተን ነው፡፡ አቅም አነሰና!
የመሥሪያ ቤት ዘበኛ ያለምንም ምክንያት…አለ አይደል… ስላሰኘው ብቻ “መግባት አይቻልም…” ከማለት አልፎ ቆመጡን ሲወዘውዝብን “ቀጠሮ እያለኝ ማስገባትና ያለማስገባት የአንተ ሀላፊነት አይደለም…” ማለት እንኳን እያቃተን ነው፡፡ አቅም አነሰና!
በሁሉም ነገር አቅም የሚጨምር ‘ምስር’ ይላክልንማ!
እናላችሁ… ባነሰን አቅም የራሳችንን መፍትሄ እንኳን መፈለግ አቅቶናል፡፡ ነገርዬው ‘በምስር ፈንታ ቪያግራ’ ነገር ሆኗል፡፡ ምክንያቱም ምስር የሀበሻ ቪያግራ ነዋ!
እንግዲህ ጨዋታም አይደል… መቼም እንደ ዘንድሮ ለፈረንጅ ‘ጀርባችን የጎበጠበት’ ዘመን የነበረ አይመስለኝም፡፡ ኮሚክ እኮ ነው…እኛስ ሰፊ ህዝቦች ፈረንጅን አይደለም ብቻህን ከእነቤተሰብህና ሚጢጢ ውሾችህ ጋር እንኮኮ ላድርግህ የምንለው ቢሞረሙረን፣ ጉሮሯችን ቢደርቅ ይሆናል፡፡ በኦፊሴል “የእንትን ቱሪስቶች አደነቁን…”  “የስብሰባው ተካፋዮች ነፍስ የሆነች አገር ነች አሉ…”  “የእንትን መንግሥት መቶ ምናምን ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ሊሰጡን ነው…” ምናምን ማለት ሁሉ የሚበዛው ያው ‘ጀርባ ሲጎብጥም’ አይደል! እና ጀርባ ሲጎብጥ ምስርን ትቶ ቪያግራ መቃም ይበዛል፡ ቂ…ቂ…ቂ…
እናላችሁ…እንደ ዓቢይ ብሔራዊ ጉዳይ ሆኖ ቪያግራ ወደ መሠረታዊ ፍላጎትነት ለመለወጥ ሲንፏቀቅ…አለ አይደል… ቪያግራው እንኳን ቀርቶብን በሁሉም በኩል አቅም የሚጨምር ‘ምስር’ ይላክልንማ!
ደህና ሰንብቱልኝማ!

Published in ባህል

አሳታሚዎች፣ መፃሕፍት ሻጮችና መገናኛ ብዙኃን የሚሳተፉበት “ኢትዮ አለም አቀፍ የመፃህፍት አውደ ርዕይ እና የሚዲያ ኤክስፖ” በትላንትናው እለት በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል የተከፈተ ሲሆን ዝግጅቱ እስከ ፊታችን  ሰኞ ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ ታውቋል፡፡
ዝግጅቱ የንባብ ባህል እንዲዳብር፣ የመፃህፍት ገበያ እንዲጎለብት፣ የአሳታሚና የህትመት ኢንዱስትሪው እንዲጠናከር ታልሞ የተሰናዳ እንደሆነ አዘጋጆቹ በላኩት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ “በእውቀትና በመረጃ ለበለፀገ ህብረተሰብ መፃህፍትና ሚዲያ በአንድ ስፍራ” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው አውደ ርዕይና የሚዲያ ኤክስፖ ላይ የተለያዩ አዝናኝ ዝግጅቶች እንደሚቀርቡም ታውቋል፡፡
ትላንትን ጨምሮ ለአምስት ቀናት በሚዘልቀው ዝግጅት ላይ ከ60 በላይ አሳታሚዎች፣ መፃሕፍት ሻጮች፣ የግልና የመንግስት መገናኛ ብዙኃን፣ የጠፉና የማይገኙ መፃሕፍት አቅራቢዎች ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡

“windmills of the Gods” የተሰኘው የእንግሊዛዊው ደራሲ የሲድኒ ሼልደን ልቦለድ መጽሐፍ “የፍቅር ፈተና” በሚል በፋንታሁን ኃይሌ /አስኳል/ ወደ አማርኛ ተተርጉሞ ሰሞኑን ለገበያ ቀረበ። በ302 ገፆች የተቀነበበው ልቦለዱ፤ በ50 ብር ከ70 እየተሸጠ ሲሆን መጽሐፉን የሚያከፋፍለው ብርሃኔ መፃህፍት መደብር ነው፡፡

በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን “የልጆች ፕሮግራም”  ተረት በማቅረብ ህፃናትን ለረጅም አመታት ያዝናኑትና ያስተማሩት እንዲሁም በተዋናይነታቸው የሚታወቁት አርቲስት ተስፋዬ ሳህሉ (አባባ ተስፋዬ) 91ኛ ዓመት የልደት በዓል ዛሬ ከቀኑ 8፡30 ጀምሮ በእቴጌ ጣይቱ ሆቴል እንደሚከበር ተገለፀ፡፡
የአባባ ተስፋዬን የልደት በዓል ያዘጋጁት ቤተሰቦቻቸውና “ልጆች ኢንተርቴይንመንት” ሲሆኑ አርቲስቶች፣ ታዋቂ ሰዎችና ጋዜጠኞች በሚታደሙበት በዚህ የልደት በዓል ላይ የተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚካሄዱ ተጠቁሟል፡፡

1. ጁሊዮ ሴዛር
2. ካይሎር ናቫስ
3. ማኑዌል ኑዌር
4. ጉሌርሞ ኦቾ
5.ቪንሰንት ኢንየማ
6. ቲም ሀዋርድ

ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር በእያንዳንዱ የዓለም ዋንጫ ስድስት ልዩ  ልዩ ሽልማቶችን በተለያዩ ዘርፎ ለሚመረጡ ተጨዋቾች እና ቡድኖች ያበረክታል፡፡  ለምርጥ በረኛ የወርቅ ጓንት፤ ለኮከብ ግብ አግቢ የወርቅ ጫማና ለኮከብ ተጨዋች የወርቅ ኳስ  የሚሰጡት ሶስትይ ሽልማቶች ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ በዓለም ዋንጫ አብይ ስፖንሰርነት የሚታወቀው አዲዳስ የወርቅ ኳስ እና የወርቅ ጫማ ሽልማቶችን በኩባንያው  ስም ያበረክታል፡፡ በሶስቱም ሽልማቶች በተጨማሪ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃ ለሚያገኙት ተጨዋቾች የብር እና የነሐስ  ሽልማቶች ይሰጣሉ፡፡ በዓለም ዋንጫ በሁለተኛ ደረጃ የሚታዩ ሌሎች ሶስት የክብር ሽልማቶችም አሉ፡፡ የዓለም ዋንጫ ምርጥ ተጨዋች፤ የዓለም ዋንጫው ምርጥ ስፖርታዊ ጨዋነት እና የዓለም ዋንጫው ምርጥ ቡድን የሚሸለሙባቸው ናቸው፡፡ የዓለም ዋንጫ ምርጥ ወጣት ተጨዋች ምርጫ ለመጀመርያ ጊዜ የተካሄደው በ1958 እኤአ ቢሆንም በደንበኛ ትኩረት መሸለም የተጀመረው በ2006 እኤአ ላይ ጀርመን ባዘጋጀችው 18ኛው የዓለም ዋንጫ ሲሆን የጀርመኑ ሉካስ ፖዶልስኪ ቀዳሚው ተሸላሚ ነበር፡፡ የዚህ ሽልማት ስፖንሰር የመኪና አምራቹ ሃዩንዳይ ኩባንያ ነው፡፡ በ2010 እኤአ በተደረገው 19ኛው የዓለም ዋንጫ ደግሞ የጀርመኑ ቶማስ ሙለር ተሸልሞበታል፡፡ የዓለም ዋንጫው የስፖርታዊ ጨዋነት አሸናፊን መሸለም የተጀመረው በ1970 እኤአ ላይ ነው፡፡ ከ4 ዓመት በፊት የስፖርታዊ ጨዋነት ሽልማቱን የወሰደው ሻምፒዮኑ የስፔን ብሄራዊ ቡድን ነበር፡፡ የዓለም ዋንጫው ምርጥ ቡድን ደግሞ ከ1994 እኤአ ወዲህ ሲሸለም ቆይቷል፡፡


በጎል ፌሽታው፤ ማን ብዙ አግብቶ ይጨርሳል?
20ኛው ዓለም ዋንጫ በጎሎች ብዛት የምንግዜም ምርጥ በመሆን ላይ ነው፡፡ ከሩብ ፍፃሜ በፊት በተደረጉ 56 ጨዋታዎች 154 ጎሎች ተመዝግበዋል፡፡  በየጨዋታው በአማካይ 2.75 ጎል እየገባ ነው፡፡ በዓለም ዋንጫ 64 ጨዋታዎች መደረግ ከጀመረበት ከ1986 እኤአ ወዲህ ዘንድሮ ከፍተኛው የጎል ብዛት እንደሚመዘገብ ተጠብቋል፡፡ በ1994 እ.ኤ.አ 171፤ በ2002 እ.ኤ.አ 161፤ በ2006 እ.ኤ.አ 147 እንዲሁም በ2010 እ.ኤ.አ 145 ጎሎች በ64 ጨዋታዎች ተመዝግበዋል፡፡ ትናንት ከተጀመሩት ሁለት የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች በፊት የኮከብ ግብ አግቢነቱን ሲመራ የነበረው በ4 ጨዋታዎች አምስት ጎሎች ከመረብ ያዋሃደው የኮሎምቢያው ጀምስ ሮድሪጌዝ ነው። በ4 ጎሎቻቸው የሚከተሉት ደግሞ የአርጀንቲናው ሊዮኔል ሜሲ፤ የጀርመኑ ቶማስ ሙለር እና የብራዚሉ ኔይማር ዳሲልቫ ናቸው፡፡ እያንዳንዳቸው 3 ጎሎች ያስመዘገቡ 5 ተጨዋቾች ናቸው፡፡ ቡድኖቻቸው ወደ ሩብ ፍፃሜ በማለፋቸው በፉክክር የሚቆዩት የሆላንዶቹ ቫንፕርሲ እና ሮበን እንዲሁም የፈረንሳዩ ካሬም ቤንዜማ ናቸው፡፡ የኢኳደሩ ኢነር ቫሌንሽያ እና የስዊዘርላንዱ ሻኪሪ 3 ጎሎች ቢኖራቸውም ቡድኖቻቸው ሩብ ፍፃሜ ባለመድረሳቸው ከፉክክር ውጭ ሆነዋል፡፡ 2 ጎሎች በማስመዝገብ ስማቸው የተመዘገበላቸው 16 ተጨዋቾች ሲሆኑ አንድ ጎል ያገቡት ደግሞ 88 ተጨዋቾች ናቸው፡፡
በዓለም ዋንጫው ኮከብ ግብ አግቢነት ለወርቅ ጫማ ሽልማት የሚበቃው ተጨዋች በጎሎቹ ብዛት የሚመረጥ ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ የጎል ብዛት የሚጨርሱ ተጨዋቾች ከአንድ በላይ ከሆኑ ደግሞ አሸናፊው የሚለየው ለጎል የበቁ ኳሶችን በብዛት ማን አቀብሏል ተብሎ ነው፡፡ በግብ ብዛትና ለጎል የበቁ ኳሶችን በማቀበል እኩል የሆኑ ተጨዋቾች ከሁለት በላይ ከሆኑ ደግሞ አሸናፊነቱ አነስተኛ ደቂቃዎች ተሰልፎ ብዙ ላገባው ተጨዋች የሚሰጥ ይሆናል፡፡
የወርቅ ጫማ አሸናፊ ሽልማት በሁሉም ዓለም ዋንጫዎች ሲሸለም የቆየ ነው፡፡ በ20ኛው ዓለም ዋንጫ ባገባው ጎል አዲስ ታሪክ የሰራው ተጨዋች የ36 ዓመቱ ጀርመናዊ አጥቂ ሚሮስላቭ ክሎሰ ነው፡፡ በዚህ ዓለም ዋንጫ የውድድሩ የምንግዜም ከፍተኛ ጎል አግቢ ሊሆን የሚችልበት እድል ይዞ መሳተፍ የጀመረው ሚሮስላቭ ክሎሰ ከጀርመን ብሄራዊ ቡድን ጋር በተሳተፈባቸው 3 የዓለም ዋንጫዎች 14 ጎሎች ነበሩት፡፡ ጀርመን ከጋና ባደረጉት ጨዋታ ላይ ተቀይሮ ከገባ በኋላ 15ኛውን ጎል አስመዘገበ፡፡  በዚህም የዓለም ዋንጫ የምንግዜም ከፍተኛ ግብ አግቢ  ከነበረው ብራዚላዊው ሊውስ ናዛርዮ ዴሊማ ጋር ክብረወሰኑን ተጋርቷል፡፡ ከሩብ ፍፃሜው በኋላ ሚሮስላቭ ክሎስ አንድ ተጨማሪ ጎል ካስመዘገበ የዓለም ዋንጫ የምንግዜም ከፍተኛ ግብ አግቢ ለመሆን ይችላል፡፡



በረኞች ያልተዘመረላቸው የእግር ኳስ ጀግኖች
20ኛው የዓለም ዋንጫ ላይ  በርካታ ጎሎች ሲመዘገቡ መቆየታቸው የበረኞችን ብቃት አጠያያቂ ቢያደርገውም ቢያንስ ስምንት በረኞች በየቡድኖቻቸው አስገራሚ ብቃት አሳይተዋል፡፡  እነዚህ በረኞች በወሳኝ ጨዋታዎች ያለቀላቸውን የግብ እድሎች ሲያመክኑ፤ ቡድኖቻቸውን በአምበልነት በመምራት የሚደነቅ አስተዋፅኦ ሲያበረክቱ፤ የቡድኖችን ውጤት ለማስጠበቅ ከፍተኛ ጥረት ሲያሳዩ፤ በጥሎ ማለፍ በተከሰቱ የመለያ ምቶችን በማዳን  ውጤቶችን ሲወስኑ ሰንብተዋል፡፡ በእርግጥ በእግር ኳስ ስፖርት  በኮከብ ተጨዋችነት ብዙውን ጊዜ  ለአጥቂዎች እና ለአማካዮች ትኩረት የሚሰጥ ቢሆንም ፤ በዚህ ዓለም ዋንጫ በረኞች  በምርጥ አቋማቸው ለቡድናቸው የኮከብነት ሚና እንደሚኖራቸው ተረጋግጧል፡፡ በርካታ ስፖርት አፍቃሪዎች ከበረኞች ስህተት የመጠበቅ ልማድ አለባቸው፡፡ በየጨዋታው በረኞችን አንድ ስህተት ሲያጋጥማቸው ወይም ጎል ሲገባባቸው ለቡድናቸው ሽንፈት ተጠያቂ ያደርጓቸዋል፡፡   አጥቂዎች ብዙ ጎሎችን ሲስቱ የሚደርስባቸው ወቀሳ ግን ያን ያህል ነው። ለበረኞች ሚና አነስተኛ ትኩረት እንደሚሰጥ በብራዚላዊው ጁሊዮ ሴዛር ላይ የተከሰተውን ሁኔታ እንደ ማስረጃ መጥቀስ ይቻላል፡፡ በብራዚል ለግብ ጠባቂዎች ብዙም አድናቆት የለም፤ እንደውም አንዳንድ ስፖርት አፍቃሪዎች ጁሊዮ ሴዛርን “ዶሮው ሰውዬ” እያሉ ያሾፉበታል፡፡ ብራዚል በጥሎ ማለፍ ከቺሊ ጋር ባደረገችው ጨዋታ ላይ ግን አዘጋጇን አገር ከውድቀት ያዳነው እሱ ነበር፡፡ ከብራዚልና ቺሊ ጥሎ የሚያልፈው ቡድን በመለያ ምቶች ሲታወቅ ሁለት ኢሊጎሬዎችን በማዳን ጁሊዮ ሴዛር የእለቱ ኮከብ ነበር፡፡ በዚህ ጀግንነቱም ከሌሎች ምርጥ ተጨዋቾች ይልቅ ትኩረት ተሰጥቶት ተደጋጋሚ ቃለምልልሶች አድርጓል፡፡  “በፊት የሚያናግረኝ አልነበረም፤ አሁን  ሁሉም አስተያየቴን ስለሚጠይቅ በጣም ደስ ብሎኛል” በማለት ጁሊዮ ሴዛር እያነባ ተናግሯል፡፡
በ20ኛው ዓለም ዋንጫ የታየ ምርጥ በረኛ የብራዚሉ ጁሊዮ ሴዛር ብቻ አይደለም፡፡  ቡድኖቻቸውን ለሩብ ፍፃሜ በማብቃት ጉልህ ሚና ከነበራቸው ምርጥ በረኞች የቤልጅዬሙ ቲቦልት ኮርትዬስ፤ የኮስታሪካው ኬዬሎር ናቫስ፤ የኮሎምቢያው ዴቪድ ኦስፒና፤ የአርጀንቲናው ሰርጂዮ ሮሜሮ፤ የፈረንሳዩ ሁጎ ሎሪስና የጀርመኑ ማንዌል ኑዌር ዋናዎቹ ተጠቃሾች ናቸው።  ከምድብ ጨዋታዎች እስከ ጥሎ ማለፉ  ቡድኖቻቸውን በአስገራሚ ብቃታቸው ያገለገሉ ሌሎችም ምርጥ በረኞች ነበሩ፡፡ የአሜሪካው ቲም ሃዋርድ፤ የናይጄርያው ቪንሰንት ኢኒዬማ እንዲሁም  የቺሊው  ጉሌርሞ ኦቾ  ናቸው፡፡ የዓለም ዋንጫ ኮከብ በረኛ ሆኖ የወርቅ ጓንት ለመሸለም የሚበቃው ከእነዚህ ምርጥ ግብ ጠባቂዎች አንዱ መሆኑ አይቀርም፡፡ በምድብ ማጣርያው በ3 ጨዋታዎች ግብ ሳይገባበት አንደኛ ደረጃ የተሰጠው የፈረንሳዩ ሁጎ ሎሪስ ነው፡፡ የ22 ዓመቱ የቤልጅዬም በረኛ ቲቦልት ኮርትዬስ  ወደ ጎል ከሚሞከሩ ኳሶች 87 በመቶውን  በማዳን ተደንቋል፡፡ የጀርመኑ ማኑዌል ኑዌር ደግሞ በዓለም ዋንጫው  ፍፁም ቅጣት ምት በማዳን 29 በመቶ ብቃት አስመዝግቧል፡፡ ማኑዌል ኑዌር ከሌሎቹ ምርጥ በረኞች ልዩ የሚያደርገው  ከግብ ክልል ውጭ እንቅስቃሴ በማድረግ  እንደሊብሮ ተጨዋች ማገልገሉ ነው፡፡ ይህ የማንዌል ኑዌር ብቃት በተለይ ጀርመንና አልጄርያ ባደረጉት ጨዋታ  የታየ ነበር፡፡
የአሜሪካው ግብ ጠባቂ ቲም ሃዋርድ አገሩ ከቤልጅዬም ጋር ባደረገችው ጨዋታ 15 ያለቀላቸው የግብ ሙከራዎችን አድኖ በውድድሩ ታሪክ አዲስ ክበረወሰን ተመዝግቦለታል፡፡ ከ4 ዓመት በፊት ደቡብ አፍሪካ ባስተናገደችው ኛው የዓለም ዋንጫ በረኞች የአዲዳስ ምርት በሆነችው ጃቡላኒ የተባለች ኳስ ምርጥ ብቃታቸውን ለማሳየት አልታደሉም ነበር፡፡ ዘንድሮ ግን በብራዙካ ኳስ አንድም በረኛ ሲቸገር አልታየም፡፡
የፊፋ ቴክኒክ ቡድን የዓለም ዋንጫውን ኮከብ በረኛ በውድድሩ ላይ ባሳየው አጠቃላይ ብቃት መሰረት መርጦ ለሽልማት ያበቃዋል፡፡ የዓለም ዋንጫ ምርጥ በረኛ ከ1994 እኤአ ወዲህ በታዋቂው ራሽያዊ ግብ ጠባቂ ሌቭ ያሺን መታሰቢያነት የሚሸለም ነበር፡፡ ከ2010 እኤአ በኋላ ግን የወርቅ ጓንት ሽልማት ተብሎ ለአሸናፊው መበርከት ጀምሯል፡፡


በ1ኛው ዓለም ዋንጫ የኡራጋዩ ኢነሪኬ ባሌስትሮ
በ2ኛው የዓለም ዋንጫ የስፔኑ ሪካርዶ ዛሞራ
በ3ኛው የዓለም ዋንጫ የኡራጋዩ ሮክዌ ማስፖሊ
በ4ኛው የዓለም ዋንጫ የቼኮስላቫኪያው ፍራንቲሴክ ፕላኒካ
በ5ኛው የዓለም ዋንጫየሃንጋሪው ጉዮላ ግሮሲክስ
በ6ኛው የዓለም ዋንጫ  የሰሜን አየርላንዱ ሃሪ ግሬግ
በ7ኛው የዓለም ዋንጫ የቼኮስላቫኪያው ቪሊያም ሽኮሪጄፍ
በ8ኛው የዓለም ዋንጫ የእንግሊዙ ጎርደን ባንክስ
በ9ኛው የዓለም ዋንጫ የኡራጋዩ ላዲሳሎ ማዙሪኪኤውሲዝ
በ10ኛው የዓለም ዋንጫ የምዕራብ ጀርመኑ ሴፕ ማዬር
በ11ኛው የዓለም ዋንጫ የአርጀንቲናው ኡባልዶ ፊሎል
በ12ኛው የዓለም ዋንጫ የጣሊያኑ ዲኖ ዞፍ
በ13ኛው የዓለም ዋንጫነየቤልጅዬሙ ጂን ማርዬ ፕፋፍ
በ14ኛው የዓለም ዋንጫ የኮስታሪካው ሊውስ ጋቤሎና የአርጀንቲናው ሰርጂዮ ጎይኮቻ
በ15ኛው የዓለም ዋንጫ የቤልጅዬሙ ሚሸል ፕሩድሜ
በ16ኛው የዓለም ዋንጫ የፈረንሳዩ ፋብያን ባርቴዝ
በ17ኛው የዓለም ዋንጫ የጀርመኑ ኦሊቨር ካን
በ18ኛው የዓለም ዋንጫ የጣሊያኑ ጂያንሉጂ ቡፎን
በ19ኛው የዓለም ዋንጫ የስፔኑ ኤከር ካስያስ
በጎል ፌሽታው፤ ማን ብዙ አግብቶ ይጨርሳል?
20ኛው ዓለም ዋንጫ በጎሎች ብዛት የምንግዜም ምርጥ በመሆን ላይ ነው፡፡ ከሩብ ፍፃሜ በፊት በተደረጉ 56 ጨዋታዎች 154 ጎሎች ተመዝግበዋል፡፡  በየጨዋታው በአማካይ 2.75 ጎል እየገባ ነው፡፡ በዓለም ዋንጫ 64 ጨዋታዎች መደረግ ከጀመረበት ከ1986 እኤአ ወዲህ ዘንድሮ ከፍተኛው የጎል ብዛት እንደሚመዘገብ ተጠብቋል፡፡ በ1994 እ.ኤ.አ 171፤ በ2002 እ.ኤ.አ 161፤ በ2006 እ.ኤ.አ 147 እንዲሁም በ2010 እ.ኤ.አ 145 ጎሎች በ64 ጨዋታዎች ተመዝግበዋል፡፡ ትናንት ከተጀመሩት ሁለት የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች በፊት የኮከብ ግብ አግቢነቱን ሲመራ የነበረው በ4 ጨዋታዎች አምስት ጎሎች ከመረብ ያዋሃደው የኮሎምቢያው ጀምስ ሮድሪጌዝ ነው። በ4 ጎሎቻቸው የሚከተሉት ደግሞ የአርጀንቲናው ሊዮኔል
በ1ኛው ዓለም ዋንጫ  በ8 ጎሎች የኡራጋዩ ጉሌርሞ ስታብል
በ2ኛው የዓለም ዋንጫ በ5 ጎሎች የቼኮስሎቫኪያው ኦሊድሪች
በ3ኛው የዓለም ዋንጫ በ7 ጎሎች የብራዚሉ ሊዮኒዴስ
በ4ኛው የዓለም ዋንጫ በ8 ጎሎች የብራዚሉ አዴሚር
በ5ኛው የዓለም ዋንጫ በ11 ጎሎች የሃንጋሪው ሳንዶር ኮሲስ
በ6ኛው የዓለም ዋንጫ በ13 ጎሎች የፈረንሳዩ ጀስት ፎንታይኔ
በ7ኛው የዓለም ዋንጫ በእኩል 4 ጎሎች የብራዚሎቹ ጋሪንቻና ቫቫ፤ የዩጎስላቪያው ድራዛን ጄርኮቪች እና የቺሊ ሊዮኔል ሳንቼዝ
በ8ኛው የዓለም ዋንጫ በ9 ጎሎች የፖርቱጋሉ ዩዞብዮ
በ9ኛው የዓለም ዋንጫ በ10 ጎሎች የጀርመኑ ገርድ ሙለር
በ10ኛው የዓለም ዋንጫ በ7 ጎሎች የፖላንዱ ግሬጎርዝ ላቶ
በ11ኛው የዓለም ዋንጫ በ6 ጎሎች የአርጀንቲናው ማርዮ ኬምፐስ
በ12ኛው የዓለም ዋንጫ በ6 ጎሎች የጣሊያኑ ፓውሎ ሮሲ
በ13ኛው የዓለም ዋንጫ በ6 ጎሎች የእንግሊዙ ጋሪ ሊንከር
በ14ኛው በ6 ጎሎች የጣሊያኑ ሳልቫቶሪ ስኪላቺ
በ15ኛው የዓለም ዋንጫ በ6 ጎሎች የሩስያው ሳሌንኮና የቡልጋሪያው ስቶችኮቭ
በ16ኛው የዓለም ዋንጫ በ6 ጎሎች የክሮሽያው ዳቮር ሱከር
በ17ኛው የዓለም ዋንጫ በ8 ጎሎች የብራዚሉ ሮናልዶ
በ18ኛው የዓለም ዋንጫ በ5 ጎሎች የጀርመኑ ሚሮስላቭ ክሎሰ
በ19ኛው የዓለም ዋንጫ በ5 ጎሎች የጀርመኑ ቶማስ ሙለር

ኮከብ ተጨዋች ከዋንጫው አሸናፊ ይገኛል
የዓለም ዋንጫው ኮከብ ተጨዋች ለማወቅ እስከ ዋንጫው ጨዋታ መጠበቅ ይጠይቃል፡፡ ከሩብ ፍፃሜው በፊት ለዚህ ሽልማት እጩ ተፎካካሪ እንደሚሆኑ የተነገረላቸው በምርጥ ጎሎቻቸው የተደነቁት የሆላንዱ ቫን ፒርሲ እና የኮሎምቢያው ጄምስ ሮድሪጌዝ ናቸው፡፡ የብራዚሉ ኔይማርና የአርጀንቲናው ሊዮኔል ሜሲ ቡድኖቻቸውን ለዋንጫ የሚያበቁ ከሆነም ለሽልማቱ ግንባር ቀደም እጩዎች ይሆናሉ፡፡ የዓለም ዋንጫ ኮከብ ተጨዋች የሚሸለመው የወርቅ ኳስ ሲሆን ምርጫውን የሚያከናውኑት ዓለም አቀፍ ጋዜጠኞች እና ፊፋ ናቸው፡፡

በ1ኛው ዓለም ዋንጫ የኡራጋዩ ጆሴ ናሳዚ
በ2ኛው የዓለም ዋንጫ የጣሊያኑ ጁሴፔ ሜዛ
በ3ኛው የዓለም ዋንጫ የብራዚሉ ሊዮኒዴስ
በ4ኛው የዓለም ዋንጫ የብራዚሉ ዚዝንሆ
በ5ኛው የዓለም ዋንጫ የሃንጋሪው ፌርኔክ ፑሽካሽ
በ6ኛው የዓለም ዋንጫ የብራዚሉ ዲዲ
በ7ኛው የዓለም ዋንጫ የብራዚሉ ጋሪንቻ
በ8ኛው የዓለም ዋንጫ የእንግሊዙ ቦቢ ቻርልተን
በ9ኛው የዓለም ዋንጫ የብራዚሉ ፔሌ
በ10ኛው የሆላንዱ ዮሃን ክሩፍ
በ11ኛው የአርጀንቲናው ማርዮ ኬምፐስ
በ12ኛው የጣሊያኑ ፓውሎ ሮሲ
በ13ኛው የአርጀንቲናው ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና
በ14ኛው የጣሊያኑ ሳልቫቶሬ ስኪላቺ
በ15ኛው የብራዚሉ ሮማርዮ
በ16ኛው የዓለም ዋንጫ የብራዚሉ ሮማርዮ
በ17ኛው የጀርመኑ ኦሊቨር ካን
በ18ኛው የፈረንሳዩ ዚነዲን ዚዳን
በ19ኛው የኡራጋዩ ዲያጎ ፎርላን

ታዋቂው የፒያኖ ተጫዋችና የሙዚቃ ቀማሪ ግርማ ይፍራሸዋ ‘ላቭ ኤንድ ፒስ’ የሚል ርዕስ ያለውን አዲስ የፒያኖ ሙዚቃ አልበሙን በዚህ ወር መጨረሻ አሜሪካ ውስጥ በሚያቀርበው ኮንሰርት ያስመርቃል፡፡
በሜሪላንድ ቤተሳዳ ውስጥ በሚገኘው ‘ቤተሰዳ ብሉዝ ኤንድ ጃዝ ሱፐር ክለብ’ በሚከናወን ስነስርዓት የሚመረቀው አልበሙ፣ ቀረጻ ባለፈው አመት ኒውዮርክ ብሮክሊን ውስጥ መጠናቀቁን የዘገበው ታዲያስ መጽሄት፤ አልበሙን ለገበያ ያቀረበው ‘አንሲን ሪከርድስ’ የተባለው ታዋቂ የሙዚቃ አሳታሚ ኩባንያ መሆኑን ገልጿል፡፡
‘አምባሰል’፣ ‘ጨዋታ’፣ ‘ሰመመን’ና ‘እልልታ’ን ከመሳሰሉ በአገርኛ የሙዚቃ ስልቶች የተቀመሩ የሙዚቀኛውን ወጥ ስራዎች በያዘው በዚህ አልበም፤ በታዋቂው ኢትዮጵያዊ የሙዚቃ ሰው በፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ የተደረሰው ‘ባለ ዋሽንቱ እረኛ’ የተባለ ተወዳጅ ሙዚቃ በግርማ እንደገና ተሰርቶ እንደተካተተበት ተነግሯል፡፡
በቡልጋሪያ፣ በለንደን ሮያል የሙዚቃ አካዳሚና ጀርመን ውስጥ በሚገኘው ሌፕዚግ የሙዚቃና የቲያትር ተቋም ትምህርቱን የተከታተለው ግርማ ይፍራሸዋ፤ በተለያዩ የአለም አገራት በተዘጋጁ ኮንሰርቶች የሙዚቃ ስራዎቹን በማቅረብ የሚታወቅ ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓትም የኢትዮጵያንና የክላሲካል ሙዚቃን ለማስተዋወቅ በአፍሪካና በአውሮፓ አገራት እየተዘዋወረ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ተዘግቧል፡፡

Published in ጥበብ
Saturday, 05 July 2014 00:00

የፖለቲካ ጥግ

(ስለዲፕሎማት)
ዲፕሎማት ማለት ሁልጊዜ የሴትን የልደት ቀን የሚያስታውስ ነገር ግን ዕድሜዋ ትዝ የማይለው ሰው ማለት ነው፡፡
ሮበርት ፍሮስት
(አሜሪካዊ ገጣሚ)
በዚህ ዘመን ዲፕሎማት ሌላ ሳይሆን አልፎ አልፎ መቀመጥ የተፈቀደለት የአስተናጋጆች አለቃ ማለት ነው፡፡
ፒተር ዪስቲኖቭ
(እንግሊዛዊ ተዋናይ፣ ዳይሬክተርና ፀሃፊ)
እውነተኛ ዲፕሎማት የሚባለው የጎረቤቱን ጉሮሮ ጎረቤቱ ሳያውቅ መቁረጥ የሚችል ነው፡፡
ትሪግቭ ላይ
(ኖርዌጃዊ ፖለቲከኛ)
አምባሳደር ለአገሩ ጥቅም እንዲዋሽ ወደ ውጭ አገር የሚላክ ሃቀኛ ሰው ነው፡፡
ሄነሪ ዎቶን
(እንግሊዛዊ ገጣሚና ዲፕሎማት)
እኔ እንደሃኪም ነኝ፡፡ በሽተኛው ክኒኖቹን በሙሉ መውሰድ ካልፈለገ የራሱ ውሳኔ እንደሆነ እነግረዋለሁ፡፡ ነገር ግን በቀጣዩ ጊዜ በቀዶ ህክምና ባለሙያነቴ ቢላዬን ይዤ እንደምመጣ ማስጠንቀቅ አለብኝ፡፡
ዣቬር ፔሬዝዲ ሱላር
(የፔሩ ዲፕሎማት)
ውጭ አገር ስትሆን ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊ ነህ፤ አገር ቤት ግን ፖለቲከኛ ብቻ ነህ።
ሃሮልድ ማክሚላን
(እንግሊዛዊ ጠ/ሚኒስትር)
ከፍርሃት የተነሳ ድርድር ውስጥ መግባት የለብንም፤ ነገር ግን ድርድርን ፈፅሞ ልንፈራ አይገባም፡፡
ጆን ፊትዝጌራልድ ኬኔዲ
(የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት)
አንዳንድ ጥያቄዎቻችሁን እመልስላችኋለሁ። በጣም አስቸጋሪዎቹን ደግሞ የሥራ ባልደረቦቼ ይመስላችኋል፡፡
ሮላንድ ስሚዝ
(እንግሊዛዊ የቢዝነስ ኃላፊ፤ በብሪቲሽ ኤሮስፔስ
 ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የተናገሩት)
ወጣቶች ከሚሞቱ በዕድሜ የገፉ ዲፕሎማቶች ቢሰላቹ ይሻላል፡፡
ዋረን ሮቢንሰን አውስቲን
(አሜሪካዊ ዲፕሎማት፤ በተባበሩት መንግስታት
ድርጅት በተካሄደው ሰረዥም ውይይት ተሰላችተው እንደሆነ ሲጠየቁ የመለሱት)

Page 16 of 16