Saturday, 20 June 2015 12:31

የWATCH ፕሮጀክት ተጠናቀቀ

  በእናቶችና ህፃናት ጤና እንክብካቤ ላይ አተኩሮ ላለፉት 42 ወራት በአማራ፣ በኦሮሚያና በደቡብ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች ሲንቀሳቀስ የነበረውና WATCH (Women and their Children Health) የተባለው ፕሮጀክት ተጠናቀቀ፡፡
በካናዳ መንግስት ድጋፍ በፕላን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያና በኢትዮጵያ የፅንስና ማህፀን ሐኪሞች ማህበር የጋራ ትብብር ሲተገበር የቆየውን የዚህኑ ፕሮጀክት መጠናቀቅ አስመልክቶ በጁፒተር ሆቴል በተዘጋጀ ፕሮግራም ላይ የፕላን ኢንተርናሽናል ሲኒየር ማኔጀር የፕሮጀክቱ ኃላፊ ወ/ሮ አይናለም አሸብር እንደተናገሩት፤ ፕሮጀክቱ በሶስቱ የአገሪቱ ክልሎች ማለትም በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል በሲዳማ ዞን ሸበዲኖ፣ ጐርቼና ቦና ዙሪያ፣ በኦሮሚያ ክልል በጅማ ዞን ቀርሳ ወረዳና ጢሮ አፍታ ወረዳዎች እንዲሁም በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን በመቂት፣ ላስታና ቡግና ወረዳዎች ላይ ላለፉት 3 ዓመታት ከስድስት ወራት ሲንቀሳቀስ ቆይቷል፡፡ ፕሮጀክቱ በእናቶችና ልጆቻቸው ጤና እንክብካቤ በተለይም እርጉዝ እናቶች በእርግዝና፣ በወሊድና ከወሊድ በኋላ የሚያጋጥማቸውን ችግር ለመቅረፍ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ አተኩሮ የሚሰራ ፕሮጀክት ነው፡፡ ፕሮጀክቱ ፍላጐትና አቅርቦትን ባጣጣመ መልኩ የእናቶችና ልጆቻቸውን ጤና በመንከባከብ ተግባር ላይ አተኩሮ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን የተናገሩት ወ/ሮ አይናለም፤ የፕሮጀክቱ መጠናቀቂያ ጊዜ በመድረሱ ምክንያት ከወረዳዎቹ መውጣቱን ጠቁመው ወደፊት ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ ሌሎች ፕሮጀክቶች እንደሚኖሩም ገልፀዋል፡፡

Published in ዋናው ጤና

ባለፈው ሳምንት በሚሊኒየም አዳራሽ በተካሄደው 3ኛው ሆቴል ሾው ኢትዮጵያ 2007 ከተሳተፉት 145 ኩባንያዎች የኢጣሊያዊው የቢዝነስ ፕሮሞሽንና ኤክስፖርት ኖቫ ኮንሰልቲንግ አንዱ ነበር፡፡ የኖቫ ኮንሰልቲንግ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሚ/ር ፋብዮ ሳንቶኒ ለኢትዮጵያ አዲስ አይደሉም - ከ15 ዓመት በፊት ነው የሚያውቋት፡፡ ለአቃቂ ጨርቃ ጨርቅ፣ ለጅማ፣ ለባህርዳር፣ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲዎችና ለአንዳንድ የግል ድርጅቶች መሳሪያዎች ያቀርቡ ስለነበር ኢትዮጵያን በደንብ እንደሚያውቋት ይናገራሉ፡፡
ሚ/ር ሳንቶኒ፣ በአሁኑ ወቅት ሥራቸው የኢጣሊያ ኢንቨስተሮች በአፍሪካ በካሜሩንና በኢትዮጵያ ኢንቬስት እንዲያደርጉ ማግባባት እንደሆነ በሚሊኒየም አዳራሽ ከጋዜጠኞች ጋር ባደረጉት ውይይት ገልጸዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በጣም ተለውጣለች ያሉት ሚ/ር ሳንቶኒ፤ “ኢትዮጵያ ከየትኛውም የአፍሪካ አገር ለኢንቬስትመንት በጣም ምቹና ተስማሚ ከመሆኗም በላይ በጥሩ እድገት ላይ ትገኛለች፡፡ የኢጣሊያ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ኢንቬስት ለማድረግ ፈልገዋል፡፡ እኛ መሥራት የምንፈልገው ከመካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ጋር ነው፡፡ ኢንተርፕራይዞቹ የእኛን ቴክኖሎጂ፣ ገንዘብ፣ እውቀት፣ ገበያ፣ ይጠቀማሉ፡፡ የእኛ ባለሀብቶች የአገሪቷን ገበያ ይጠቀማሉ፡፡ ሁለቱ አገሮች በጋራ የ50፣50 ተጠቃሚነት ዕድገታቸው ተቀራራቢ ይሆናል፡፡ የሕዝቦችም ታሪካዊ ግንኙነት ይጠናከራል” ብለዋል፡፡
ማኔጂንግ ዳይሬክተሩ በኢትዮጵያ ኢንቬስት እንዲያደርጉ ይዘው የመጡት 72 የኢጣሊያ ኩባንያዎች ሲሆኑ የኩባንያዎቹ ፍላጐት ሆቴል ወይም በሌላ ኢንዱስትሪ ግንባታ ሳይሆን ኢትዮጵያውያኑን በእውቀትና ልምዳቸው በሆቴል፣ በሪዞርት፣ በመሳሪያ አቅርቦት፣ ዲዛይንና አርክቴክቸር፣ የአዋጭነት ጥናት፣ በሆቴል ማኔጅመንት (አመራር) ሆቴልና ሪዞርቶች ዓለምአቀፍ ደረጃ እንዲኖራቸው ማድረግ ነው፡፡ ሌሎች ደግሞ በመስኮትና በር፣ በጣሪያ ክዳንና በሶፋ አቅርቦት መሳተፍ ሲፈልጉ አንዳንዶች ደግሞ በስብሰባና ሲኒማ ቤት አዳራሾች ግንባታ የማማከር እውቀት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡
አሁን በአገሪቷ የሚታየው ዕድገት ጥሩ ቢሆንም የበለጠ የሀብቷ ተጠቃሚ ሆና ዕድገቷ እንዳይፋጠን የሚያደርጉ ፈታኝ ችግር ቀፍድዶ እንደያዛት አልደበቁም፡፡ በእኔ አስተያየት ይላሉ ሚ/ር ሳንቶኒ፤ ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አገሮች ከፍተኛ እምቅ ሀብት አላት፡፡ እንዲያውም ከደቡብ አፍሪካ የበለጠ የቱሪዝም ሀብት እንዳላት አምናለሁ፡፡ ችግሩ፣ ግን ብዙ ኢትዮጵያውያን እኔ የበለጠ አዲስ ነገር መፍጠር እፈልጋለሁ ብሎ ሲተጋ አይታይም፡፡ የአገልግሎት አሰጣጤን፣ የሆቴልን፣ የምርቴን፣ የጥራት ደረጃ ወደላቀ ደረጃ አደርሳለሁ አይሉም ብለዋል፡፡
ሌላው ከፍተኛ ችግር የአገሪቷ ዕድገት በአዲስ አበባ ብቻ መሆኑ ወይም ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ላይ መከተሟ ነው፡፡ በአገሪቷ የተመጣጣነ የዕድገት ደረጃ የለም፡፡ ይህ ደግሞ ከፍተኛ ችግር አለው። አክሱም፣ ላሊበላ ወይም ጐንደር ስንሄድ ዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው ሆቴል ማግኘት በጣም ከባድ ነው፡፡ ይህ ሁኔታ አገሪቷ ከቱሪዝም የምታገኘውን ገቢ በእጅጉ እየተፈታተነ ነው፡፡ ከአንዳንድ የታሪክ ሰዎች ጋር ስንወያይ “ታሪክ ሲባል በተጀመረበት ሁኔታ መቆም (መቆየት) አለበት” ይላሉ፡፡ ነገር ግን እውነታው እንደዚያ አይደለም፡፡ ዓለም በእያንዳንዱ ደቂቃ በለውጥ ጐዳና እየተንደረደረች፣ እየሮጠች፣ እየተለወጠች፣ እያደገችና እየተመነደገች ነው፡፡ ኢትዮጵያም እርምጃዋን ከዓለም ጋር ማስተካከልና መለወጥ አለባት፡፡
ለለውጥና ዕድገት ያለመፍጠን በቱሪዝም ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በሌሎችም የሚታይ ነው፡፡ አነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች የሉም ማለት ይቻላል። ጥቂት ቢኖሩም ከቁጥር የሚገቡ አይደሉም፡፡ አንድ ምሳሌ ልጠቀስ፡፡ አገሪቷ ማንጐ አብቃይ ሆና ጥሬ ዕቃው በእጃቸው እያለ በአግሮ ኢንዱስትሪ ማቀነባበር ሥራ የተሰማሩ ድርጅቶች የሉም ማለት ይቻላል፡፡ ለእኔ ይኼ ሞኝነት ነው፡፡ ስለዚህ ኢትዮጵያውያን ለሥራ ያላቸው ግንዛቤ መለወጥ አለበት፡፡ ሥራ ማለት ወደ ቢዝነስ መግባትና ያፈሩትን ምርት ወይም ያዘጋጁትን አገልግሎት የሚገዛ ደንበኛ ማፍራት ነው፡፡
በቢዝነስ ዓለም ዋናው አስፈላጊ ነገር ቢዝነስ ፕላን ነው፡፡ የቢዝነስ ሰው የፈጠራ ሰው (ኢንተርፕሪነር) መሆን አለበት፡፡ አንድ ሰው ገንዘብ ስላለው ብቻ ዝም ብሎ ቢዝነስ መጀመር የለበትም፡፡ ፈጠራ ሲባል አዲስ ነገር መፈልሰፍ ብቻ አይደለም። ቢዝነስ ከመጀመር በፊት ያለኝ ገንዘብ ምን ሊያሠራኝ ይችላል? እዚህ አካባቢ ምን ብጀምር ነው የሚያዋጣኝ? ሕዝቡ በጣም የሚፈልገው ነገር ምንድነው? የመግዛት አቅሙስ? ጥሬ ዕቃውስ እንዴት ነው በቀላል ማግኘት የሚቻለው?... ብሎ ማጥናት የሚችልበት እውቀት ሊኖረው ይገባል፡፡
ስለዚህ አዲስ ኢንተርፕሪነሮች በጥናት ላይ የተመሠረተ እውነተኛ ቢዝነስ ፕላን ማዘጋጀት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ያለ ጥናት ዝም ብሎ የሚጀመር ቢዝነስ ብዙ ጊዜ ውጤቱ መጥፎ ሊሆን ይችላል - ትርፍ ጠብቆ ኪሳራ ማፈስ እንዳይሆን፡፡
አንድ ዋነኛ ነጥብ ደግሞ ቢዝነስ የግድ ከትልቅ ወይም ከፍ ካለ ደረጃ መጀመር የለበትም ይላሉ ሚ/ር ሳንቶኒ፡፡ የብዙ ኢትዮጵያውያን አስተሳሰብ ሼክ ሙሐሙድ አሊ አላሙዲንን መሆንና እሳቸው እንደሠሩት ትልቅ ነገር ሥራት ነው፡፡ እንደዚያ መሆን የለበትም፡፡ በትንሽ ቢዝነስ ጀምረው የራሳቸውን ገበያና ደንበኛ በማፍራት በሂደት ደረጃ በደረጃ፣ የሥራ አመራር ክህሎት በማዳበር፣ የምርትና አገልግሎትን ጥራት በማሳደግ ማደግና ካሰቡት ደረጃ መድረስ ይቻላል፡፡ በአገሬ ቢዝነስ የሚሠራው እንደዚህ ነው፡፡ አባት ትንሽ ቢዝነስ ይጀምራል፡፡ ሲደክመው ልጅ ይረከባል፣ ከዚያም ትልቅ የቤተሰብ ቢዝነስ ይሆናል በማለት ገልፀዋል፡፡
የስኬት ሁነኛው ቁልፍ ጥራት ቢሆንም አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ለጥራት ቦታ (ግምት) እንደማይሰጥ ይናገራሉ፡፡ ጥራት ሲባል ብዙ መለኪያዎች አሉት ያሉት ማኔጂንግ ዳይሬክተሩ፣ እኔ ወደ አንድ ሆቴል ስገባ ደንበኛ ወይም ተገልጋይ ነኝ፡፡ ደንበኛ ደግሞ ንጉሥ ስለሆነ ከሆቴሉ አስተናጋጆች የንጉሥ መስተንግዶ እጠብቃለሁ፡፡ ይህን መስተንግዶ ማግኘት ያለብኝ መኝታ ክፍል ስጠይቅ ብቻ አይደለም፡፡  በሁሉም የሆቴሉ አገልግሎት መስጫዎች፣ ባር፣ ሬስቶራንት፣ የመኝታ ክፍል…ሁሉ የተሟላ አገልግሎት ማግኘት አለብኝ። ክፍሌ ውስጥ የሚያስፈልጉኝ ነገሮች ሁሉ ውሃ፣ መብራት፣ ስልክ፣ ፍሪጅ፣ ቲቪ፣ ንፁህ አንሶላና ፎጣ፣ ንፁህና ጣፋጭ ምግብ፣ ማግኘት የሆቴሉን ጥራት ያመለክታል፡፡
አስተናጋጆችም ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃ ያለው መስተንግዶ መስጠት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ ጥሩ ሥልጠና ሊሰጣቸው ይገባል። ወደ ሆቴሉ የሚመጡት የተለያየ አገር ዜግነት ያላቸው እንግዶች ናቸው፡፡
የአሜሪካ የጣሊያን፣ የፈረንሳይ፣ የጀርመን፣… ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ የየአገሩ እንግዳ ወይም ቱሪስት የሚፈለገው ዓይነት አገልግሎትና አቀባበል የተለያየ ነው፤ ስለዚህ አንድ እንግዳ ሲመጣ የየት አገር ዜጋ እንደሆነ ለይቶ የሚፈልገውን ዓይነት አገልግሎት መስጠት ነው ጥራት ማለት፤ ለጀርመኑ ቱሪስት የሚደረገው አቀባበልና የምግብ ዝግጅት ለአሜሪካዊው አይመቸውም፡፡
ለኢጣሊያው የሚዘጋጀው ምግብና የሚደረግለት መስተንግዶ ለፈረንሳዩ፣ ለአረቡ፣ ለጃፓኑ፣ ለቻይናው፣ አይስማማም፡፡ ፈረንጅ ሁሉ አንድ ነው በማለት አንድ ዓይነት ምግብ አዘጋጅቶ ማቅረብ ትክክል አይደለም፡፡
በአገሩ የለመደውና የሚወደው የምግብ አይነት ነው መዘጋጀት ያለበት በማለት የጥራትን ፅንሰ - ሐሳብ አስረድተዋል፡፡

በአገር ውስጥ ባለሀብት በአቶ አዲስ ገሠሠና በሆላንዳዊው ባለሀብት በሚ/ር ሚሪያም ቫን አልፈን በአክሲዮን በዱከም ከተማ ኢንዱስትሪ ዞን በ2.5 ሚሊዮን ዶላር ያቋቋሙት ቢ ኮኔክትድ ፕሪንቲንግና ቢ ኮኔክትድ ሌብሊንግ የተባሉ ፋብሪካዎች ሰሞኑን ተመረቁ፡፡
ፋብሪካዎቹን የመረቁት የኢንዱስትሪ ሚ/ር ዴኤታ ዶ/ር መብራህቱ መለስ፣ ፋብሪካዎቹ በኢትዮጵያ በዓይነታቸው የመጀመሪያ እንደሆኑ ጠቅሰው ሁሉም የአገር ውስጥ የጨርቃጨርቅ ፋብሪካዎች በምርት ሰንሰለት ሂደት የጎደላቸውን ፕሪንትና ሌብል በማድረግ እሴት ጨምረው ኤክስፖርት የሚያደርጉትን መጠን እንዲጨምሩ ይረዳቸዋል ብለዋል፡፡
ፕሪንቲንግ ማለት በነጭ ቲ -ሸርት ላይ የተለያየ ምስልና ጽሑፍ በማተም ወደ ውጭ መላክ ሲሆን ሌብሊንግ ደግሞ ከውጭ በሚገቡ ሸሚዞች አንገት ላይ ተሰፍቶ የምናገኘውን የሸሚዙን ቁጥር፣ የተሰራበትን አገር፣ ስሙና (ሞዱን) እንዲሁም በሸሚዙ የጎን ስፌት ላይ የሚገኘውን ሸሚዙ ከምንና ምን ድብልቅ እንደተሰራ፣ እንዴት መታጠብ፣ መድረቅ መተኮስ፣ … እንዳለበት የሚገልፀው የፀሐይ፣ የዳመና፣ የካውያ … ምልክቶች ያሉበት ጨርቅ ማለት ነው፡፡
ምርቶቻቸውን ወደ ውጭ አገር የሚልኩ ሁሉም ፋብሪካዎች ሌብሉን ከውጭ አገር በውጭ ምንዛሪ እንደሚገዙ የጠቀሱት የቢ ኮኔክትድ ኢንዱስትሪየል ጀኔራል ማናጀር ሚ/ር ቫን አልፈን፣ የፋብሪካቸው አጠቃላይ የኤክስፖርት መጠን እንደሚጨምር እናምናለን ብለዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በመላው ዓለም ከሚሸጡ ቲ-ሸርቶች ውስጥ ከመቶ 70 ህትመት ያለባቸው ሲሆኑ በነጭነታቸው የሚሸጡት ከመቶ 30 መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
እጅግ ዘመናዊ የሆነው የህትመት ፋብሪካችን 800 ሜትር ርዝመት ባለው ስክሪን ጠረጴዛና ከፍተኛ ደረጃ ባለው እንግሊዝ ሰራሹ ሞላላ መሳሪያ በቀን 80, 000 ያትማል ያሉት ጀነራል ማናጀሩ፣ የሌብሊንግ መሳሪያቸው ደግሞ በዓለም ታዋቂ በሆነው ስዊዘርላንድ ሰራሹ ሙለር መሳሪያ የተለያዩ የሽመና ሌብሎች እንደሚያመርቱ ተናግረዋል፡፡
የፋብሪካዎቹ ዋና ዓላማ ከትርፍ ባሻገር የእውቀት ሽግግር ነው ያሉት አቶ አዲስ፣ በተለያዩ የኢንጂነሪንግ ዘርፎች በኤሌክትሪካል፣ በኬሚካል፣ በማሽነሪ፣ … ዘጠኝ ኢንጂነረች ወደ ቤልጂየም፣ ስዊዘርላንድና ቻይና ልከው ስለመሳሪያዎቹ አጠቃቀምና ጥገና በሚገባ ሰልጥነው ወደ አገራቸው ተመልሰው እየሰሩ ስለሆነ በቀሰሙት እውቀት ሌሎች 400 የፋብሪካው ሰራተኞች እንደሚያሰለጥኑ ገልፀዋል፡፡
አቶ አዲስ፣ ሸሪካቸው ሚ/ር ቫን አልፈን የሚያንቀሳቅሱት የቤተሰብ ኩባንያ እንደሆነ ጠቅሰው በተለያዩ የኤስያ አገራት ሰባት ፋብሪካዎች እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ ይህኛው በአፍሪካ የመጀመሪያው ሲሆን ባለሀብቶቹ ኢትዮጵያን ስለወደዱ ከባንክ ሳይበደሩ በራሳቸው ገንዘብ በ5 ወራት የፋብሪካዎቹን ግንባታ አጠናቀው ማስመረቃቸውን አስረድተዋል፡፡
ሚ/ር ቫን አልፈን በተለያዩ ኩባንያዎች ከ50 በላይ ፈቃድ ስላላቸው ቢ ኮኔክትድ ኢንዱስትሪያል እቅዱ መቶ ፐርሰንት ኤክስፖርት ቢሆንም የአገር ውስጥ ፋብሪካዎች በቀጥታም ባይሆን የምርቱ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል፡፡

 ዲፊድ ፕሮጀክቱ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆኑ በመረጋገጡድጋፍ ይገባዋል ብሏል

    የእንግሊዝ አለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዲፊድ)በኢትዮጵያ የልጃገረዶችን አቅም ለመገንባት ታስቦ
ተግባራዊ በመደረግ ላይ ለሚገኘው “የኛ” ፕሮጀክትሁለተኛ ምዕራፍ ማስፈጸሚያ ሊሰጠው ያሰበው
ተጨማሪ የ16 ሚሊዮን ፓውንድ የገንዘብ ድጋፍተቃውሞ እንደገጠመው ዴይሊ ሜይል ዘገበ፡፡ገንዘቡን የሚረዳው ዲፊድ በበኩሉ፤ በፕሮጀክቱ ላይባደረገው ግምገማ አዎንታዊ ተጽዕኖ እያሳደረና ተጨማሪልጃገረዶች ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ እያበረታታቸውመሆኑን የሚያሳዩ ውጤቶች ማግኘቱን ገልጾ፣ ገንዘቡመሰጠቱና ፕሮጀክቱ በቀጣይነት መደገፉ አግባብነትአለው ብሏል፡፡ዲፊድ 54 ሚሊዮን የእንግሊዝ ፓውንድለተመደበለት የገርል ሃብ ፕሮጀክት ሁለተኛ ምዕራፍማስፈጸሚያ የሚውል ተጨማሪ 16 ሚሊዮን ፓውንድለመስጠት መወሰኑን በይፋ ለመግለጽ በዝግጅትላይ መሆኑን የጠቆመው ዴይሊ ሜይል፤ የእርዳታተጽዕኖዎችን የሚያጠና አንድ የአገሪቱ ገለልተኛኮሚሽን ግን፣ የፕሮጀክቱ የስራ ሃላፊዎች የፕሮጀክቱንውጤታማነት በተጨባጭ ማሳየት እስካልቻሉ ድረስየገንዘብ ድጋፉን እንዲያቋርጡ ለሚመለከታቸውሚንስትሮች ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል ብሏል፡፡ገለልተኛ ኮሚሽኑ ከትናንት በስቲያ ያወጣውንሪፖርት ጠቅሶ ዴይሊ ሜይል እንደዘገበው፤ ዲፊድ የገርልሃብን ውጤታማነት ሚያረጋግጥና ተጨማሪ የገንዘብድጋፍ ለማድረግ የሚያስወስነው ከገለልተኛ አካል የተገኘማስረጃ የለውም ብሏል፡፡ፕሮጀክቱ በናይጀሪያ በተለያዩ ምክንያቶች ውጤታማአለመሆኑ በሁሉም አካላት ዘንድ መታመኑን የገለጸውሪፖርቱ፣ በ ኢትዮጵያ ወ ይም በ ሩዋንዳም የ ፕሮጀክቱን ውጤታማነት በተመለከተ የሚቀርቡ ማስረጃዎችአስተማማኝ አይደሉም ብሏል፡፡የእንግሊዝ የግብርከፋዮች ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ጆናታን አይሳቢበበኩላቸው፣
የእንግሊዝ ባለስልጣናት ተገቢነታቸውአጠያያቂ በሆኑ የሌሎች አገራት ፕሮጀክቶች ላይይሄን ያህል ከፍተኛ ገንዘብ እንዲባክን መተባበራቸው፣የአገሪቱን ግብር ከፋዮች እጅግ የሚያስደነግጥ አስገራሚጉዳይ ነው ማለታቸውን ዘገባው ገልጿል፡፡ ገርል ሃብከናይኪ ፋውንዴሽን ጋር በጥምረት የሚተገበር መሆኑንና
እስካሁንም ከእንግሊዝ ግብር ከፋዮች የተሰበሰበ 27.1ሚሊዮን ፓውንድ በድጋፍ ማግኘቱን ስታወሰውሪፖርቱ፣ የፕሮጀክቱ አስተዳደር እንደሚያሳስበው ጠቅሶ፣ናይኪ ሃላፊነቱን በአግባቡ መወጣቱም አጠያያቂ ነውብሏል፡፡ የፕሮጀክቱ ቃል አቀባይ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱየአፍሪካውያን ልጃገረዶችን ህይወት ለማሻሻል ታስቦመተግበር ከጀመረበት እ.ኤ.አ 2010 ጀምሮ፣ በሚሊዮኖችየሚቆጠሩ በድህነት ውስጥ የሚኖሩ ልጃገረዶችን፣ ወጣትወንዶችንና አዋቂዎችን ተጠቃሚ ያደረጉ የማህበራዊናየግንዛቤ ለውጥ ስራዎችን አከናውነናል ብለዋል፡፡“ለአብነትም በኢትዮጵያ በመተላለፍ ላይ የሚገኘውንየኛ የሬዲዮ ድራማና ቶክ ሾው ከሚከታተሉ ልጃገረዶች መካከል 84 በመቶው በራስ መተማመናቸውንለማሳደግ እንደረዳቸው ማረጋገጣቸውንና 76 በመቶየሚሆኑትም ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ እንዳነሳሳቸውመመስከራቸውን መጥቀስ ይቻላል” ብለዋል ቃል

Published in ጥበብ

  በደራሲ ተወልደ ሲሳይ የተፃፈው “77” የተሰኘው በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ ልብወለድ መፅሃፍ ሰሞኑን ለገበያ ቀረበ፡፡ መፅሃፉ መቼቱን በ1977 በኢትዮጵያ በተከሰተውና በመቶ ሺ የሚቆጠሩ ዜጎችን በፈጀው ድርቅና ረሃብ ላይ ያደረገ ነው ተብሏል፡፡
ደራሲው የመፅሃፉን መታሰቢያነት በ1977 ድርቅና መከራ ምክንያት ህይወታቸው ላለፈ፣ ህይወት ለተመሰቃቀለባቸውና በአጠቃላይ የወቅቱ ሰለባ ለሆኑ ኢትዮጵያውያን አድርጓል፡፡ በ 363 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ፤ ለአገር ውስጥ በ75 ብር፣ ለውጭ አገር በ20 ዶላር እንደሚሸጥ ታውቋል፡፡

በፊልም ጥበብ ባለሙያው ሰለሞን በቀለ ወያ የተዘጋጀው “የፊልም ዝግጅት ቴክኒክና ጥበብ” 1ኛ መፅሃፍ በትላንትናው ዕለት በጀርመን ባህል ተቋም (ገተ ኢንስቲቲዩት) ተመርቋል፡፡
መፅሃፉ በፊልም አሰራር፣ ቴክኒካዊ ጥበብና በፊልም አዘገጃጀት ዙሪያ የቀረበ ትምህርታዊ መፅሃፍ ሲሆን ደራሲው በዘርፉ የካበተ የማስተማር ልምድ ያላቸው መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
ደራሲው በሃገር ውስጥና በውጭ ሃገር ዩኒቨርሲቲዎች ከፊልምና ከስነፅሁፍ ጋር የተያያዙ ትምህርቶችን በተለያዩ የዲግሪ ደረጃዎች የተማሩ ሲሆን ታዋቂ በሆኑ አለማቀፍ የፊልም ፌስቲቫሎች ላይም በዳኝነት መስራታቸው ተገልጿል፡፡
ባለሙያው ለበርካታ ዓመታት በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር ጥናታዊ ፊልሞችን የሰሩ ሲሆን በሀገሪቱ የመጀመሪያው እንደሆነ የሚነገርለትን “አስቴር” የተሰኘውን ባለ 35 ሚ.ሜ ልብ ወለድ ፊልም በደራሲነት እና በዳይሬክተርነት አዘጋጅቶ በማቅረብና በሲኒማ ቤቶች ለረጅም ጊዜያት እንዲታይ በማድረግም ውጤታማ ስራ መስራታቸው ተጠቅሷል፡፡
በአሁን ሰዓት ደራሲው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሂውማኒቲስ ኮሌጅ የውጭ ቋንቋዎች ክፍል በዘመናዊ የአውሮፓ ቋንቋዎች ዩኒት ውስጥ በማስተማር ላይ የሚገኙ ሲሆን የተለያዩ የፊልም ጥበብ ስልጠናዎችን እንደሚሰጡም ታውቋል፡፡

 በደራሲ እያዩ ደባስ የተፃፈው “ሁለት ገፅ” የተሰኘ ረዥም ልቦለድ መፅሃፍ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ ደራሲው በመግቢያው ላይ ባሰፈረው መልዕክት፤ “ተረጋጉ፤ አትረበሹ፤ አትጨነቁ፡፡ ስለማንም ቢሆን ክፉ አታስቡ፡፡ መልካምነት ከጉያችሁ ስር ያለ ቅርባችሁ ነው፡፡ በእናንተ ውስጥ ትልቅ ኃይልና መሰጠት አለ፡፡ ያንን ፈልጉ፡፡ ሰዎችን አትመልከቱ፡፡ ራሳችሁን እዩ…” እያለ ይቀጥላል፡፡
በ171 ገፆች ተሰናድቶ የቀረበው መፅሃፉ፤ በማራኪ የታሪክ ፍሰትና አወቃቀር ተሰናስሎ የቀረበ መሆኑን ደራሲው ጠቁሟል፡፡ ከሚቀጥሉት ሥራዎቹ ቀዳሚ ያላቸውንም “የሶርዲኒያሞቹ ምዛዥ”፣ “ቤንዚኒስ” እና “አሽዶዳውያን” በሚል ጠቅሷል፡፡

“ግጥም ሙዚቃና ስዕል፤ ልዩነትና ተዛምዶ” በሚል ርዕስ በነገው ዕለት በብሔራዊ ቤተ መፅሐፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ከቀኑ 8 ሰዓት ተኩል ጀምሮ ውይይት እንደሚካሄድ ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ አስታወቀ፡፡
ለውይይት መነሻ ሃሳብ የሚያቀርበው ገጣሚ ኤፍሬም ስዩም ሲሆን በዝግጅቱ ላይ ገጣሚያን፣ ደራሲያን የሙዚቃ ባለሙያዎችና የጥበብ ቤተሰቦች እንደሚገኙ ተጠቁሟል፡፡
የውይይት ፕሮግራሙን ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ ከኢትዮጲስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ያሰናዳው ሲሆን ከውይይቱ በተጨማሪ የመፃሕፍት ንባብ መርሃ ግብርም የዝግጅቱ አካል እንደሆነ ታውቋል፡፡

Saturday, 20 June 2015 11:40

ዕጣ ፈንታ!

እሣት እንደናፈቀው ምድጃ ፊቱ ቀዝቃዛ ነው። አይኖቹ እሣት አይወረውሩም፡፡ ይልቅ በረዶ ይረጭባቸዋል፡፡ ጥርሶቹ ብዙ ጊዜ ባይገለጡም አንዳንዴ ለቀቅ ሲያደርጋቸው፣ ክርክም ብለው የተደረደሩ ናቸው፡፡ ግን የትምባሆ ጢስ ፈርሞባቸው ያን ያህል ትኩረት አይስቡም፡፡
መርመራ ዳንሣሞን ያለ መጥረቢያ ማየት ይናፍቃል፡፡ ጧት ሻይ ቤት፣ ቀን ሥራ ቦታ፣ ምሽት አረቄ ቤት ሲቆይ ወይም ወደ ቤቱ ሲገባ ትከሻው ላይ ጣል አድርጐት ነው፡፡ መጥረቢያው እንጀራው፤ የሕይወቱ ዋልታና ማገር ነው፡፡
ልጁ ቢላሎም አንዳንዴ ከርሱ ጋር አብሮ ይወጣና ሽንብራ ከሱቅ ገዝቶ ወደ ቤት ይልከዋል፡፡ ሌላም ጊዜ “ቢጤ” የሚባለውን ለምግብነት የተዘጋጀ ቆጮ ወደ እናቱ የሚያደርሰው ያው ልጁ ቢላሎ ነው።
ቁመናው ዘለግ ያለ፣ እግሩ ጫማ ያለመደ፣ ልብሱ ላብ የጠገበ፣ አቧራ የቃመ ነው፡፡ በዚያ ላይ የቀናው ዕለት ግሥላ ሲጋራ፣ ያጣ ቀን ደግሞ ትምባሆ በወረቀት ጠቅልሎ ስለሚያጨስ ጠረኑን ተጋርቷል። ኑሮ ኑሮ የሚመሥለውም ግሥላ ያጤሰ ቀንና አረቄ መጠጫ ያገኘ ጊዜ ነው፡፡ ያኔ ሠላምታው ሁሉ ሞቅ ያለ ነው፡፡
ጧት ለሥራ ሲወጣ አፉ ላይ የሚያደርጋት ቂጣ እንኳ ባይኖር፣ በምራቁ አጥፍቶ ጆሮው ላይ በቁጠባ የሰካትን ትምባሆ ምጎ ቀኑን አሃዱ ይላል፡፡
ባለቤቱ ታደለችም ከእሱ የባሰች ናት፡፡ ቤተሰቦችዋ አልቀው፤ ሰው ቤት እየዞረች ሥራ ስትሰራ አግኝቶ ነው ያገባት፡፡ የመጀመሪያ ልጅዋን ቢላሎን ስትወልድ፣ ደጓ ጐረቤታቸው ወይዘሮ አስካለ ባይኖሩ ጉድ ፈልቶ ነበር፡፡ እንጀራ እየፈተፈቱ፣ ቡና እያፈሉ “እኔን የማርያም አራስ!” በማለት ከርህራሄ ጋር አርሰዋት ነበር፡፡ አሁን ግን እሣቸውም ደኸዩ፡፡ ባላቸው ከሞቱ በኋላ ቤታቸው መቅኖ ራቀው፡፡ ከመርመራ ቤት ለዓመል ያህል ይሻላል እንጂ እንደ ድሮ ብዙ ትሩፋት የለውም፡፡ እንዲያም ሆኖ ወይዘሮ አስካለ አሁንም ደግ ናቸው፡፡ ዛሬም ለሰው ይራራሉ፡፡ ያለቻቸውን ቆርሰው ያካፍላሉ፡፡ መሃን ስለሆኑ ወደ ቤተክርስቲያን ባያደሉ ኖሮ ጠጅ መጣል ይዋጣላቸው ነበር፡፡ ግን ባላቸው ሲሞቱ “የታባቱ ለዚህ ከንቱ ዓለም” ብለው ፊታቸውን ወደ ቤተስኪያን አዞሩ፡፡
መርመራ ማታ ሲገባ ተበሳጭቶ እንደነበር ሚስቱ አስታውሳ፤ “አይዞህ የታባቱ ፈጣሪ ያለው ይሆናል!...ዛሬ ብታጣ ነገ ታገኛለህ፡፡ ጤና ብቻ ይስጠን” ብላ አረጋግተው ነበር፡፡ እንጨት የሚያስፈልጠው ሰው እንዳላገኘ ገብቷታል፡፡ አንዳንዴ እንዲህ እንደሚሆን ሁለቱም ያውቁታል፡፡ የቀናው ዕለት ያም ያም… ናልኝ… ናልኝ ይለዋል፡፡ ዕድል ስትጠምበት ደግሞ ሁሉም ፊቱን ያዞርበታል፡፡ ያኔ ኩርምት ይላል። በተለይ ትምባሆዋን ሲያጣ ሞት ያስመኘዋል፡፡ ደግነቱ የሱስን ነገር የሚያውቅ ሰው አያልፈውም፡፡
ዛሬ ጧት ሲወጣ ግን የማይደፈር ነገር ሊደፍር ወስኗል፡፡ የማሕበረሰቡን ሕግ ሊጥስ ቆርጧል። እርሱ እየተራበ፣ አራስ ሚስቱ ሆድዋ እየጮኸ፣ ለአንድ ሀብታም የተለቀሰበት እንጨት በቁሙ ሲበሰብስ ቆሞ አይመለከትም፡፡ ዛሬ ይለይለታል፤ ብሏል ለራሱ፡፡ በሲዳማ ብሔር ለትልቅ ሰው ልቅሶ ተተክሎ የተለቀሰበት እንጨት ለማገዶ አይውልም፣ ሃራም ነው፤  እንደ ነውር ይቆጠራል፡፡ መርመራ ይህንን ከልጅነቱ ጀምሮ ያውቃል፡፡ ያደገበት ነው፡፡ ተወልዶ ያደገው ተፈሪ ኬላ ባለወልድ ቤተክርስቲያን አካባቢ ነው፡፡ ከትንሿ ከተማ ወጣ ብሎ ነው ዕድሜውን የገፋው፡፡
ረፈድፈድ ሲል ወይዘሮ አስካለ ሁለት ስኒ ቡና በሕፃናት ወተት መያዣ ቆርቆሮ እንዲሁም፣ ትንሽ ቁራሽ ቂጣ አፏ ላይ ጣል አድርገው ለአራስዋ አመጡላት፡፡
አራስዋ ሌላ የምትቀምሰው ነገር አልነበራትም፡፡ ልጅ ቢላሎ ለእናቱ ብሎ እንጂ ሻይ ቤት ሄዶ ቢላላክ፣ ዳቦና ሻይ አያጣም ነበር፡፡ ግን አራስ እናቱን መጋኛ እንዳይመታት ብሎ ፈራ፡፡ እናቱን ከሚያጣ ደግሞ ረሃብ ቢያኝከው ሺ ጊዜ ይመርጣል፡፡ ሁሌም ለእናቱ ይሳሳላታል፡፡
ወይዘሮ አስካለ ቡና ሲያመጡላት ለእሱ የመጣለት ያህል ነበር የተደሰተው፡፡ የእሳቸውን እግር መውጣት ተከትሎ እናቱ ጠራችው፡፡ ገብቶታል፤ ለምን እንደጠራችው፡፡ በሌላ ስኒ ቡና አድርጋ ከቂጣው ላይ ቆርሣ ሰጠችው፡፡
“በቃኝ ታዱ…አንቺ ብዪ እኔ አልራበኝም” አላት እየተግደረደረ፡፡
“ለምን አይርብህም? ማታም ጦም አይደል ያደርከው?”
ከቁራሹ ላይ ቆርሶ ጐረሰና መለሰላት፡፡
ዛሬ ማታ ግን መርመራ ባዶ እጁን አይመጣም። የዕድል ቀኑ እንደሆነ ጠዋት ሲወጣ ነግሯታል፡፡ ቀኑን በምጥ አሣልፈው መርመራን መጠባበቅ ያዙ። ወይዘሮ አስካለም ያለወትሯቸው ብቅ ሳይሉ ቀሩ፡፡
ቢላሎ ተንቆራጠጠ፡፡ ቢቸግረው አብዝቶ አረቄ ወደሚቀማምስባት ቤት ሄዶ አንዣበበ፡፡ አባቱ ግን አልነበረም፡፡ ከተማዋ ውስጥ ሞቅ ያለውን መጠጥ ቤት ሁሉ  አሰሰ፤ የለም፡፡ መርመራን የበላ ጅብ አልጮህ አለ፡፡ ወረድ ብሎ ወደ አበበ አድማሴ ግንብ ቤት ሲደርስ ግርግር አየ፡፡ የሆነ ሰው ወድቆ በመኪና እያፋፈሱ ያስገቡት ነበር፡፡
ቢላሎ ግን እርሱ አልታየውም፤ መኪናው ሲነሳ ቀልቡ ያረፈው መሬት ላይ የተበተነ ሽንብራ ላይ ነበር፤ እያፈሰ በሹራቡ ያዘው፡፡ ተስገብግቦ ሰበሰበው፡፡ በሞትና ሕይወት መካከል ያለን ሰው ሽምብራ በማፈሱ የተናደደው ሰውዬ “የማን አባቱ ባለጌ ነው!” ሲል አምባረቀበት፡፡
 “እንዴ…የራሱ የመርመራ ልጅ አይደል!” ሌላ ሰው በምፀት ተናገረ፡፡
እሱ ግን ሽንብራውን እንደያዘ በድን ሆኖ ቀረ፡፡
“አንተ አባትህ እኮ ነው የተገጨው፣ አንድ ሰውዬ ሲያባርረው የጎማ እራት ሆነ፤ አይተርፍም!”
ቢላሎ እየተንቀጠቀጠ ሽምብራውን ይዞ በረረ። ቤት ሲደርስ ግን ለእናቱ ምንም ትንፍሽ አላለም፡፡ ወዲያው ምጣድ ጥዶ በበቆሎ አገዳ ቆላና ሰጣት። በጣሳ የተቀመጠችውን ቡና ሞቅ አድርጐ አቀረበላት፡፡
አራስዋ እሷን ቀማምሣ ሕፃንዋን ማጥባት ያዘች።
አሁን ቢላሎ ልቡ አላርፍ አለ፤ ነፍሱ ባተተች። ዐይኑን እንባ ጋረደው፡፡ አባቱ ለእነርሱ ሆድ ሲባትል መኪና እንደገጨው ያውቃል፡፡ ሊወጣ ፈለገ፣ ደግሞ እናቱስ? ለማን ጥሏት ይሂድ? በዚህ ምሽት ይህን ጭራሮ ግርግዳ ጥሶ ጅብ ቢበላበትስ?
በዚህ መሀል ወይዘሮ አስካለ ከተፍ አሉ፡፡ “ቤቶች!” ከሌላው ቀን በተለየ ዘው ብለው ገቡ፡፡
“እሜት፤ እትዬ አስካለች” አለች ታደለች፡፡
“ሠላም ናችሁ?”
“ሠላም ነን!”
ምንም አዲስ ወሬ እንደሌለ ገባቸውና ቢላሎን ለብቻው ጠሩት፡፡ ፊቱ ኦና መስሏል፡፡
“የተሠማ ወሬ አለ እንዴ?”
“እናቴ እንዳትሠማ!” አለ ቢላሎ በፍርሃት እየተርበደበደ፡፡
“የአባትህን አደጋ ሠምተሀል?...ይርጋለም ሆስፒታል ተወስዷል፡፡”
አንገቱን አቀርቅሮ ዝም አለ፡፡
“ምን ይሻላል ታዲያ … እናትህ ደሞ ኋላ ለምን አልነገራችሁኝም ትለን ይሆን?”
“አሁን አይንገሯት!” አሮጊቷን ተማፀናቸው፡፡
ወይዘሮ አስካለ ቢላሎን ውጭ ትተውት ወደ ቤት ገቡ፡፡
ምሽቱን በሙሉ ልጅንም አባቱንም ጠበቁ፡፡ ሊነጋጋ ሲል አንድ መኪና መጥቶ ደጅ ላይ ሲቆም ታደለች ደነገጠች፡፡
“እትዬ አስካለ መርመራ አንድ ነገር ሆኗል?!” ስትል ሊያረጓጓት ሞከሩ፡፡ በርግጥ መርመራ ምንም አልሆነም። ድንጋጤ እንጂ ብዙ ጉዳት የለበትም ተብሎ የመጀመሪያ እርዳታ ተደርጎለት ነበር የመጣው፡፡
“እንኳን እግዜር አተረፈህ!” ብለው ተቀበሉት። መኪናዋም አጓርታ እንደ አመጣጧ ጠፋች፡፡  አሁን ቤት ውስጥ የጎደለው ቢላሎ ነው፡፡ የሄደበትን ለማንም አልተናገረም፡፡ ወ/ሮ አስካለ የአባቱ ነገር አልሆንለት ብሎት ሃኪም ቤት የሄደ መስሏቸው ነበር፡፡ እነታደለችን ተሰናብተው ወደ ቤታቸው ሊሄዱ ሲሉ ግን እውነቱን በዓይናቸው በብሌኑ አዩት። አንድ ጊዜ እሪታቸውን ሲያቀልጡት መርመራ ከቤቱ ተስፈንጥሮ ወጣ፡፡ ቢላሎ ጓሮ ያለው ዛፍ ላይ ተንጠልጥሏል፡፡ መርመራ ዛፉን ትክ ብሎ አየው፡፡ “ዛሬ ለመሸጥ የቆረጥኩት የለቅሶ ዛፍ ጣጣ ይሆን?” ብሎ አሰበ፡፡ ይህንን ግን ሌላም ጊዜ አድርጐታል። ዓይኑን ከዛፉና ከቢላሎ ላይ ሳይነቅል ግሥላውን አውጥቶ ለኮሰ፡፡

Published in ልብ-ወለድ

የሰዓሊ ግዛቸው ከበደ 20 የሚደርሱ የስዕል ሥራዎች ለዕይታ የሚቀርቡበት ኤግዚቢሽን በትላንትናው ዕለት ምሽት ከገርጂ መብራት ኃይል ወደ ሳሊተ ምህረት በሚወስደው መንገድ፣ ከሮቤራ ካፌ ጀርባ፣ በማላንጋ የስዕል ጋለሪ ተከፈተ፡፡ ኤግዚቢሽኑ ለተመልካች ክፍት የሚሆነው ዘወትር ቅዳሜና እሁድ፣ ለአራት ተከታታይ ሳምንታት ነው ተብሏል፡፡ ሰዓሊው የአሁኑን ጨምሮ በ50 የስዕል ኤግዚቢሽኖች ላይ (በግልና በቡድን) ሥራዎቹን እንዳቀረበ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ሰዓሊና ቀራጺ ግዛቸው ከበደ፤ ከዚህ ቀደም ዘመን ባንክ በር ላይ የቆመውንና በአሜሪካ የስቶክ ገበያ ተምሳሌት የሆነውን  የበሬ ኮርማ (bull) ፣ከፊትለፊቱ  በኦዳ ታወር ላይ ያለውን ሞሳይክ መስራቱ የሚታወቅ ሲሆን ስቴዲየም በሚገኘው የኦሮምያ ባህል ማዕከል ባለ ሁለት አውታረ መጠን ቅርጾችንም ሰርቷል፡፡   

Page 5 of 16