ሻምፕዮኖቹ ታሪክ ይሰሩ ይሆን?
ብራዚል፣ አርጀንቲና፣ ጀርመን፣ ስፔን
የአለም ዋንጫ ባለቤት፣ የአውሮፓ ሻምፒዮን፣ የፊፋ ሰንጠረዥ ቁንጮ የሆኑት ስፔናዊያን፤ ዘንድሮ ታሪክ ይሰሩ ይሆን? እንደገና ዋንጫ ይዘው ወደ አገራቸው የሚመለሱ ከሆነ፤ 50 ዓመታት ያልታየ አዲስ ታሪክ ያስመዘግባሉ። የአለም ዋንጫን በተከታታይ ያሸነፈ ቡድን የለም - ከብራዚል በስተቀር - እ.ኤ.አ በ1962።
ለዋንጫ ቅድሚያ ግምት የተሰጣቸው ግን፣ ከሁሉም በፊት ለብራዚል ከዚያም ለአርጀንቲና ነው። በመቀጠል ለጀርመንና ለስፔን።

በስቴዲዬሞች ዝግጅት ብትዝረከረክም፣ ብራዚል 3.3 ሚሊዮን ቲኬቶችን ለመሸጥ ተስፋ አድርጋለች። የትኬቶቹ ዋጋ ይለያያል። ለመክፈቻው ውድድርየቲኬቶች ዋጋ 90 ዶላር (1800 ብር) ገደማ ነው።የአንዳንድ ጨዋታዎች ከዚህ ያንሳል። የመጨረሻው የዋንጫ ፍልሚያ ለመመልከት ግን 1ሺ ዶላር (20ሺ) ብር ገደማ ያስፈልጋል።
እንዲያም ሆኖ፣ ብራዚላዊያን በቅናሽ ትኬት እንዲገዙ ተፈቅዶላቸዋል - ለምሳሌ በ27 ዶላር (ከ500 ብር በላይ ነው)። የቲኬት ዋጋ ተወደደብን በሚል የተቃውሞ ረብሻ በየቦታው ተከስቶ እንደነበር ይታወሳል።



Hawk-Eye systemተብሎ የሚታወቀው ቴክኖሎጂ፤ አጀማመሩ ለጨዋታ የታሰበ አልነበረም። በአንድ በኩል እሳት ለብሶ እሳት ጎርሶ የሚወነጨፈውን ሚሳዬል በምን ያህል ፍጥነትና በየትኛው አቅጣጫ እየተጓዘ እንደሆነ ለመከታተልና ለመቆጣጠር ነው የተጀመረ ቴክኖሎጂ ነው - በወታደራዊ ምርምር። ዛሬ ዛሬ ጂፒኤስ ተብሎ ይታወቃል። ሃይለኛ የካሜራ አይን የተገጠመላቸው በርካታ ሳተላይቶች በምድራችን ዙሪያ ወደ ታች አፍጥጠወ ያንዣብባሉ፡፡ የማንኛውንም ነገር ምስል ይቀርፃሉ የሚሳዬልም ጭምር፡፡ ከምስራቅና ከምዕራብ፣ ከደቡብና ከሰሜን አቅጣጫውን ለማስላት እንዲሁም ከፍታውንም ለይቶ ለማወቅ የሚያስችል መረጃ ያቀርባሉ፡፡ ይህንኑ ቴክኖሎጂ በትንሽ ቦታ ተግባራዊ ሲደረግ ነው - ለአንጐል ቀይ ህክምና ጠቃሚ የሆነው፡፡ ከኤክስሬይ ጋር በሚመሳሰል ዘዴ የአንጐልን ምስል የሚቀርፁ መሳሪያዎች በጭንቅላት ዙሪያ ይተከላሉ፡፡ እናም ከታች እስከ ላይ ከቀኝ እስከ ግራ ከፊት እስከ ኋላ ድረስ የአንጐልን ሙሉ ቅርጽ ለማየት ያስችላል፡፡


ዘመናዊ ስታዲዬም ግንባታ፣ የተራቀቀ ቀረፃና ስርጭት፣ ምርጥ ቲቪና ‘ሪፕሌይ’፣ ምቹ ታኬታና የሚያምር ማሊያ... እነዚህ ሁሉ የእግርኳስን ተወዳጅነት ያሻሻሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ቢሆኑም፤ ፊፋ ለቴክኖሎጂ ፍቅር የለውም። እንዲያውም ወደ ጠላትነት ያመዝናል። ዘንድሮ ግን፤ ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር መራመድ ግድ ሆኖበታል።ዳኞች አሻሚ ነገር ሲገጥማቸው፣ የቪዲዮ ቀረፃ አይተው ቢፈርዱ ምናለበት? መስመር አልፎ ጎል የገባ ኳስና መስመር ያላለፈ ኳስ ለይቶ ለማወቅ አስቸጋሪ የሚሆንበት አጋጣሚ መኖሩ አይካድም። በቀላል የኤሌክትሮኒክስ ዘዴ መፍትሄ ቢበጅለትስ? በደቡብ አፍሪካ የ2010 የአለም ዋንጫ ሲካሄድ እነዚህን ቴክኖሎጂዎች መጠቀም ይቻል ነበር። ፊፋ በእጄ አላለም።ቴክኖሎጂዎቹን መጠቀም፣ በጨዋታዎች መሃል ልዩነት ያመጣል በማለት የተቃወሙት የፊፋ ፕሬዚዳንት ሰፕ ብላተር፤ የአለም ዋንጫ ውድድሮችና ተራ የወረዳ ጨዋታዎች በእኩል አይን መታየት አለባቸው ብለዋል። አየ ወግ! አንደኛ፤ የአለም ዋንጫና የወረዳ ውድድር በተፈጥሯቸው እኩል አይደሉም። ሁለተኛ፤ የጊዜ ጉዳይ እንጂ፣ ቴክኖሎጂው እስከ ወረዳና ቀበሌ መውረዱ የማይቀር ነው። ፊፋ ከአቋሙ ፍንክች የማለት ፍላጎት አልነበረውም። ነገር ግን፤ ለትክክለኛ ዳኝነት የሚረዳ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ ባይውልም፤ የተሳሳተ ዳኝነትን የሚያጋልጥ ቴክኖሎጂን መከልከል አይቻልም። ከመዓት አቅጣጫ እየተቀረፀ የሚተላለፈው የቲቪ ስርጭት አብዛኞቹን የዳኝነት ስህተቶች ያጋልጣል። ለምሳሌ ባለፈው የአለም ዋንጫ የእንግሊዙ ላምፓርት በጀርመን ቡድን ላይ ያስገባት ጎል አላግባብ የተሻረችው በዳኝነት ስህተት ነው። እንዲህ አይነት ያፈጠጡ ስህተቶች ላይ የሚፈጠረው ውዝግብ ነው፤ በፊፋ ባለስልጣናት ላይ ጫና በማሳደር፤ ለቴክኖሎጂ እጅ የሰጡት።

በ2007 ‹‹ሱፕርናሽናል ሊግ›› ይጀመራል
በ2007 ወደ የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ የሚያድጉ ሁለት ክለቦችን የሚለየው የብሄራዊ ሊግ ማጠቃለያ ውድድርን የባህር ዳር ስታድዬም እንደሚያስተናግድ ታወቀ፡፡
ስታድዬሙ ውድድሩን እንዲያስተናግድ የተመረጠው ባለው ዓለም አቀፍ የብቃት ደረጃ የተሻለ ፉክክር ይስተናገድበታል በሚል ግምት ሲሆን በየክልሉ የሚገኙ አዳዲስ የስፖርት ማዘውተርያ ስፍራዎችን  መጠቀም አስፈላጊነቱ ስለታመነበት ነው፡፡ የብሄራዊ ሊግ ማጠቃለያ ውድድር 16 ክለቦችን ያሳትፋል፡፡ በ2006 የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሊግ 69 ክለቦች በሰባት ምድቦች ተከፍለው ሲፎካከሩ ቆይተዋል፡፡ ከብሄራዊ ሊጉ 7 ምድቦች  አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ የሚያገኙት 14 ክለቦች እና ሁለት ምርጥ ሶስተኛ ቡድኖች  በባህርዳር ስታድዬም ለሚካሄደው የ16 ክለቦች ማጠቃለያ ውድድር የሚያልፉ ይሆናል፡፡ ውድድሩ ተቀራራቢ ነጥብ በያዙ ክለቦች ጠንካራ ፉክክር ሲታይበት ቆይቷል፡፡  
ይህ በእንዲህ እንዳለ በሚቀጥለው የውድድር ዘመን በተለያዩ ዞኖች ተካፋፍሎ በሚደረገው የብሄራዊ ሊግ እና የፕሪሚዬር ሊግ ውድድር መካከል ሱፕር ናሽናል ሊግ የሚባል አዲስ ውድድር ሊካሄድ ታቅዷል፡፡ ሱፕር ናሽናል ሊጉ 16 ክለቦችን በማሳተፍ ዓመቱን ሙሉ በዙር ውድድር ተካሂዶ ወደ የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ የሚያልፉ ሁለት ክለቦች የሚወሰኑበት ይሆናል። ለብሄራዊ ቡድን የሚሆኑ ተጨዋቾችን ለመመልመል ሱፕር ናሽናል  ሊጉ  አመቺ መድረክ መሆኑ አይቀርም። ምክንያቱም  ወደ ፕሪሚዬር ሊግ የሚያልፉ ክለቦችን ከአድካሚ ውድድሮች በኋላ  ከመለየት ከ16 ቡድኖች ምርጡን ማግኘት የሚሻል በመሆኑ ነው

ሪያል ማድሪድ ባለፈው ሳምንት የተጎናፀፈውን 10ኛው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ  እስኪያገኝ ባለፉት 12 የውድድር ዘመናት የነበረው የውጭ እና ሌሎች ሁኔታዎች እንዲህ ናቸው፡፡
ባለፉት 11 የውድድር ዘመናት ክለቡ ከግማሽ ፍፃሜ ማለፍ ተስኖት ነበር፡፡
በዚሁ ጊዜ ከክለቡ የለቀቁ 12 ተጨዋቾች በተለያዩ ክለቦች የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን አንስተዋል፡፡
በአጠቃላይ በ12 ዓመታት እስከ 19.5 ቢሊዮን ብር ወጭ ሆኗል፡፡
ባለፉት 10 ዓመታት በተጨዋቾች የዝውውር ገበያ 3 ጊዜ አዳዲስ ክብረወሰኖችን የሰበረው ክለቡ ከ2002 እኤአ ጀምሮ ዘንድሮ እስከተገኘው አስረኛው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ድረስ ሪያል ማድሪድ 62 ተጨዋቾች አስፈርሟል፤ 20 ዎቹ ከእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ናቸው፡፡ በዝውውር ገበያው ወጭ የሆነባቸው ደግሞ 32.74 ቢሊዮን ብር ነው፡፡
በየዓመቱ ለደሞዝ ክፍያ ብቻ የሚያወጣው 2.74 ቢሊዮን ብር የሚደርስ ሲሆን ባለፉት 12 ዓመታት የከፈለው 32.88 ቢሊዮን ብር ነው፡፡
የቡድኑ ዋጋ ግምት 60.45 ቢሊዮን ብር
ተንቀሳቃሽ ትርፉ 3.32 ቢሊዮን ብር
ውዝፍ እዳው 4.49 ቢሊዮን ብር

ለ14ኛው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የፊታችን ሰኞ ምዝገባው ሊጀመር ነው፡፡ ከስድስት ወር በኋላ   በአዲስ አበባ በሚካሄደው የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫው  ላይ ተሳታፊዎች 40ሺ  እንደሚሆኑ ይጠበቃል፡፡
የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዘጋጆች እንዳስታወቁት ለ14ኛው የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ውድድር ሰኞ እለት በተመረጡ ስምንት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ መስርያ ቤቶች ምዝገባው የሚጀመር ሲሆን  ለመጀመርያዎቹ 1ሺ ተመዝጋቢዎች የልምምድ ቲሸርት እንደሚሰጥ ገልፀዋል፡፡
በሌላ በኩል በነገው እለት ከሚደረገው የቀለበት መንገድ የዱላ ቅብብል ጋር ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ያዘጋጃቸው ውድድሮች ብዛት 100 ደርሰዋል፡፡

    ሆላንዳዊው የ62 ዓመት ምርጥ አሰልጣኝ ሊውስ ቫንጋል በማንቸስተር ዩናይትድ አሰልጣኝነት ለመስራት  የሶስት ዓመት የኮንትራት ውል ከ3 ሳምንት በፊት ተፈራርመዋል፡፡ በዓመት 6 ሚሊዮን ፓውንድ ደሞዝ የሚሰጣቸው ሲሆን ኦልድትራፎርድ የሚደርሱት በ20ኛው ዓለም ዋንጫ ከሆላንድ ብሄራዊ ቡድን ጋር ተሳትፈው ነው፡፡   የማንችስተር ዩናይትድ ክለብ ሃላፊዎች  በምክትልነት አብሯቸው እንዲሰራ ሪያን ጊግስን ሾመውታል፡፡ ለተጨዋቾች ዝውውር  ገበያ የሚሆን የ200 ሚሊዮን ፓውንድ በጀት አቅርቧል፡፡
በመጀመርያ የውድድር ዘመናቸው የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግን ማሸነፍ እንደሚፈልጉ የተናገሩት ሊውስ ቫንጋል በአውሮፓ እግር ኳስ ከ20 ዓመታት በላይ ልምድ አላቸው፡፡ በተለያዩ ሶስት አገራት የሊግ ውድድሮች ሻምፒዮን ሆነዋል፡፡ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ፤ የአውሮፓ ማህበረሰብ ዋንጫን፤ የኢንተርኮንትኔንታል ካፕ እና የአውሮፓ ሱፕር ካፕ ዋንጫዎችንም ወስደዋል፡፡
ሰሞኑን በወጡ ዘገባዎች እንደተገለፀው የቫንጋል የአሰለጣጠን ፍልስፍና በርካታ ክልከላዎችን በኦልድትራፎርድ ይፈጥራል፡፡ በሊውስ ቫንጋል ጥብቅ መመርያዎች ሊያስቀጡ ከሚችሉ ጥፋቶች መካከል  በመመገቢያ ክፍል በስነስርዓት አለመቀመጥ፤ በግጥሚያ ላይ የኳስ አብዶ ማብዛት፤ በመልበሻ ክፍል ሆነ በማንኛው ቦታ ከአሰልጣኝ ጋር እሰጥ አገባ መግባት፤ ለአንጋፋ ተጨዋቾች ከበሬታ መንፈግ እና ስለደሞዝ እና ዝውውር ጉዳይ በአደባባይ ማውራት የሚሉት ይገኙበታል፡፡

የሶፍትዌር እውቀት በየእለቱ ቱጃሮችን ይፈጥራል ብንል ይሻላል፡፡ የሁለት ኢንተርፕረነሮችን ታሪክ ላጫውታችሁ፡፡ ማይክ ካኖን ብሩክስ እና ስኮት ፍራከር ይባላሉ፡፡ ሁለቱ አውስትራላውያን ወጣቶች የሶፍትዌር ባለሙያ ናቸው፡፡  በጋራ የመሰረቱት አትላሲያን የተባለ የሶፍትዌር ኩባንያ 3.3 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ እንዳለው ከታወቀ በኋላ ለእያንዳንዳቸው የ1.1 ቢሊዮን ዶላር ድርሻ ስላጎናፀፋቸው የቢሊየነሮችን ክለብ መቀላቀል ችለዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲ ተማሪ እያሉ የተገናኙት ሁለቱ ወጣቶች፤ በ10ሺ ዶላር ብድር በሽርክና የሶፍትዌር ቢዝነስ የጀመሩት ከ12 ዓመት በፊት ነው፡፡ የሥራ ሂደት ማኔጅመንት (Workflow-management) የተባለውን ፕሮጀክታቸውን እንደፌስቡክ፣ ሲስኮስና ሲቲ ግሩፕ፣ ቢኤምደብሊው (BMW) የመሳሰሉ ታላላቅ ኩባንያዎችን ጨምሮ 35ሺ ኩባንያዎች እየተጠቀሙበት ነው፡፡
የኢንተርፕረነሮቹ ምርት በማስታወቂያ ብዛት የታጀበ አልነበረም፡፡ ዝም ብለው ምርታቸውን በዌብ ሳይታቸው ነው የሸጡት፡፡ አሁን ይሄው ቢሊየነሮች ሆነዋል፡፡

ለሁለት ዓመት ተኩል የአሜሪካ ኩባንያ ይመራዋል
“መንግሥት ከንግድ ሥርዓት ውስጥ እጁን ማውጣት አለበት” - የኢኮኖሚ ባለሙያ

     በመንግስት የተቋቋመው “አለ በጅምላ” የንግድ ድርጅት፣ ከመገናኛ ወደ ቦሌ በሚወስደው መንገድ ላይ የመጀመሪያውን የጅምላ ንግድ ማዕከል ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በተገኙበት ባለፈው ሰኞ አስመርቋል፡፡ ከመንግስት የልማት ድርጅቶች አንዱ የሆነውን ይህን የንግድ ማዕከል ለማቋቋም ከሁለት አመት በላይ ጥናት የተደረገ ሲሆን “A.T. Kearney” የተሰኘ የአሜሪካ ኩባንያ ድርጅቱን የማቋቋምና የማደራጀት ሃላፊነት እንደተሰጠው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ለሁለት አመት ተኩልም ኩባንያው የስራ አመራሩን ሃላፊነት በኮንትራት የወሰደ ሲሆን ኮንትራቱ ሲጠናቀቅ፣ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ይተኩታል ተብሏል፡፡
“አለ በጅምላ” የንግድ ማዕከል” ደረቅ የምግብ ሸቀጦች፣ የውበትና ንፅህና መጠበቂያዎች እንዲሁም የፅህፈት መሣሪያዎችን በማቅረብ ስራውን የጀመረ ሲሆን ማዕከሉ ማቀዝቀዣዎች ሲሟሉለት አትክልትና ፍራፍሬዎችንም ማቅረብ እንደሚጀምር የንግድ ሚኒስትሩ አቶ ከበደ ጫኔ፤ ገልፀዋል፡፡
የንግድ ማዕከሉ ከግል የጅምላ ንግድ አስመጪዎች ጋር በትብብር እንደሚሠራ የጠቆሙት ሚኒስትሩ፤ በዋጋ ረገድ አሁን ካሉት የግል አስመጪዎች ከ5 እስከ 15 በመቶ ቅናሽ እንደሚኖረው ጠቁመው፤ “አትራፊነታችን እንደተጠበቀ ሆኖ፣ በተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶች ለተጠቃሚው እንዲቀርቡ እናደርጋለን” ብለዋል፡፡
ዘመናዊ የንግድ አሠራርና መረጃን መሠረት ያደረገ አገልግሎት እንደሚሰጥ የተነገረለት የንግድ ድርጅቱ፤ የማይነጥፍ አስተማማኝ አቅርቦት ይኖረዋል ተብሏል፡፡ ዋነኛ ተልዕኮው የግብይት ስርአቱን ማረጋጋት ቢሆንም በየጊዜው የሚፈጠሩ አዳዲስ ምርቶች በኢትዮጵያ ገበያ ድርሻ እንዲኖራቸው ማድረግና በጥናት ላይ የተመሰረቱ ዘመናዊ የንግድ ስርአቶችና አሠራሮችን መፍጠርም የድርጅቱ አላማ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
አቅርቦትን በተመለከተ የተጠየቁት ሚኒስትሩ፤ ከሃገር ውስጥና ከውጭ ፋብሪካዎች በቀጥታ ምርቶችን መቀበልን እንደሚያካትት አስረድተዋል፡፡ በዚህ እድል ለሚጠቀሙ የሃገር ውስጥ ፋብሪካዎች፤ የገበያ ትስስሮሽ በተጠናከረ መልኩ ይፈጠርላቸዋል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ኢንተርፕራይዙ በቀጥታ ምርቱን ከፋብሪካዎች መቀበሉ የግብይት ሰንሰለቱን ያሳጥረዋል፤ የግብይት ስርአቱን የሚረብሹ ደላላዎችም ከጨዋታ ውጪ ይሆናሉ ብለዋል፡፡
“ጅንአድ” የመንግስት ንግድ ድርጅትና አዲስ የተቋቋመው “አለ በጅምላ”፤ ተልዕኳቸው አንድ ቢሆንም አዲሱ ኢንተርፕራይዝ በዘመናዊነት ለመስራት መዘጋጀቱ ለየት እንደሚያደርገው የጠቀሱት ሚኒስትሩ፤ ጅንአድ አሁን የተሰጡትን ስኳር፣ ዘይትና የመሳሰሉ ሸቀጦችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ይቀጥላል፤ “አለ በጅምላ” ሲጠናከር ሁለቱ ተቋማት ሊዋሃዱ ይችላሉ ብለዋል፡፡
“አለ”ን የማቋቋም አስፈላጊነትን አስመልክቶ ያብራሩት ሚኒስትሩ፤ በሀገሪቱ የንግድ ስርአት ዙሪያ ለሁለት አመታት ሲደረግ በቆየው ጥናት፤ የግብይት ስርአቱና የሸቀጦች ዋጋ መልክ የሌለው እንደሆነ መረጋገጡን ጠቅሰው፤ ጥናቱን መነሻ በማድረግም በዘመናዊ መልኩ ግብይት መፍጠር እንዲቻል በርካታ አማራጮች መቅረባቸውን ያወሳሉ፡፡ እንደ ዎል ማርት አይነት ድርጅቶች ወደ ሀገሪቱ ገብተው እንዲሠሩ መፍቀድ የሚለውን ጨምሮ፣ የዎል ማርት አይነት ድርጅት ማቋቋም የሚሉ ሃሳቦች ቀርበው እንደነበር የጠቆሙት ሚ/ሩ፤ “መንግስት የዎል ማርት አይነት ስራ ሊሠራ የሚችል ኢንተርፕራይዝ መክፈት የሚለውን ሃሳብ ተቀብሎ እውን አድርጓል” ብለዋል።
ዎል ማርት በቀጥታ ወደ ሃገር ውስጥ ቢገባ ኖሮ፣ በታዳጊ ደረጃ ያለውን የሃገሪቱን ነጋዴ ሊጐዳ እንደሚችልና ከትርፍ የሚገኘው ገንዘብ ወደ ውጭ ፈሰስ እንደሚሆን ያስረዱት ሚኒስትሩ፤ መንግስት የገበያ ጉድለት ባለበት ሁሉ የመግባት ሃላፊነት ስላለበት፣ የግሉን ዘርፍ በማይጐዳና ተወዳዳሪነቱን በማያቀጭጭ መልኩ፣ ይህን ኢንተርፕራይዝ አቋቁሞ ወደ ገበያው መግባት የሚለውን እንደ አማራጭ መውሰዱን ገልፀዋል፡፡
ተጠሪነቱ ለንግድ ሚኒስቴር የሆነው “አለ በጅምላ”፤ የሰው ሃይሉን ለማጠናከር አለማቀፍ ልምድ ያላቸውን ዳያስፖራዎች ጨምሮ ከ150 በላይ በዘርፉ ልምድና እውቀት ያላቸው የስራ አመራርና የግብይት ባለሙያዎችን እንደቀጠረ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በሶስት አመት ጊዜ ውስጥም ከፍተኛ የህዝብ ክምችት አለባቸው ተብለው በተለዩ 27 የክልል ከተሞች ውስጥ ወደ 36 የሚደርሱ የማከፋፈያ ማዕከላት እንደሚከፈቱ ተጠቁሟል፡፡
ሰሞኑን መገናኛ አካባቢ ተመርቆ ስራ ከጀመረው የንግድ ማዕከል በተጨማሪ በቅርቡ ቃሊቲና መርካቶ ቢስ መብራት አጠገብ ሁለት ማዕከላት ተከፍተው ስራ ይጀምራሉ ተብሏል፡፡  
በአለማቀፍ የኢኮኖሚ ተቋም ውስጥ በሃላፊነት የሚሰሩ አንድ የኢኮኖሚ ባለሙያ በሰጡት አስተያየት፤ ለዘመናት የሃገሪቱን የጅምላ ንግድ ሲመራ የቆየው ጅንአድ፤ ትርጉም ያለው ተፅዕኖ አለመፍጠሩን ጠቅሰው፤ ያሁኑም ተቋም የተለየ ተፅዕኖ አይፈጥርም ብለዋል፡፡ “መንግስት ከንግድ ስርአት ውስጥ እጁን ማውጣት አለበት” ያሉት ባለሙያው፤ ማዕከሉ በመሰረታዊ የፍጆታ ዕቃዎች ላይ ብቻ አተኩሮ ለመስራት መፈለጉ የግል ነጋዴዎችን እምብዛም ላይጎዳ ይችላል፤ ነገር ግን መንግስት በሂደት የጅምላ ንግድ ስርአቱን ሙሉ በሙሉ ለሃገር ውስጥና ለውጭ ባለሃብቶች መተው እንዳለበት ጠቁመዋል፡፡
“በተለይ የሃገር ውስጥ ባለሃብቶች በብዛት ወደ ጅምላ ንግድ ስርአቱ ገብተው ተወዳዳሪነትን መፍጠር እንዲችሉ መንግሥት ማገዝ ይኖርበታል” ሲሉ አሳስበዋል፡፡ እኔም እንደባለሙያ፣ የጅምላ ንግድ ስርአቱ በጥቂቶች መያዙን እረዳለሁ ያሉት አስተያየት ሰጪው፤ “የመንግስት በጅምላ ንግድ ስርአት ውስጥ መግባት በሃገሪቱ የንግድ ተወዳዳሪነት ደካማ መሆኑን ያመለክታል”፤ በማለት ተወዳዳሪነት መፈጠር እንዳለበትና መንግስትም ለዚህ ምቹ መደላድሎችንና የፖሊሲ አማራጮችን መፈተሽ እንደሚገባው ተናግረዋል፡፡ 

         ኢትዮጵያ የቡና ምርት ሂደትና ግብይት ስርአትን ዘመናዊ ባለማድረጓ፣ ከአለማቀፍ ገበያ የሚፈለገውን ያህል ተጠቃሚ መሆን እንዳልቻለች አንድ ጥናት አመለከተ፡፡
ከትናንት በስቲያ በአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያ ልኡክ ጽ/ቤት አዘጋጅነት በአዲስ አበባ ደሳለኝ ሆቴል በተከናወነው የ1ቀን ሴሚናር ላይ፣ የቡና ላኪዎችና አምራቾችን ጨምሮ በቡና ላይ የሚሰሩ አለማቀፍ ተቋማት የተሳተፉ ሲሆን የኢትዮጵያ የቡና ምርትና ግብይት ስርአት ላይ ጥናት ያደረጉት ገንተር ሄላወስ የተባሉ ኤክስፐርት፤ ሃገሪቱ በቡና ምርት ግብይት እያጋጠሟት ያሉትን ተግዳሮቶች ከጠቆሙ በኋላ፣ በአለማቀፍ ደረጃ በዘርፉ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቀጠል በርካታ ማሻሻያዎችን ማድረግ እንደሚጠበቅባት ተናግረዋል፡፡
ጥናት አቅራቢው፤ በኢትዮጵያ የቡና አመራረት ስርአት ዘመናዊነት እንደሚጎድለው ማስረጃዎችን ያቀረቡ ሲሆን ምርታማነትን በሚያሳድጉ ምርምሮች እምብዛም የማይታገዝ መሆኑ፣ የቡና ችግኞችን በተገቢው መንገድ ከበሽታ መከላከል አለመቻሉ፣ በአምራቹ እና በምርምር ማዕከላት መካከል ያለው ግንኙነት ጠንካራ አለመሆኑ እንዲሁም የመረጃ ልውውጥ ስርአቱ ደካማ መሆኑ ለምርታማነቱ አለመዳበር አስተዋፅኦ ማበርከቱን ገልፀዋል፡፡
ከግብይት አንፃር ክፍተቶች ተብለው በጥናት አቅራቢው ከተጠቆሙት መካከልም፤ ግልፅነት የሌለው የተወሳሰበ የንግድ ሰንሰለት መኖር፣ የትራንስፖርት አገልግሎት የመሳሰሉ መሰረተ ልማቶች ተደራሽነት አለመኖር፣ ደካማ የጥራት መመዘኛ በስራ ላይ መዋሉ፣ ትክክለኛ የገበያ መረጃ አለመኖር የሚሉ እና ተለዋዋጭ ህግና መመሪያዎች በየጊዜው መውጣታቸው… ተግዳሮት ሆነዋል ተብሏል፡፡  በቀጣይ ቢተገበሩ ለሃገሪቱ የቡና ምርታማነትና የገበያ ተደራሽነት አጋዥ ናቸው ተብለው በኤክስፐርቱ ከተጠቆሙት መካከልም፤ ኢትዮጵያ የምትታወቅበትን የአረቢካ ቡና ምርታማነት ማሳደግና የግብይት ሰንሰለቱን ማሳጠር እንዲሁም ሰፊ የማስተዋወቅ ስትራቴጂ መንደፍ የሚሉት ይገኙበታል፡፡  

          ቡና፣ ዛሬም የውጪ ንግድ ዘርፉን ገቢ ይመራል። በዚህ ሳምንት አጋማሽ የንግድ ሚ/ር ሚኒስትር ክቡር አቶ ከበደ ጫኔ፤ የመ/ቤታቸውን የዘንድሮ ዓመት የ10 ወራት ዕቅድ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ሲያቀርቡ፣ ከአጠቃላይ የወጪ ንግድ በገቢ ከፍተኛ ድርሻ የያዘውን የቡና የወጪ ንግድ የበለጠ ትኩረት እንዲያገኝ ለማድረግ የድጋፍ ክትትልና ቁጥጥር ተግባራት ለማጠናከር በቡድን ደረጃ የነበረውን አደረጃጀት ወደ ዳይሮክተሬት ደረጃ ማሳደጋቸውን ተናግረዋል፡፡
የግብርና ምርቶች ኤክስፖርት ክትትልና ድጋፍን አስመልክቶ ሚ/ሩ እንደገለጹት፤ ባለፉት 10 ወራት 206,825 ቶን ቡና በመላክ፣ 822.08 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ፣ 136ሺ (65.8%) ቶን ቡና በመላክ፣ 489.28  (53.3%) ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን ገልፀዋል፡፡ ይህ አኀዝ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ቅናሽ አሳይቷል፡፡
ለዚህም ምክንያቱን ሲገልጹ፣ የሚፈለገው የቡና መጠን ወደገበያ ባለመቅረቡ፣ በቡና ዋጋ መዋዠቅ የተነሳ የሚጠበቀውን ያህል ቡና ባለመላኩ፣ በየደረጃው የሚገኘው አመራርና ፈጻሚ ቅንጅታዊ አሠራር በመጓደሉ፣ በነባርና በአዳዲስ ገበያዎች ሰብሮ ለመግባት በቂ የገበያ ማስፋፊያ ባለመሠራቱ፣ የኤክስፖርት ቡና በሕገወጥ መንገድ በሀገር ውስጥና ወደ ጐረቤት አገር በመውጣቱና ይህንንም የኮንትሮባንድ ንግድ ለመከላከል የተደረጉ ጥረቶች ውሱን በመሆናቸው እንደሆነ ጠቅሰው፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የዓለም የቡና ገበያ ዋጋ እየተሻሻለ በመምጣቱ የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ለማሳካት የሚቻልበት አዝማሚያ መኖሩን አመልክተዋል፡፡
ባለፉት 10 ወራት በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በኩል፣ የእርሻ ምርቶች የሆኑትን  ቡና፣ ሰሊጥ፣ ነጭ ቦሎቄ 515,827 ቶን ማገበያየታቸውን የገለፁት ሚ/ሩ፤ ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 43,961 (9%) ሜትሪክ ቶን ዕድገት ማሳየቱን፣ 519,152 ሜትሪክ ቶን ቡና፣ ሰሊጥ፣ ነጭ ቦሎቄና ማሾ ወደ ምርት ገበያው መጋዘኖች ማስገባታቸውንና ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 45,945 (10%) ሜትሪክ ቶን ጭማሪ እንዳሳየ ጠቁመዋል፡፡
ሚ/ሩ በኤክስፖርት ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች፣ ምርቶቻቸውን በብዛትና በጥራት አምርተው ለውጭ ገበያ እንዲያቀርቡ ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ ማድረጉን ገልፀው፤ ባለፉት 10 ወራት ከግብርና ምርቶች፣ ከማኑፋክቸሪንግና ከማዕድን ዘርፎች በአጠቃላይ 4.25 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ፣ 2.61 ቢሊዮን ወይም የዕቅዱ 67.39% መገኘቱን ተናግረዋል፡፡ ይህ አኅዝ ከዕቅድ በታች ቢሆንም ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረው 2.49 ቢሊዮን ዶላር ጋር ሲነፃፀር፣ በ120.11 ሚሊዮን ዶላር ወይም (4.82%) ጭማሪ አሳይቷል ብለዋል፡፡
መ/ቤታቸው ክትትል የሚያደርግባቸው የግብርና ምርቶች የኤክስፖርት አፈጻጸም በተመለከተ፣ ባለፉት 10 ወራት 1.16 ሚሊዮን ቶን የተለያዩ የሰብል ምርቶችን ለዓለም ገበያ በማቅረብ 2.026 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት አቅዶ ነበር። ነገር ግን 776,006 ቶን ወይም የዕቅዱን 67% ቶን የተለያዩ ሰብሎችን ለዓለም ገበያ አቅርቦ 1.54 ቢሊዮን ዶላር ወይም የዕቅዱን 76% ገቢ አግኝቷል፡፡
947,557 የቁም እንስሳትን ለዓለም ገበያ በማቅረብም 223.71  ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ፣ 515, 140 ወይም የዕቅዱን 54.37% የቁም እንስሳት በማቅረብ፣ 164.2 ሚሊዮን ዶላር ወይም የዕቅዱን 73.4% ገቢ አግኝቷል፡፡ በአጠቃላይ የሰብል ምርቶችና የቁም እንስሳት ለዓለም ገበያ አቅርቦ፣ 2.24 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ፣ 1.71 ቢሊዮን ዶላር ወይም 76.34% ገቢ ተገኝቷል። ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀርም የሰብል ምርቶች መጠን 0.8 በገቢ ደግሞ 22% ጭማሪ አሳይቷል፡፡ በሌላ በኩል፤ በቁም እንስሳት በመጠን 11.24% ሲቀንስ በገቢ ደግሞ በ15.68% ጨምሯል፡፡ በአጠቃላይ የንግድ ሚ/ር ክትትል በሚያደረግባቸው የግብርና ምርቶች፣ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በገቢ 10.8% ጭማሪ ተመዝግቧል፡፡
ከኤክስፖርት ክትትልና ድጋፍ አንፃር የቅባት እህሎች ምርት ባለፉት 10 ወራት 335,958 ቶን የቅባት እህሎች ለማቅረብ ታቅዶ፣ 226,640 ወይም የዕቅዱ 67% ግዢ ተፈጽሟል፡፡ 222,727 ቶን ሰሊጥ ለምርት ገበያ እንዲቀርብ የተደረገ ሲሆን ከዕቅዱ ጋር ሲነፃፀር (70%) ብቻ ተሳክቷል፡፡ ዕቅዱ ሙሉ በሙሉ ያልተሳካው አምራች አርሶአደሮች፣ ባለሀብቶችና አቅራቢዎች ምርትን በወቅቱ ለገበያ ባለማውጣታቸው እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
የአቅርቦት መጠኑ ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ከነበረው 163,160.73 ሰሊጥ ጋር ሲነፃፀር የ36.51% ጭማሪ አሳይቷል፡፡ ከጥራጥሬ ምርት፣ ክትትልና ድጋፍ አንፃር 66,605 ቶን ነጭ ቦሎቄ ለኢትዮጵያ ምርት ገበያ እንዲቀርብ ታቅዶ፣ 59,028.6 ቶን ወይም የዕቅዱ 88.6% ቀርቧል፡፡
ባለፉት 10 ወራት 41,054.9 ቶን ጫት በመላክ፣ 235.4 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ፣ 39,970.8 ቶን ወይም የዕቅዱን 92.5% በመላክ፣ 216.8 ሚሊዮን ዶላር ወይም የዕቅዱ 92.1% ገቢ ተገኝቷል። በበጀት ዓመቱ 10 ወራት 920,173 የቁም እንስሳት በመላክ፣ 242.58 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ የተሳካው የዕቅዱን 60 በመቶ፣ 548,664 የቁም ከእንስሳት በመላክ 163.916 ሚሊዮን ዶላር ወይም የእቅዱ 67.6% ገቢ ተገኝቷል፡፡ በሀገሪቷ የተለያዩ ክፍሎች ከሚገኙ የጥሬ ቆዳና ሌጦ አቅራቢዎች 23,262,022 ጥሬ ቆዳና ሌጦ ለተለያዩ ፋብሪካዎች ለማቅረብ ታቅዶ፣ ማሳካት የተቻለው 16,109,240 ወይም የእቅዱ 69.25% ብቻ ነው፡፡
ንግድ ሚ/ር ባቀረበው የ10 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት፤ ከእቅድ በላይ የላቀ አፈጻጸም የታየው በአዲስ የንግድ ፈቃድ አሰጣጥ ነው። 202,236 አዲስ የንግድ ፈቃድ ለመስጠት ታቅዶ 208,728 መስጠቱን ሚ/ር ዴኤታው አመልክተዋል፡፡ እንዲሁም 176,581 አዲስ የንግድ ምዝገባ ለማካሄድ ታቅዶ 157,803 ምዝገባ መካሄዱን፣ 840,991 የንግድ እድሳት ለማካሄድ ታቅዶ 731,665 መከናወኑን አመልክተዋል፡፡
ሌላው የሚ/ሩ ከፍተኛ ስኬት የንግድ ስም ማጣሪያ ክንውን ነው፡፡ 21ሺ የንግድ ስም ለማጣራት ታቅዶ 53,210 የዕቅዱ ማከናወን ተችሏል፡፡ የዚህ ስኬት ምክንያት ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማትን ጨምሮ ወደ ንግድ ሥርዓቱ የሚገባው ማኅበረሰብ ቁጥር በመጨመሩ እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡
ባለፉት 10 ወራት ለተጠቃሚው የስንዴ ዳቦ እንዲቀርብ፣ ለክልሎችና ለሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የሚሆን 5.73 ሚሊዮን ኩንታል ጥሬ ስንዴ፣ ለዱቄት ፋብሪካዎችና ዳቦ ቤቶች ቢቀርብም ፍላጐትና አቅርቦት አልተመጣጠኑም፡፡ ከሚያዝያ ወር ጀምሮ በእህል ንግድ ድርጅት በኩል ስንዴ ከአገር ውስጥ 150ሺ ኩንታል ቢገዛም የስንዴ ፍሰትና አቅርቦት በቂ ባለመሆኑና የስንዴ ዋጋ እየጨመረ በመሄዱ፣ ግዢው በተፈለገው መጠን ሊሳካ እንዳልቻለ ተገልጿል፡፡ ስለዚህ መንግሥት 400ሺ ቶን ስንዴ ከውጭ እንዲገዛ በወሰነው መሠረት ግዢው ተፈጽሞ ስንዴው በሐምሌ ወር እንደሚገባ ታውቋል፡፡ የሸቀጦችን ገበያ ለማረጋጋት ምግብ ነክ የሆኑ ምርቶችንና ምግብ ነክ ያልሆኑ ሸቀጦችን ከውጭና ከአገር ውስጥ አምራቾች ግዢ መፈፀሙን የጠቀሱት ሚ/ሩ፤ ከዚህ ወር ጀምሮ በአዲስ አበባ በሦስት ክፍለ ከተሞች ለመክፈት ካቀዳቸው መጋዘኖች ውስጥ የመጀመሪያውን መገናኛ አካባቢ ከአምቼ የመኪና መገጣጠሚያ ፊት ለፊት “አለ በጅምላ” የጅምላ ንግድ ሸቀጦች መደብር መከፈቱን ገልፀዋል። በክልል ከተሞችም ተመሳሳይ ሥራ ለመጀመር በቀጣይ 3 ዓመታት በ27 ከተሞች 36 መደብሮች ለመክፈት የቅድመ ጥናት ዝግጅት መጀመሩን ሚኒስትሩ ዴኤታው አስታውቀዋል፡፡
የንግድ ዘርፉን ዘመናዊና ቀልጣፋ ለማድረግ ከመ/ቤታቸው ሠራተኞችና ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር በርካታ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተግባራት ማከናወናቸውን ገልፀዋል፡፡ በፌዴራል፣ በክልል መስተዳድሮችና በከተማ አስተዳደሮች፣ በንግዱ ዘርፍ አመራርና ፈጻሚ እንዲሁም በንግዱ ኅብረተሰብ ዘንድ በንግድ አሠራርና ውድድር ላይ የጠራ ግንዛቤ አለመኖር፣ የመፈፀም አቅም ውሱንነት፣ ቅንጅታዊ አሠራር ያለመዳበርና ሌሎች በርካታ ተግዳሮቶች በወቅቱ መታየታቸውን ጠቅሰው በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቷቸው እንደሚሠሩባቸው አመልክተዋል፡፡
ንግድ ሚ/ር በበጀት ዓመቱ ለመደበኛ ወጪዎች ብር 63.23 ሚሊዮን፣ ለካፒታል በጀት 31,645,832 ብር እንደመደበለት ጠቅሶ፣ ባለፉት 10 ወራት ከመደበኛ በጀት ብር 41.96  ሚሊዮን፣ ከካፒታል በጀት ብር 13.83 ሚሊዮን ወጪ መደረጉን ገልፀዋል፡፡
ከንግድ አሠራር ቋሚ ኮሚቴና ከም/ቤቱ አባላት በርካታ ጥያቄዎች ቀርበው ሚ/ር ዴኤታው ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ቋሚ ኮሚቴው፣ ለውጪ ንግድ ዘርፍ ከፍተኛ ድጋፍና ክትትል እንዲሰጠው አሳስቧል፡፡   

በወሲባዊ ግንኙነት ጊዜ ከወንድ ልጅ የሚመነጨው ፈሳሽ/ semen/ የሚነሳው ከአንድ ቦታ ላይ ብቻ አይደለም፡፡ አንድ በመቶ የሚሆነው እርግዝና እንዲፈጠር የሚያስችለው ፈሳሽ /sperm/ ከብልት ሁለት ፍሬዎች ውስጥ መንጭቶ ከዛው ላይ በሚነሳ እጅግ ቀጭን ቱቦ አማካኝነት በማለፍ ወደ ዋናው ቱቦ በመድርስ ከቀሪው 99 በመቶ ከሚሆነው ፈሳሽ ጋር ተቀላቅሎ ይጓዛል፡፡ ዘር እንዲፈጠር ምክንያት የምትሆነውም አንድ በመቶ የሆነችው የዘር ህዋስን/cell/ የተሸከመችው ፈሳሽ ብቻ ነች፡፡ ሌላው ፈሳሽ ይች ህዋስ በቀላሉ ወደ ሴቷ የዘር እንቁላል እንድትደርስ የሚያጓጉዝ፣ ሁኔታውን የሚያፋጥን፣ ለህዋሷ የሚፈጥር ፈሳሽ ነው፡፡ ታዲያ እርግዝናን በወንዶች በኩል ለመከላከል የሚሰራው የወንድ ዘር ማስተላለፊያ ቱቦ የመዝጋት ስራ የሚሰራው ይችን አንድ በመቶ የሚያጓጉዝ ቱቦ / Vas deference /ጠልፎ በመዝጋት /vasectomy/ ወይም በማቋረጥ ሂደቱን መግታት ነው፡፡
በአጠቃላይ ከምናውቃቸውና ሳይንስ ከፈጠራቸው የወሊድ መቆጣጠሪያ መንገዶች ውስጥ በሃገራችን ብዙ የማይታወቀውና በአገልግሎቱም በመጠነኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው የወንድ ዘር መተላለፊያ ቱቦን ማገድ/vasectomy/ ዘዴ ነው፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ 43 ሚሊዮን የሚሆኑ ጥንዶች የዚህ ወሊድ መቆጣጠሪያ ተጠቃሚ ቢሆኑም 77 በመቶ የሚሆኑት የሚገኙት በእስያ ሲሆን፤ ከእነዚህም 70 በመቶዎቹ በቻይናና ህንድ ይገኛሉ፡፡
ይህን የቤተሰብ አገልግሎት እቅድ በለመለከተ ትንታኔ እንዲሰጡኝ እንግዳ ጠርቻለሁ፡፡ እንግዳዬ በተለይ በሃገራችን በመንግስት ጤና ተቋማት ውስጥ ዘላቂ የሆነውን የወንዶች የወሊድ መቆጣጠሪያ መንገድ የሆነውን የዘር መተላለፊያ ቱቦ መዝጋትን በተመለከተ ሞያዊ እገዛና ስልጠና በሚሰጥ ኢንጀንደር ኅልዝ/Engender Health / በተሰኘ ድርጅት ውስጥ ከፍተኛ የጤና አማካሪ ናቸው፡፡ ዶ/ር ደረጀ ንጉሴ የማህጸንና ፅንስ ስፔሻሊስት ሃኪምና የኢሶግ/Ethiopian Society of Obstetrician and Gynecologist / ፕሬዚዳንትም ናቸው፡፡
ዶ/ር ደረጀ ንጉሴ
የማህጸንና ፅንስ ስፔሻሊስት ሃኪም፣በኢንጀንደር ኅልዝ ኢትዮጵያ/Engender Health / ከፍተኛ የጤና አማካሪና  የኢሶግ/Ethiopian Society of Obstetrician and Gynecologist / ፕሬዚዳንት

እኔ ቀድሜ ያነሳሁላቸው ጥያቄ አልፎ አልፎ ከዘልማድ በመነሳት በሚሰሙ ጉዳዮች በማንሳት ነው። የወንድ ዘር ፈሳሽ መተላለፊያ ቱቦን መዝጋት ( vaslotomy) ከወሲባዊ እርካታ ከወሲባዊ ፍላጎትና ብቃት ጋር የሚያያዝ ጉዳይ አለ ወይ አልኳቸው።“ፈጽሞ ከእነኚህ ጉዳዮች ጋር አይያያዝም። የሚታገደው ቱቦ የዘር ፈሳሽን የሚያጓጉዘው ብቻ ነው። በተረፈ ሌሎች የሚመነጩ ፈሳሾች (testestrone)የሚሄዱት በደም ስር አማካኝነት  ነው። ይህ ደግሞ አይነካም። ግንኙነት በሚደረግበት ጊዜ የፈሳሹ መጠን፣ ቀለምና ማንኛውም ነገር በነበረበት ይሄዳል፣ይቀጥላል እንደተጠበቀ ነው። ሄኖም ማስረገዝ የሚችለው አንድ በመቶ የሚሆነው ህዋስ (spermatolzo) እሱ አይኖርም፡፡ ስለዚህ የወሲባዊ ፍላጎት፣እርካታ፣ወንድነትን የሚገልፁ ሌሎች ጉዳዮች ሁሉ እንደተጠበቁ ይቀጥላሉ” ።


ሀኪሞቹ የተሳሳተ ግንዛቤን (misconception) አንዴ ወደራሳችን ካስገባን በኋላ ያንን ግንዛቤ በቀላል ልንነቅለው ይከብዳል ይላሉ። እውነታው እንዲህ ምንም ያህል የጎላ ቢሆንም በሌሎች ሰዎች ተሞክሮ፣ በአይናችን አይተን፣ ውጤቱን ተረድተን ክልሆነ የተሳሳተውን ግንዛቤ ለራሳችን እውነት ነው ብለን ተቀብ እንኖራለን። ወሊድን መቆጣጠር የጋራ (የባልና ሚስት)ሃላፊነት ሆኖ እያለ ለብዙ ዘመናት ወንዶች ሀላፊነቱን ሴቶች ላይ ጥለው ይኖራሉ(እንኖራለን)፡፡
ይህን የዘር መተላለፊያ ቱቦ በሚያዘጋ አንድ ሰው ላይ የሚከሰቱ የጎን ጠንቆች ምንድን ናቸው ስል ዶ/ር ደረጀ ንግግራቸውን ቀጠሉ
“ይኸውልህ ሁለት ነገሮችን እናነፃፅር ለወንዶችም ይሁን ለሴቶች ወሊድን ለመቆጣጠር ሲባል የሚሰሩ ዘለቄታዊ የመቆጣጠሪያ መንገዶች አሉ። ለሴቶች የሚሰራው ሆድ ተቀዶ ነው። ይህም በአንፃራዊ ጊዜ ይወስዳል። ረዘም ላለ ጊዜ ህመም ይኖራል። የተወሰኑ ድህረ ህክምና ህመሞች(complications) ይኖራሉ፣መቀደድና መሰፋት አለ። ለወንዶች በሚሰራው የወሊድ መቆጣጠሪያ የዘር ቱቦን የመዝጋት ዘዴ  /vasectomy/ የሚቀደድና የሚሰፋ ነገር የለም፣ ከአስራ አምስት እስከ ሃያ ደቂቃ ብቻ የሚወስድ ስራና የሁለት ቀን እረፍት ብቻ የሚጠይቅ ሲሆን ከሁለት ቀናት በኋላ ወደ እለታዊ ተግባር መመለስ ይቻላል፣ በቀላሉ የሚሰራ ብዙ ውጣ ውረድ የሌለበት፣ የጎን ጠንቅ ያልበዛበት ነው፡፡ ወሲባዊ ግንኙነትን በተመለከተ ግን ስራው ከተሰራ ጀምሮ ለሶስት ወራት ጥንዶቹ ሌሎች የወሊድ መቆጣጠሪያ መንገዶችን መጠቀም ይኖርባቸዋል፣ ይህን የዘር መተላለፊያ ቱቦ ማዘጋትን የሚያሰራ ሰው አንዴ ወስኖ ከተሰራ በኋላ በእኛ ሀገር አሁን ባለ ህክምና ደረጃ ወደነበረበት መመለስና ግለሰቡ መውለድ ቢፈልግ እንዲወልድ ማድረግ አይቻልም”
በእኛ ሃገር አይቻልም ማለት በሌሎችም አይቻልም ማለት ነው? የእኔ ጥያቄ ቀጠለ፣ ዶ/ር ደረጀም “ ያን ማለት አይደለም፡፡ በእኛ ሀገር መሳሪያውና ስልጠናው ስለሌለ እንጅ በሌሎች ሃገራት ተሞክሮ 90 በመቶ በሚሆን ደረጃ የተሳካ ውጤት ማየት ተችሏል”፡፡
ከዚህ ይልቅ አልኳቸው እንደ ሴቶቹ ሁሉ የሚዋጡ ወይም በመርፌ የሚሰጡ የወሊድ መከላከያ መንገዶች ለወንዶችም መፍጠር አልተቻለም ማልት ነው? በጣም ጥናት የተደረገባቸውና ሙከራዎች ተጀምረውባቸው የነበሩ ዘዴዎች ነበሩ፤ ይሁንና ወንዶች የመድሃኒቶቹን የጎን ጠንቆች ተቅጣጥሮ ጥናቱን አስፈላጊ እስከሆነው  ጊዜ ማስቀጠል አልተቻለም፡፡ በዚህ ረገድ በእርግጥ ወንዶችም የሴቶችን ያህል ኃላፊነት ወስደው ሙከራዎቹን ማስቀጠል ቢችሉ ሙከራዎቹ አንደ ቦታ ላይ ውጤት ያመጣሉ፡፡ ለሙከራ ሙከራ ጣቢያዎች የገቡ ወንዶች መድሃኒቶቹን መውሰድ ከጀመሩ በኋላ በተለያዩ ከጎን ጠንቆች ጋር በተያያዘ እስከ መጨረሻ መዝለቅ አልቻሉም፡፡ ሴቶች ለረዥም ዘመናት ህመሙን፣ችግሩን፣ የጎን ጠንቆቹን ሁሉ ታግሰው እየወሰዱ ነው የወሊድ መቆጣጠሪያ መንገዶች አሁን ከደረሱበት የእድገት ደረጃ መድረስ የተቻለው፡፡ በተመራማሪዎችና ለሙከራዎቹ ፈቃደኛ በሆኑ ግለሰቦች መሃከል አሁንም ትብብሩ ከቀጠለ ጥናቶቹ ውጤት ላይ መድረሳቸው አይቀርም፡፡ ያም ሆነ ይህ አሁን ወንዶችን በተመለከተ አገልግሎት ላይ ያለውን የዘር መተላለፊያ መስመርን ወይም ቱቦን በማዘጋት ወሊድን መቆጣጠር ላይ ወንዶች የሴቶችን ችግር ከመጋራት፣ ከማበረታታትና ከመደገፍ አልፎ ኃላፊነት በመውሰድ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎቱን መጠቀም ይኖርባቸዋል”
እውነትም ልብ ብለን ስንመለከተው ሴቶች ስለበርካቶቹ የወሊድ መቆጣጠሪያ መንገዶች የጎን ጠንቆች ሲያነሱና አንዳንዶቹም ሲያማርሩ ይሰማሉ፡፡ በጣም አልፎ አልፎ ቢሆንም አንዳንዶቹ ፈፅሞ የሚስማማቸው የወሊድ መከላከያ መንገድ ያጣሉ፡፡ አንዱ ክብደት ይጨምራል ሌላው ምቾት ይነሳል፣ አንዱ ራስ ምታት ይሰጣል ሌላው የሆድ ህመም ይፈጥራል፣ አንዱ የወር አበባ ያዛባል ሌላው ጭራሹን ክስተቱን ያጠፋል ወይም ፈሳሹን ያበዛል ወዘተ፡፡ ነገር ግን ሴቶች ይህን ሁሉ ፀጋ እስኪመስል ለምደው ተለማምደውት የወሊድ መቆጣጠሪያዎቹን ይጠቀማሉ፡፡ ኃላፊነቱ የባልና የሚስት ሆኖ እያለ ወንዶች ይህን በተመለከተ ሚስቶቻቸውን ወይንም የፍቅር ጓደኞቻቸውን ‘ይህን ሞክሪ ያኛውን ተይው … ደግሞ እስኪ ሌላ ሞክሪ’ ከማለት ባለፈና የህመም ማስታገሻ መድሃኒት ከማቀበል ባለፈ ያለፈ ኃላፊነት የሚወስዱት በቁጥር እዚህ ግባ የሚባሉ አይደለም፡፡
ዶ/ር ደረጀ እርስዎ በዚህ ሞያና ስራ ውስጥ ከመገኘትዎ አንፃር ይህን አገልግሎት የሚፈልጉ ወንዶች ከውሳኔያቸው በፊት ልብ ሊሏቸው  የሚገቡ ጉዳዮች ምንድን ናቸው? እንደገና ወደመጨረሻዎቸ ጥያቄዎች ገባሁ፡፡ ዶ/ር ደረጀ በጥብቅ ከነገሩኝ ጉዳዮች ውስጥ ይኽኛው መሰረታዊ ጉዳይ እንደሆነ ገመትኩኝ እስኪ እናንተም አንብቡት
“በመጀመሪያ የወንድ ዘር መተላለፊያ ቱቦን መዝጋት /vasectomy/ ዘላቂ የሆነ የወሊድ መቆጣጠሪያ መንገድ ነው፤ ከተሰራ በኋላ በአንድና በሌላ ምክንያት ጥንዶቹ መውለድ እንፈልጋለን ቢሉና ሃሳብ ቢለውጡ ቱቦውን በመቀጠል ወደነበረበት መመለስ አይቻልም /አንድም ግለሰቡ አቅም ኖሮት ወደ ውጭ ሃገር ሄዶ ካላሰራ በስተቀር/ ስለዚህ . . . ውሳኔአቸው  ቅፅበታዊ መሆን የለበትም፣ ተረጋግተው ባልና ሚስቱ ተወያይተው መወሰን አለባቸው፤ ይሄ አስቸኳይና አጣዳፊ ጉዳይ አይደለም፤ በቂና የሚፈልጉትን የልጆች ቁጥርና ፆታ ማግኘታቸውንና ተጨማሪ እንደማይፈልጉ እርግጠኞች መሆን አለባቸው፤ የተደላደለና ስምምነት ያለበት ትዳር መኖር አለበት/ካልሆነ ምንም እንኳን ፍችን መተንበይ ባንችልም ድንገት ቢያጋጥምና ቀጥሎ ከሚኖር ግንኙነት ልጅ የሚፈልጉና የማይፈልጉ መሆናቸውን ከወዲሁ ማየት መገመት ያስፈልጋል/ ይህን ዘዴ የሚመርጡ ሰዎች ሌላውና ዋናው ሊያቁት የሚገባ ጉዳይ የወሊድ መቅጣጠሪያው ዘዴ የአባላዘር በሽታዎችንና ኤች አይ ቪን አይከላከልም፡፡ ቤተሰብ እቅድ አገልግሎት በሚያቀርቡ ተቋማትና ባለሞያዎች በኩልም የወሊድ መቆጣጠሪያ መንገዶችን በተመለከተ ያሉትን አማራጮች በሙሉ ለተጠቃሚዎች ማሳዎቅ ያስፈልጋቸዋል፤ ” ማጠቃለያችንም ይኽው ነው፡፡ ሳምንት እንገናኝ፡፡

Published in ላንተና ላንቺ
Page 3 of 21