የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን (ሉሲዎቹ) በኢኳቶሪያል ጊኒ አስተናጋጅነት በ2007 ዓ.ም. ለሚከናወነው 9ኛው የአፍሪካ ዋንጫ  ለማለፍ  ጥቋቁሮቹን ንግስቶች ከተባሉት የጋና አቻቸው  በደርሶ መልስ ይፋለማሉ፡፡ የመጀመርያው ጨዋታ ነገ በአዲስ አበባ ስታድዬም የሚደረገው ነው፡፡ ሉሲዎቹ በዚሁ ፍልሚያ በሰፊ የግብ ልዩነት ማሸነፍ ከቻሉ የማለፍ እድላቸውን ያጠናክራሉ፡፡ ሁለት የወዳጅነት ጨዋታዎችን ከካሜሮንና ከናሚቢያ ብሔራዊ ቡድኖች ጋር የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በሜዳቸው እና ከሜዳ ውጭ አድርገዋል፡፡ በጥሩ ደረጃ አቋማቸውን በመፈተሽም አስተማማኝ ብቃት ላይ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ከፕሪምየር ሊግ 12 ክለቦች የተወጣጡና 16 አዳዲስ ተጨዋቾች በሚገኙበት ቡድን በአጠቃላይ 37 ተጨዋቾች አሰባስቦ ቢያንስ ለወር ያህል ጠንካራ ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡

     በ2015 በሴኔጋል ለሚካሄደው 19ኛው ከ20 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ አንድ ዙር የማጣርያ ምእራፍ ይቀራል፡፡ ወደዚሁ የመጨረሻ የማጣርያ ምእራፍ ለመሸጋገር ደግሞ የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች ብሔራዊ ቡድን ነገ ከደቡብ አፍሪካ አቻው ከሜዳው ውጭ በመልስ ጨዋታ  ይገናኛል፡፡
ከሁለት ሳምንት በፊት በአዲስ አበባ ስታድዬም በተካሄደው ጨዋታ የደቡብ አፍሪካ ከ20 አመት በታች ብሔራዊ ቡድን   2ለ0 ከሜዳው ውጭ በማሸነፍ የማለፍ እድሉን አስፍቷል፡፡ በነገው የመልስ ግጥሚያ ከሜዳው ውጭ የሚጫወተው የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች ብሔራዊ ቡድን ወደ ቀጣዩ የማጣርያ ምእራፍ ለመሸጋገር በ3 ንፁህ ጎሎች ማሸነፍ ይጠበቅበታል። የመልሱን ጨዋታ ጌታነህ ከበደ የሚገኝበት የደቡብ አፍሪካው ክለብ ቢድቬስት ዊትስ ስታድዬም ያስተናግደዋል፡፡ ከሁለቱ ቡድኖች ጥሎ የሚያልፈው በ3ኛው ዙር የመጨረሻ ማጣርያ  ከካሜሮን ጋር ለደርሶ መልስ ትንቅንቅ ይደርሳል፡፡ በተያያዘ የወጣት ቡድኑን ተከላካይ መስመር ለማጠናከር ያሰበው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በዋናው ብሄራዊ ቡድን የነበሩትን ሳልሀዲን በርጌቾ እና ቶክ ጀምስ ጠርቶ ነበር፡፡ ይሁንና የአፍሪካ የእግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ይህን አካሄድ  ውድቅ አድርጎታል፡፡ ካፍ ለእግር ኳስ ፌደሬሽኑ በላከው ደብዳቤ ሁለቱ የተጨዋቾች  ከጨዋታው አስር ቀናት በፊት ባለመመዝገባቸው ደቡብ አፍሪካን በሚገጥመው ቡድኑ ውስጥ መካተት እንደማይችሉ አስታውቋል፡፡

የተራ ሞባይሎች ተፈላጊነት እየቀነሰ፤ “የስማርት ፎን” ሽያጭ ባለፈው አመት አንድ ቢሊዮን ያህል የደረሰ ሲሆን፤ የምርጦች ምርጥ ሆነው የገነኑት የአፕል አይፎን እና የሳምሰንግ ጋላክሲ ሞባይሎች ላይ ፉክክሩ አይሏል - በየገበያው እና በየፍርድ ቤቱ።
አፕል እስካሁን፣ ግማሽ ቢሊዮን አይፎኖችን ሸጧል። ቆየት ብሎ ወደ “ስማርትፎን” ገበያ የገባው ሳምሰንግ፣ ምርቶቹን በፍጥነት በማስፋፋት ከ200 ሚሊዮን በላይ ጋላክሲ ሞባይሎችን ለመሸጥ ችሏል።
አፕል ባለፈው መስከረም ወር ለገበያ ያቀረበው አይፎን 5፤ በመጀመሪያዎቹ ሶስት ቀናት 9 ሚሊዮን ያህል ተሽጦለታል። ከጊዜ ወደ ጊዜ ሽያጩ እየጨመረ፣ ባለፉት አስራ ሁለት ወራት ብቻ፤ 160 ሚሊዮን የተለያዩ የአይፎን ሞባይሎችን ለመሸጥ ችሏል። ነገር ግን፤ የሳምሰንግ ጋላክሲ ብርቱ ተፎካካሪ ሆነውበታል።
ከአይፎን በሶስት አመት ዘግይቶ የመጣው የሳምሰንግ ጋላክሲ፤ በፍጥነት እየተሻሻለ ከጋላክሲ ኤስ1 ዘንድሮ ጋላክሲ ኤስ5 ደርሷል። ባለፈው ወር  ለገበያ የቀረበው ጋላክሲ ኤስ5፤ ከአይፎን 5 ያልተናነሰ ገዢ እያገኘ እንደሆነ ተዘግቧል።



Published in ከአለም ዙሪያ

በሃይማኖት አክራሪነቱ ምክንያት ተቃውሞ የገጠመውን “የሙስሊም ብራዘርሁድ መንግስት” በመገልበጥ ስልጣን የያዙት ጄ/ል አልሲሲ፣ በግብፅ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ያለ ብዙ ፉክክር በሰፊ ልዩነት ያሸንፋሉ ተብሏል።
በእርግጥ ምርጫው የሚጀመረው  ሰኞ ነው። ነገር ግን፤ በውጭ የሚኖሩ ግብፃዊያን ከወዲሁ ድምፅ ሰጥተው ቆጠራ ተካሂዷል። በዚሁ ቆጠራ፤ ጄ/ል አልሲሲ፣ 94.5% ድምፅ ሲያገኙ፣ ወደ ሶሻሊዝም የሚያዘነብሉ ተቀናቃኛቸው 5.5% ድምፅ ማግኘታቸውን ዎልስትሪት ጆርናል ዘግቧል።
ሰኞ በሚጀመረው የአገር ውስጥ ምርጫም አልሲሲ አብዛኛውን ድምፅ እንደሚያገኙ ከመራጮች የተሰበሰበሰ አስተያየት ይጠቁማል። በእርግጥ፤ በጭራሽ ድምፅ ላለመስጠትና ላለመምረጥ የወሰኑ ግብፃዊያን ብዙ ናቸው። ከፊሎቹ ጄነራሉን በጠላትነት የሚቃወሙ የሙስሊም ብራዘርሁድ ደጋፊዎች ናቸው። ከፊሎቹ ደግሞ፤ የተሻለ አማራጭ የያዘ ደህና ፓርቲና ደህና ፖለቲከኛ በማጣት ከምርጫው ራሳቸውን አግልለዋል። ከእነዚህ ውጭ የሆነው አብዛኛው ግብፃዊ መራጭ፤ ለጊዜው ለአገሪቱ የሚበጃት ጄነራል አልሲሲን የመሰለ ጨከን ያለ መሪ ነው ብለው ያምናሉ።
በሌላ በኩል፤ በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ይዘው ከሰላሳ አመት በላይ ግብፅን የገዟት ሆስኒ ሙባረክ፣ 3 ሚሊዮን ዶላር ገደማ የመንግስት ገንዘብ አጭበርብረዋል በሚል ሰሞኑን የሶስት አመት እስር ተፈርዶባቸዋል። ልጃቸው ደግሞ የአራት አመት እስር። ከዚሁም ጋር የ14 ሚሊዮን ዶላር ቅጣት ተወስኖባቸዋል።

Published in ከአለም ዙሪያ

         ጡረተኛው ጄነራል ካሊፋ ሂፍጠር ከሁለት ወር በፊት አስቀድመው ተናግረዋል። “የሊቢያ መንግስት የሃይማኖት አክራሪዎችንና አሸባሪዎችን መቆጣጠር ካልቻለ፤ የራሴን እርምጃ እወስዳለሁ” በማለት በይፋ የተናገሩት በየካቲት ወር ነው። አንዳንድ ሊቢያውያን፤ “ምነው እንደአፋቸው ባደረጉት!” በማለት ተመኝተዋል። አንዳንዶች ደግሞ፤ “ጦር ሰራዊት የሌለው የጦር ጄነራል!” በማለት ተሳልቀዋል። ከአርባ አመት በላይ ሊቢያን አንቀጥቅጠው የገዟት ሶሻሊስቱ ሙዐመር ጋዳፊ በአመፅ ከስልጣን ወርደው ከተገደሉ በኋላ ለጥቂት ወራት የተስፋ ጭላንጭል ቢታይም፤ ብዙም ሳይቆይ አገሪቱ ወደ ግጭትና ትርምስ ተንሸራትታለች።
ፓርላማው፤ በአክራሪዎች እና አክራሪነትን በሚቃወሙ በርካታ ፓርቲዎች ለሁለት ተከፍሏል። አክራሪዎቹ እርስበርስ ይቀናቀናሉ - በጭካኔ ብዛት ይፎካከራሉ። አክራሪነትን የሚቃወሙት ፓርቲዎችም ቢሆኑ፤ በጎሳ እየተቧደኑ ይሻኮታሉ። ፉክክሩና ሽኩቻው፣ በንግግርና በፅሁፍ ብቻ አይደለም። ዘ ጋርድያን እንደዘገበው፤ እያንዳንዱ ፓርቲና ቡድን፤ የየራሱ ጦርና ታጣቂ ቡድን አለው። አንዳንዶቹ በታንክና በከባድ መሳሪያ የተደራጁ፤ በሺ የሚቆጠሩ ታጣቂዎችን ያሰለፉ ናቸው። የታጣቂ ቡድኖቹ ብዛት በመቶ ይቆጠራል። በሊቢያ የጦር መሳሪያ እጥረት የለም። አንዳንዶቹ  እንደአቅሚቲ በወረዳ፣ ከዚያም አልፎ በመንደርና በሰፈር ግዛታቸውን ለማስፋፋት የታጣቂ ቡድን ያንቀሳቅሳሉ። ገሚሶቹ ግን ወደቦችንና የነዳጅ ማውጫ ቦታዎችን ለመቆጣጠር ይዘምታሉ። ሌት ተቀን፣ ግድያ፣ ተኩስ፣ ፍንዳታ፣ ውጊያ ነው። የሊቢያ የነዳጅ ምርት፣ በቀን 1.4 ሚሊዮን በርሜል እንደነበረ የገለፀው ዎልስትሪት ጆርናል፤ አሁን በታጣቂዎች ግጭት የተነሳ የአገሪቱ የነዳጅ ምርት ወደ 200ሺ እንደወረደ ዘግቧል።
ባለፈው የካቲት ወር በትሪፖሊ በርካታ ነዋሪዎች በታጣቂዎች ከተገደሉ በኋላ ከፍተኛ ተቃውሞ በመነሳቱ፤ ዋና ከተማዋን ተቀራምተው የነበሩ ታጣቂ ቡድኖች ከተማዋን ለቀው እንዲወጡ ተደርገዋል። ግን ብዙም አልራቁም። ዙሪያውን በተለያዩ ከተሞች ካምፕ ሰርተው ተከማችተዋል። ትሪፖሊ የተወሰነ እፎይታ ብታገኝም፤ እንደ ቤንጋዚና ሚዝራታ የመሳሰሉ ከተሞች ግን የታጣቂ ቡድኖች መፈንጫ ሆነዋል። በየሳምንቱ፤ በደርዘን የሚቆጠሩ ፖሊሶች፣ ምልምል ወታደሮችና ዳኞች በተለያዩ ታጣቂ ቡድኖች ይገደላሉ - በተለይ ደግሞ ከአልቃይዳ በማይተናነሱ አክራሪ ቡድኖች። አነስተኛ ከተሞችና የገጠር መንደሮች ደግሞ፣ በጎሳ በተቧደኑ ታጣቂዎች ይታመሳሉ።
በጎሰኝነት እና በሃይማኖት አክራሪነት የተቃወሱ አገሮች ውስጥ፤ እንደ ሞሶሎኒና ሂትለር፤ ወይም እንደ ግብፁ ጄነራል አልሲሲ፤ “እናት አገር” ወይም “አባት አገር” የሚል መፈክር ይዞ የሚመጣ ብሔረተኛ መች ይጠፋል? በሊቢያ ደግሞ ጄነራል ካሊፋ ሂፍጠር።
ከአርባ አመት በፊት የጋዳፊ ወዳጅ የነበሩት ጄ/ል ሂፍጠር፤ ጎረቤት አገር ላይ የወረራ ዘመቻ እንዲመሩ ተመድበው ስላልተሳካላቸው ነው የጋዳፊ ጥርስ ውስጥ የገቡት። እንደምንም አምልጠው በስደት ወደ አሜሪካ የገቡት ጄ/ል ሂፍጠር፤ ተቃዋሚዎችን ለማደራጀት ለበርካታ አመታት ቢጣጣሩም የጋዳፊን መንግስት ሊያነቃንቁት አልቻሉም። የዛሬ 3 አመት በአረብ አገራት ሰፊ የተቃውሞ አመፅ የተቀሰቀሰ ጊዜ ነው፤ ወደ ሊቢያ ተመልሰው የወታደራዊ አመፅ መሪ የሆኑት። ከድል በኋላ የመከላከያ ሃይል ዋና አዛዥ የመሆን እድል አላገኙም። ምክትል ዋና አዛዥ ሆነው ትንሽ ከቆዩ በኋላ፤ ያንኑም ትተው የወጡት ጄ/ል ሂፍጠር፤ ለሁለት አመታት ያህል ድምፃቸው አልተሰማም። ድምፃቸውን ሊያሰሙ ቢሞክሩም፤ ያን ያህልም ሰሚ አልነበራቸው። ከጊዜ ወደ ጊዜ በጎሳ የተቧደኑ ታጣቂዎች እና በተለይም የሃይማኖት አክራሪ ቡድኖች የሚፈፅሙት ግድያ፣ ግጭትና ፍንዳታ እየተባባሰ፣ በሰላም ወጥቶ መመለስ እየጠፋ ሲመጣ አብዛኛው ሊቢያዊም ሲማረር ግን ሰሚ ተገኘ።
ለጄነራሉ ጆሯቸውን ለመስጠት ቀዳሚ ከሆኑት መካከል፣ ፖሊሶችና ወታደሮች ናቸው። የታጣቂ ቡድኖች የግድያ ዘመቻ፤ በፖሊሶችና ወታደሮች ላይ ይበረታልና። በጎሳ የተቧደኑ አንዳንድ ታጣቂዎችንም ለማግባባት ሞክረዋል ጄ/ል ሂፍጠር። እንዲህ አይነት ዝግጅቶችን ለሁለት ወራት እንዳካሄዱ የሚገልፁት ጄ/ል ሂፍጠር፤ ባለፈው ሳምንት በቤንጋዚና በትሪፖሊ ከተሞች ወታደሮችን በማሰማራት ወደ ጥቃት ዘመቻ እንደተሸጋገሩ አውጀዋል። ያሰባሰቡትን ወታደራዊ ሃይል፤ “የሊቢያ ብሔራዊ ጦር” ሲሉ ሰይመውታል። “አባት አገር ተደፍሯል” የሚሉት ጄ/ል ሂፍጠር፤ የዘመቻው መጠሪያ ስም፤ “የሊቢያን ክብር የማስመለስ ዘመቻ” የሚል እንደሆነ ተናግረዋል። ቤንጋዚ ከተማ ውስጥ፤ ባለፈው አርብ ሶስት አክራሪ ቡድኖች ላይ ጥቃት ከፈፀሙ በኋላ፤ እሁድ እለት በትሪፖሊ ፓርላማ ላይ ታጣቂዎችን አዝምተዋል።
የፓርላማው የስልጣን ዘመን ካበቃ ሁለት ወር ስላለፈው ህጋዊ ስልጣን የለውም የሚሉት ጄ/ል ሂፍጠር፤ “አክራሪዎች ፓርላማውን ተቆጣጥረውታል፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአክራሪ ቡድን ተወካይ ናቸው፤ ብሔራዊ ጦርና ብሔራዊ ፖሊስን ከማደራጀት ይልቅ አክራሪ ታጣቂ ቡድኖችን በመደገፍ ያጠናክራሉ” በማለት ፓርላማ ላይ የፈፀሙት ጥቃት ተገቢ እንደሆነ ይናገራሉ። አክራሪ ቡድኖችና ታጣቂዎች በድርድርና በውይይት አያምኑም፤ ስለዚህ እስክናጠፋቸው ድረስ እንዋጋለን ብለዋል ጄነራሉ።
የጄነራሉን ድርጊት ለማውገዝ እንደማይፈልጉ የገለፁ አንዳንድ ሚኒስትሮችና የፓርላማ አባላት፤ አክራሪ ቡድኖችን መቃወም ተገቢ ነው ብለዋል። የተወሰኑ ሚኒስትሮች ደግሞ፤ የጄነራሉ ጥቃት አደገኛ ነው፤ በቋፍ ያለችውን አገር ወደ ለየለት ጦርነት ሊያስገባት ይችላል ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩና በርካታ ባለስልጣናት ግን፤ የጄነራሉ ዘመቻ ከመፈንቅለ መንግስት ተለይቶ አይታይም ሲሉ አስጠንቅቀዋል። በትሪፖሊ ዙሪያ የሰፈሩ ታጣቂ ቡድኖች ወደ ዋና ከተማዋ በመግባት የጄነራሉን ጥቃት እንዲከላከሉ ጥሪ ያስተላለፉት ጠቅላይ ሚኒስትር፤ የቤንጋዚ አየር ማረፊያ አገልግሎት እንዳይሰጥ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል። የአገሪቱ መከላከያ ሃይል፤ በጡረተኛው ጄነራል ላይ እርምጃ እንዲወስድም በይፋ አዘዋል - ጠቅላይ ሚኒስትሩ። ነገር ግን ትዕዛዛቸው አልሰራም። በሁለት ከተሞች የሚገኙ የአየር ሃይል ካምፖች በጡረተኛው ጄነራል ስር ለመመራት በመወሰናቸው፤ ሄሌኮፕተሮችና የጦር አውሮፕላኖች በቤንጋዚ ዘመቻ ላይ ተካፍለዋል። የመከላከያ ሃይል ወታደራዊ ፖሊስ አዛዥ በበኩላቸው፤ በጄነራል ሂፍጠር መሪነት የአገሪቱ መንግስት ከስልጣን መታገዱን በማወጅ፤ ጊዜያዊ መንግስት እንደሚመሰረት ገልፀዋል።
ለሁለት አመት ተረስተው የነበሩት ጡረተኛ ጄነራል፤ አሁን ወታደራዊ ልብስ ከነማዕረጋቸው ለብሰው በሳምንት ውስጥ ገናና ለመሆን ቢችሉም፤ የመንግስት ስልጣን ለመቆጣጠር አቅም ይኑራቸው አይኑራቸው ገና አልታወቀም። ለእርስ በርስ ጦርነት የሚሆን አቅም እንዳላቸው ግን አያጠራጥርም። ለዚህም ይመስላል፤ የአልጄሪያ መንግስት ልዩ ወታደራዊ ሃይል በመላክ ዲፕሎማቶቹንና ዜጎቹን ከሊቢያ ሲያስወጣ የሰነበተው። የሞሮኮ መንግስትም አምስት ሺ ወታደሮችን ወደ ድንበር አሰማርቷል። የአውሮፓ አገራትና አሜሪካ፤ ዜጎቻቸውን በአፋጣኝ ለማስወጣት መጣደፍ ጀምረዋል። በአጠቃላይ በግጭት የምትታመሰው ሊቢያ፤ አሁን እንደገና መጨረሻው በማይታወቅ የጦርነት ውጥረት ውስጥ ገብታለች።

Published in ከአለም ዙሪያ

የፕሬዚዳንት ሙሴቪኒን መንግስት ለመጣል ከበርካታ አመታት የተዋጉት ጆሴፍ ኮኒ፤ ልጃቸውን የወለዱትና ያሳደጉት እዚያው በረሃ ውስጥ ነው። ግን በአባቱ ስም አይደለም የሚጠራው። ሳሊም ሳልህ ይባላል።
ኤፍፒ እንደዘገበው፤ጆሴፍ ኮኒ ልጃቸውን ሳሊም ሳልህ ብለው የሰየሙት፣ ከፕ/ት ሙሴቪኒ ወንድም ጋር ሞክሼ እንዲሆን ስለፈለጉ ነው። ራሳቸውን እንደ ፕሬዚዳንት ልጃቸውን ደግሞ እንደ ተተኪ ፕሬዚዳንት ማየታቸው ሊሆን ይችላል። በረሃ ተወልዶ በረሃ ያደገው ልጅ፤ ዛሬ የ22 አመት ጎረምሳ ሆኗል። ሰሞኑን ደግሞ የአማፂው ቡድን ምክትል መሪ እንዲሆን በአባቱ ሹመት ተሰጥቶታል።
የክርስትና አክራሪነት ላይ የተመሰረተውና “ሎርድስ ሬዚስታንስ አርሚ” የተሰኘው አማፂ ቡድን በዩጋንዳ፤ ብዙ ሺዎችን በጭካኔ ከመጨፍጨፉም በተጨማሪ ከ60ሺ በላይ ሕፃናትን ጠልፎ ለውጊያ በማሰማራትና ለወሲብ በማስገደድ ይታወቃል። በፈጣሪ የተመረጥኩ ነብይ ነኝ የሚሉት ጆሴፍ ኮኒ፤ አላማዬ ሃይማኖታዊ መንግስት ለመመስረት ነው ይላሉ።

Published in ከአለም ዙሪያ

ታይላንድ የገዢ ፓርቲ ባለስልጣናትና ተቃዋሚዎች ሐሙስ እለት ታስረዋል

ገዢውን ፓርቲ የሚደግፉና የሚቃወሙ ቡድኖች በሚያካሂዱት አመፅ ስትታመስ የከረመችው ታይላንድ፤ በዚህ ሳምንት ለወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ተዳርጋለች። “የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ” ተግባራዊ ለማድረግ መወሰኑን ማክሰኞ እለት የገለፀው የአገሪቱ የጦር ሃይል፣ ውሳኔው የመንግስት ግልበጣ አይደለም በማለት ደጋግሞ ተናግሯል። “የጦር ሃይል፣ የመንግስት ግልበጣ ሳያካሂድ በአገሪቱ ላይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመጫን ስልጣን አለው” ሲልም ከመቶ አመት በላይ ያስቆጠረና የተረሳ ጥንታዊ የሕግ አንቀፅ በመጥቀስ ለማስረዳትና ለማስተባበል ሞክሯል። ማስተባበያው ግን ከሁለት ቀን በላይ አልዘለለም። ሐሙስ እለት፤ ወደለየለት መፈንቅለ መንግስት ተሸጋግሯል።
ስልጣን የተቆጣጠረው የጦር ሃይል፤ የተቃውሞ ሰልፎችን በማገድ ወታደሮችን ለቁጥጥር ካሰማራ በኋላ የዋና ከተማዋ ጎዳናዎች ፀጥ ረጭ ብለዋል። ከተቀናቃኝ ፓርቲዎች ጋር ጎራ ለይተው ቀውሱን ያባብሳሉ የተባሉ 14 የቴሌቪዥን ቻናሎችና 3000 የሬዲዮ ቻናሎችም ለጊዜው ታግዳችኋል ተብለዋል።
ከዚሁ ጎን ለጎን፤ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች እንዲሁም ከፓርቲዎቹ ጋር ጎራ ለይተው የተሰለፉ ተቀናቃኝ ቡድኖች ለውይይት እንዲሰበሰቡ ወታደራዊው ሃይል ማክሰኞ እለት በቴሌቪዥን ማሳሰቢያ አሰራጭቷል። ለአመታት ሲወዛገቡ የቆዩትና በተለይም ባለፉት ስድስት ወራት በየአደባባዩ ሲጋጩ የከረሙት ተቀናቃኝ ፓርቲዎችና ቡድኖች፤ አንድም ጊዜ ተቀራርበው ለመነጋገር ፈቃደኛ አልነበሩም።
ወታደራዊው ሃይል ማሳሰቢያ ባሰራጨ ማግስት ግን፣ ለውይይት ፈቃደኛ ሆነው ተሰብስበዋል። ሁለት ሰዓት ተኩል በፈጀው ውይይት አንዳች የመፍትሄ ሃሳብ ላይ ባይደርሱም ጥሩ ጅምር ነው ብሏል የወታደራዊው ሃይል ቃል አቀባይ። ፓርቲዎቹ እንደገና ሃሙስ እለት ለመገናኘት ተቀጣጥረው ነበር - በስልጣን ክፍፍልና በምርጫ ዝግጅት ላይ ለመወያየት።
የሃሙሱ ስብሰባ የተካሄደው በጦር ሃይሎች ክለብ ውስጥ ነው። ምርጫ እስኪካሄድ ድረስ በጊዜያዊነት ስልጣን የያዘው ገዢ ፓርቲና ተቃዋሚ ፓርቲ፤ እንዲሁም ጎራ ለይተው ከሁለቱ ፓርቲዎች ጋር የተሰለፉ ተቀናቃኝ ቡድኖች ለስብሰባው መጥተዋል። ሚኒስትሮች፣ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፣ የፖለቲካ ቡድኖ ተወካዮች፤ ማክሰኞ እለት እንዳደረጉት ሃሙስ እለትም ወደ ሁለት ሰዓት ገደማ ተነጋግረዋል። ግን፤ ሊስማሙ አልቻሉም። ገዢው ፓርቲ ስልጣን ለመልቀቅ ፈቃደኛ አይደለም። ተቃዋሚው ፓርቲ ስልጣን ካልተሰጠኝ ሞቼ እገኛለሁ ይላል።  ይሄኔ ነው፤ የጦር ሃይሎች ዋና አዛዥ ጄነራል ፕራዩዝ ቻንኦቻ፤ ትእግስታቸው እንዳለቀ የገለፁት። ተሰብሳቢዎቹም ሆኑ ውይይቱን ለመዘገብ የመጡ ጋዜጠኞች ምን እየተፈጠረ እንደሆነ አላወቁም። “የናንተ ንግግር ማለቂያ የለውም” ሲሉ የተናገሩት ጄ/ል ፕራዩዝ፤ “ከአሁን ጀምሮ፣ ስልጣን በኔ እጅ ውስጥ ገብቷል” በማለት ነገሩን በአጭሩ ቋጩት። ለውይይት የተሰባሰቡት ሚኒስትሮች፣ ተቃዋሚዎች፣ የፖለቲካ ቡድን መሪዎች በዚሁ የሚሰነባበቱ መስሏቸው ነበር። ነገር ግን እዚያው እንደተሰበሰቡ ወደ ምድር ጦር ካምፕ ተወስደው እንዲታሰሩ ነው ጄነራሉ ትዕዛዝ የሰጡት። ፖለቲከኞች ሲወያዩ ለማየት የሄዱ ጋዜጠኞች፣ ፖለቲከኞች ሲታሰሩ አይተው ተመለሱ። በስብሰባው ላይ ያልተገኙ ሚኒስትሮችና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች፣ በአንድ ቀን ውስጥ እጃቸውን እንዲሰጡ በሚዲያ ማስጠንቀቂያ ተሰራጭቷል።
የጦር ሃይል ዋና አዛዥ ጄ/ል ፕራዩዝና ምክትላቸው፤ እንዲሁም ኤታማዦር ሹም፣ የባህር ሃይል፣ የአየር ሃይልና የፖሊስ ዋና አዛዦችን ያካተተ የአምስት ጄነራሎች ኮሚቴ፤ የመንግስትን ስልጣን እንደተቆጣጠረ ጄ/ል ፕራዩዝ ገልፀዋል። ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል። ሁሉም የሚዲያ ተቋማት፤ የግል የቴሌቪዢንና የሬድዮ ጣቢያዎችም ጭምር፤ ከወታደራዊው ጁንታ ከሚመጣላቸው ነገር ውጭ ምንም እንዳያሰራጩ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል። የፖለቲካ ፓርቲ እንቅስቃሴ፣ ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ተከልክሏል። የማታ ሰዓት እላፊ ታውጇል።
በአጠቃላይ፤ ከመፈንቅለ መንግስት ጋር ተያይዘው የሚመጡ እርምጃዎች በሙሉ በፍጥነት ተከናውነዋል። ፍጥነታቸው አይገርምም። ታይላንድ በመፈንቅለ መንግስት በኩል፤ ከፍተኛ ልምድ የተከማቸባት አገር ናት። በመቶ አመታት ውስጥ 19 የመፈንቅለ መንግስት ታሪኮችን በማስተናገድር በአለም ቀዳሚ አገር ናት ተብሎላታል።

Published in ከአለም ዙሪያ

አንድ
የህመምተኛዋ የኋላ ታሪክ
ያገባችው በ14 ዓመቷ ሲሆን የመጀመሪያ ልጇን በ15 ዓመቷ ወለደች፡፡ በአጠቃላይ ዘጠኝ የእርግዝና ጊዜዎች ነበሯት፤ ከእነዚህ እርግዝናዎች ውስጥ የመጀመሪዎቹ  አራት ልጆች በህይወት ተወለዱ፣ በአምስተኛ ግን ውርጃ አጋጠማት፡፡ የስድስተኛው እርግዝና ቀጠለ በዚህ ጊዜ በህክምና በጣም አልፎ አልፎ የሚያጋጥም ክስተት በዚች እናት ላይ ተከሰተ፣ ፅንሱን የተሸከመው ማህፀን አብሮ የመውጣት አጋጣሚ ተከሰተ (uterine prolapse)፡፡  በወቅቱ ለእናትም ይሁን በቅርብ ላሉ ሰዎች አስደንጋጭ ቢመስልም ከሌሎች ሶስት አመታት በኋላ ይችው እናት ሶስት ጊዜ እርግዝና ተከስቶ በተመሳሳይ የማህፀን መውጣት ችግር ፅንሶቹ ሁሉ በውርጃ ተጠናቀዋል፡፡ የሁሉም የፅንስ ማቋረጥ አጋጣሚዎች የተከሰቱት በመጀመሪያዎቹ ሶስት የእርግዝና ወራት ጊዜ ውስጥ ነበር፡፡ ይች እናትም ሆነች ባለቤቷ ምንም አይነት የእርግዝና መከላከያ መንገዶችን ተጠቅመው አያውቁም፡፡ ቀጥሎ (ከምታነቡት የመጨረሻና ዘጠነኛው እርግዝና በፊት ሃኪም ቤት ጎብኝታ ወይም ሃኪም አይቷት አያቅም፡፡ የት ነው የምትኖረው…….? በኔፓል አንዲት የገጠር መንደር ውስጥ፡፡ በቻይና፣ በህንድ፣ በባንግላዲሽና በቡሁታን መሃከል ላይ እነዚህን ሀገራት ተዋስና የምትገኝ የኤዥያ ሀገር ነች፡፡
በህክምና ተቋም ውስጥ ምን ተደረገላት?
እናት ሃኪም ቤት ስትደርስ እኩለ ለሊት አልፏል (መቼም በሽታም በሉት ምጥ ለሊት ላይ የሚከሰተውና የሚባባስበት ነገር አለው፡፡ እሱም ክፋት ሆኖበት ሰውም፣ ትራንስፖርትም፣ ስራም አገልግሎትም የሌለበትን ሁሌታ ይመርጣል ልበል?) እናት ስትደርስ ላብራቶሪውም፣ መድሃኒት ቤቱም ተዘግቷል፤ የደሟን አይነት (blood group) ለመለየት እንኳን ባለሞያዎቹ የተሟላ መሳሪያ አላገኙም-ለሁሉም እስኪነጋ መጠበቅ ሊኖርባቸው ነው፡፡ የተረገዘው ልጅ እግሩ ይታያል፡፡ ከዚህ በፊት እንዳጋጠማትና እንደተለመደው የእናት ማህፀን አብሮ ዘልቋል፡፡
የማህፀን በር (የልጁ እግር በዘለቀበት በኩል) ቁስለት (decubitus ulcer) ያሳያል፡፡ ባሙያዎቹ ምንም አይነት ከፍ ያለ አደጋን የመከላከል እርምጃ ከመውሰድ የተሻለና የመረጡት በአቅራቢያ ወደሚገኝ ሆስፒታል በፍጥነት መላክን ነበር፡፡ ለዚህ የጤና ተቋም በቅርበት የሚገኘው ሆስፒታል ደግሞ በ200 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን ይህ ደግሞ በአይሮፕላን ካልሆነ በመኪና የሚታሰብ አልነበረም፤ ወደ ቦታው ለመድረስ የመኪና መንገድ የለምና። ሃኪሞቹ ለመንገድ የሚያግዛት መጠነኛ እርዳታ ካደረጉላት በኋላ ከአዋላጅ ነርስ ጋር አቆራኝተው በ200 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ወደሚገኝ ሆስፒታል እድትሄድ ወሰኑ፡፡ ሆኖም በረራ የሚጀምረው ንጋት ላይ ሆነ፡፡ አይነጋ የለም ነጋ- ሲነጋ ቲኬት ተቆርጦ ለመሳፈር በተዘጋጀችበት የመጨረሻ ቦታ (boarding) ላይ ምጡ ተባብሶ በነርሷ እርዳታ ወለደች፡፡  ህፃኑ ሶስት ኪሎ ከ200 ግራም ይመዝናል፡፤ ወደ አየር ማረፊያና መነሻው በሄደችበት ሁኔታ መጀመሪያ ወደ ታየችበት ሆስፒታል እንድትመለስ ተደረገ፡፡
የባሙያዎች ቀጣይ ስራ ለማህፀን ቁስለት መፍትሄ መሻት ነበር፡፡
ለተከታታ አስር ቀናት ህክምናው በሆስፒታሉ ውስጥ ሲደረግላት ቆየች፡፡ ሆኖም ይች እናት ከዘጠነኛው እርግዝና አደጋ በኋላ የእርግዝና አጋጣሚ እንዳይኖራት ለባለቤቷ ሰፊ ምክር በመስጠት የእርግዝና መከላከያው ለሱ እንዲሰጥ ተጠየቀ ለዚህም ፈቃደኛ ሆነ፡፡ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ባል የዘር መተላለፊያ ቱቦ እንዲቋረጥ ወይም እንዲዘጋ ተደረገ፡፡
በመጨረሻም ፀሃፊው መደምደም ሲፈልግ
ክስተቱ ያልተለመደና በጣም አልፎ አልፎ የሚታይ መሆኑን ይጠቁማል፡፡ ከ1988 እ.ኤ.አ ጀምሮ እስከ 2008 ባለው ጊዜ በተመዘገበ መረጃ ከደርዘን ባልበለጡ እናቶች ላይ ተመሳሳይ ሁኔታ መከሰቱን ያወሳል፡፡ ብዙ ጊዜ የህክምና ክትትል በሚያደርጉ፣ ተከታታይ እርግዝና ባለበት፣ ያለ ባለሙያዎች እገዛ በሰፈርና በቤታቸው ውስጥ አምጠው በሚወልዱ፣ የተመጣጠነ ምግብ በእርግዝና ወቅት አለማግኘትና ከወሊድ በኋላ እናቶች የማህፀናቸው መጠን ወደነበረበት ሁኔታ እስኪመለስ በቂ የእረፍት ጊዜ አለማግኘት ቀደም ሲል የተመለከትናትን እናት አይነት አጋጣሚ ሊከሰቱ የሚችሉባቸው ምክንያቶች ናቸው፡፡ ከተጠቀሱት ምክንያቶች በላይ ደግሞ በተለይ ማህፀን ወደ ማህፀን በር ማፈግፈግና በብልት የመውጣት አጋጣሚ ያለ እድሜ ጋብቻና ያለ እድሜ በሚወልዱ ህፃናት ላይ ሊከሰት የሚችል ችግር ነው ይላል። ምንጫችን ሬፕሮዳክቲቭ ኅልዝ ማተርስ የተሰኘው ጆርናል ነው፡፡
ሁለት
ህፃናት ከቀን ይልቅ ለሊት ለምን የበለጠ ያለቅሳሉ?
ከተወለዱ እስከ ስድስተኛው ወራት አብዛኞቹ ህፃናት (66 በመቶ የሚሆኑት ለሊት በሳምንት ሁለቴ ሊነቁና ሊያለቅሱ ቢችሉም ቀሪዎቹ (33 በመቶ የሚሆኑት) ግን በሳምንት ከ10 ጊዜ በላይ ከእንቅልፋቸው ሊነቁና ሊያለቅሱ ይችላሉ፡፡ መቼም በርካታ ወላጆች ቀን በአድካሚ ስራ ላይ ውለው እንደገና ለሊት በህፃን ልጃቸው አማካኝነት ሌላ ስራ ውስጥ የሚጠመዱበት ሁኔታ ይኖራል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ልጆቻቸውን አባብለው ካስተኙ በኋላ እነሱ እንደገና ወደ እንቅልፍ መመለስ የሚያቅታቸው ወላጆችም ይኖራሉ። በስንት መገላበጥ፣ ታሽተው….ታሽተው ሸለብ ማድረግ ሲጀምሩ ህፃኑ እንደገና ለቅሶ ያሰማል፡፡
ይናደዱ ይሆን ወይስ ያዝኑ? ከዚህም በሚብስ ሁኔታ ህፃናቱ ፈፅሞ መተኛት አቅቷቸው ለሊቱ ከቀኑ ጋር ሊገጥምም ይችላል፡፡ አንዳንድ ወላጆች የሚያግዝ ዘመድ፣ አያት ወይም ሞግዚት ይኖራቸዋል፡፡ ብዙ ባሎች ይህ ጉዳይ የእነሱም ጉዳይ እስከማይመስል ድረስ ጧ-ብለው ተኝተው የሚያንኮራፉ ባይጠፉም ከሚስታቸው ጋር ተራ የሚገቡ ባሎች መኖቸውም አይካድም፡፡
እውነታው ህፃናት ከተወላዱ ጀምሮ ያሉት ቀጣይ ሶስት ወራት የመጨረሻው የእርግዝና ጊዜ (fourth trimester) ተብሎ ይወሰዳ፡፡ ማህፀን ለፅንሱ የማያቋርጥ እንቅስቃሴ ያለበትና መዋኛ ገንዳ አይነት ነው፡ ከተወለዱም በኋላ ታዲያ እንቅስታሴ፣ ምቾት፣ ሰላም ይፈልጋሉ፡፡
ህፃናት ከተወላዱ ጀምሮ ባሉት ተከታታይ ወራት ማንኛውንም ስሜታቸውን የመቆጣጠር ወይም እኛ በምንፈልገው መንገድ መመራት አይችሉም፡፡ ሆኖም ወራቶች እየጨመሩ ሲሄዱ ስሜታቸው እየሰከነ ወይም መስመር እየተከተለ መሄድ ይቀጥላል፡፡ የስሜት ጉዳይ አንዱ ይሁን እንጂ ህፃናት እራቧቸው፣ ታመው፣ የለበሱት ልብስ ወይም የተደረገላቸው የሽንት ጨርቅ (ናፒ/ዳይፐር) ምቾት ነስቷቸው፣ ተባይ በልቷቸው፣ ሙቀት ወይም ብርድ ተሰምቷቸው፣ ወዘተ ሊያለቅሱ ይችላሉ፡፡ ብዙ ጊዜም ባይሆን አንዳንዴ የወላጆቻቸውን (የአሳዳጊዎቻቸውን) እቅፍ፣ የሰውነት ንክኪ ወይም ትንፋሽ ፈልገው ሊያለቅሱ ይችላሉ፡፡ ይህ የሚፈጥርላቸው የደህንነት (security) ስሜት ስላለ ነው፡፡ ህፃናት ምክንያት የሌለው ለቅሶ ባይኖራቸውም ወላጅ ምክንያቱን ልብ ለልብ ተናቦ ወይም የልጆቹን ቋንቋና ስሜት ተረድቶ መለየት ሊያቅተው ይችላል፡፡ ያም ሆነ ይህ ግን ተፈጥሮ በምትመራው መንገድ ህፃናት የሚያመላክቱትን ምልክት ተከትሎ ለማረጋጋት መሞከር፣ ማባበልና ዝማሬ ወይ እ ሹ ሩ ሩ ማሰማት፣ ማጥባት፣ መዳሰስና መነካካት(መደባበስ) አይናቸው ተገልጦ ከሆነ አይናቸውን በፍቅር ማየት የተሻሉና ልጆችን ወደ እንቅልፍ ለመመለስ የሚጠቀሱ ዘዴዎች ናቸው፡፡
ሆኖም በማንኛውም ሁኔታ ማልቀስ የጀመሩ ልጆችን “ሲደክመው ይተኛል” በሚል መተው የሚመረጥ መፍትሄ አይደለም፡፡ ልጆች በሚያለቅሱበት ጊዜ ቀርቦ መደባበስ፣ ማቀፍ፣ ማጥባት፣ ወዘተ ለጊዜው ወደ እንቅልፋቸው ለመመለስ ብቻ ሳይሆን በሚረበሹበት፣ አቅላቸውን በሚጠባቸው (distress) ጊዜ ራሳቸውን እንዴት ከሚያጣብብ ስሜት እደሚያወጡ እየተማሩ ይሄዳሉ። ለምሳሌ ጡጦ ካጠገባቸው ካለ ጡጦውን ጠብተው ይተኛሉ (እንቅልፍ ላይ ሆነው መጥባት ግን አይመረጥም) ሌሎች ደግሞ ከእናታቸው የሰሙትን እንጉርጉሮ መሰል ነገር እያዜሙ ሊተኙ ይችላሉ፡፡ እንዲያለቅሱ ባሉበት ከተተዉ ግን ደክሟቸው ቢተኙም ስሜትን የማስታመም ክህሎትን ግን አይማሩም፡፡
የሆነ ሆኖ የህፃናት እንቅልፍ ከቀን ይልቅ ለሊት ላይ ለምን ይቀሰቀሳል ለምን ይበዛል? ይህ ቀደም ሲል ከጠቅስናቸው ምክንያቶች በአንዱና ከአንድ በላይ በሆኑ ምቾትን ከሚያውኩ ጉዳዮች ጋር የተያያዘ ቢሆንም አንድ ሌላ መሰረታዊ ምክንያትም ይጠቀሳል፤ ህፃናቱ ከወላጅ (አሳዳጊ) ጋር ባላቸው ቀረቤታና ትስስር ጋር በተያያዘ በተለይ ከአንድ ሰው ጋር (ከእናት፣ አባት፣ ምግዚት፣ አያት….) ቁርኝት /attachment/ይፈጥሉ፡፡ ይህም ለምሳሌ ቁርኝቱ ከእናት ጋር ቢሆን እናት ባለችበት ሁሉ ህፃኑ ደህንነት ይሰማዋል፡፡ ይች እናት ደግሞ ቀን ስራ የምትውል ከሆነ በቀሪው ጊዜ (ለሊት ላይ) ህፃናቱ ስሜታቸውን የበለጠ ትስስር ላለቸው ሰው ይገልፃሉ፤ ያንፀባርቃሉ፣ ያሰማሉ፡፡
ከዚህ በተረፈ ለሊት ላይ የህፃናት መንቃት ጤናማ ያልሆነ ክስተት አይደለም፤ እስከ ስድስትና 12 ወራት ድረስ የተለመደ ነው፡፡ በሌላ በኩል ህፃናት ራሳቸውን የሚከላከሉት በማልቀስ ነው፡፡ ሲታፈኑ ያቅሳሉ፣ ሲያማቸው ያቅሳሉ፣ ወዘተ እንዲያውም ቶሎ ከእንቅልፍ የሚነቁ ልጆች ታፍኖ ከመሞት አደጋዎች ራሳቸውን ታደጋሉ፡፡



=

Published in ላንተና ላንቺ
Saturday, 24 May 2014 15:13

የሳምንቱ ምርጥ 10

Billboard TOP 10 Albums

Turn Blue  -The Black Keys
Xscape   -Michael Jackson
NOW 50   -Various Artists
Frozen   -Soundtrack
Rewind   -Rascal Flatts
Blue Smoke   -Dolly Parton
Unrepentant Geraldines   -Tori Amos
Shine On  - Sarah McLachlan
Storyline   -Hunter Hayes
Sovereign   -Michael W. Smith




Top 10 Best Sellers  Books on Amazon
1.The Fault in Our Stars by John Green
Oh, The Places You’ll Go! by Dr. Seuss
The Conscious Parent by Dr. Shefali Tsabary
Capital in the Twenty-First Century by Thomas Piketty
One Nation by Ben Carson M.D.
Frozen Little Golden Book by Victoria Saxon
.City of Heavenly Fire by Cassandra Clare
Ultimate Sticker Book: Frozen by DK Publishing
The Goldfinch: A Novel by Donna Tartt
 Skin Game (Dresden Files) by Jim Butcher


Box Office Top 10

Godzilla
Neighbors
The Amazing Spider-Man 2
Million Dollar Arm
The Other Woman
Heaven is for Real
Rio 2
Captain America: The Winter Soldier
Legends of Oz: Dorothy’s Return
Mom’s Night Out

Published in ጥበብ
Saturday, 24 May 2014 15:13

የግጥም ጥግ

የዕድገት 10ቱ ቃላት!
አንዱ የዕድገት ትርጉሙ ጠፍቶበታል
አንዳንዱ ቁልቁል ማደግም ዕድገት ነው ይላል!
አንዳንዱ እንኳን ማደግ ከነመወለዱም ጠፍቶበታል!
አንዳንዱ እንዴት እንደሚታደግ ማወቅ ተስኖታል!
አንዳንዱ ፎቅ ይሰራ ይሰራና የሚከራይ ሲያጣ፤ “ይህ ህዝብ ዕድገት አይገባውም” ይላል፡፡
አንዳንዱ ፎቅ ሰርቶ ሰርቶ ሰርቶ ጫፍ ይወጣና “መሬት ማለት ምን ማለት ነው?” ብሎ ይጠይቃል፡፡
አንዳንዱ “ዕድገት አለ ግን ወረቀት ላይ ነው ያለው፡፡ ስለዚህ ዋናው የወረቀት ዋጋ ማደግ ነው” ይላል፡፡
“አንዳንዱ ዕድገት ማለት ሌሎች ሲያድጉ ማየት ነው፡፡ ስለዚህ የድንኳን ሰባሪ እድገት ነው”! ይላል
አንዳንዱ እድገት ማለት ከዚህ ወዲያም ለምን እንዳላደግን ማሰብ ነው፡፡ በቃ ካሰብክ የግድህን ታድጋለህ” ይላል፡፡
አንዳንዱ ግን ጥብስቅ አድርጎ… አድጎ… አድጎ ከአቅሙ በላይ ተመንድጎ ማደጉን ማቆሙ ጨንቆት “ብቻዬን አድጌ እስከመቼ! የሚያግዘኝ ይቅር የሚቃወመኝ እንዴት ይጥፋ?
የኔን ፎቅ ማየት ካልቻለ
ጎጆው ሲፈረስ ይማር የለ?”
በቃ ዛሬ ገና ይግባው
ቦታ ቀይሮ ሲሰፍር ለውጥም ዕድገትም የሱው ነው፡፡
ግንቦት 2006 ዓ.ም (ለአፍቃሬ ዕድገቶች)

Published in የግጥም ጥግ
Page 7 of 21