Saturday, 30 November 2013 11:12

የድሬዳዋ የጉዞ ማስታወሻዬ!

ባለፈው እትም ከአቶ ብርሃነ የድሬዳዋ አክሽን የበጐ አድራጐት ማህበር ሰብሳቢ ጋር ውይይት ስንጀምር ነበር

ያቆምኩት፡፡ ከዛው እንቀጥል፡፡
“ምንድነው exactly (በትክክል) የምትፈልገው?” አሉኝ አቶ ብርሃነ፤ የማህበሩ ሰብሳቢ፡፡
እኔም፤ “ቢፈልጉ ስለራስዎ፣ ቢፈልጉ ስለ ድሬዳዋ፣ ቢፈልጉ ስለ ጄክዶ፣ ቢፈልጉ ስለማህበርዎ… የፈለገዎትን ይንገሩኝ!

ለጽሑፍ እሚመቸኝ እንደሰው ካወራን ነው” አልኩዋቸው፤ በአክብሮትም፣ በፍቅርም፡፡
“ከእኔ ልጀምር …እኔ ብርሃነ ጐበና እባላለሁ፡፡ ኢትዮጵያዊ ነኝ!... ያለሁት ድሬዳዋ ነው፡፡ (ድሬደዌ ነዎታ! አልኩ በሆዴ)

የሙያ መሠረተ - ጥናቴ የማህበረሰብ ልማት ነው፡፡ በኃ/ሥላሴ ጊዜ የመጀመሪያ ኮሙኒቲ ዴቬሎፕመንት ኢንስቲቲዩት

ተቋቁሟል፡፡ አዋሳ የህዝብ ዕድገት ተቋም፡፡ ብዙ ፕሮፌሰሮች… እነ ፕሮፌሰር ሥዩም፤ እነ ፕሮፌሰር እንዳልካቸው ወዘተ.

ነበሩ ያኔ፡፡ እኔም አንዱ ባልደረባ ነበርኩ፡፡
“የዱሮው ትውልድ ነዎታ! እኛ የድንጋይ ብርጭቆ ትውልድ የምንለው ነው” አልኳቸው፡፡
“መጀመሪያ፤ የሠራሁት ደግሞ ጋሽና ሰቲት ሰሜን ኤርትራ። ያኔም ኢትዮጵያዊ ነኝ” አሉ - የህዝብ ዕድገት ሹም”፡፡
እኔ ሳቅኩኝና፤ “Great!” አልኩ፡፡
“ከዚያ የተለያየ ቦታ ሠርቼ፣ በመጨረሻ ጡረታ ወጥቼ ወደ ድሬዳዋ ስመጣ፤ ሲ.አር.ዲ.ኤ ነበር እዚህ - NGOዎችን

የማስተባበር ሥራ ይሠራ ነበር፡፡ እስከ አፋር ድረስ ይንቀሳቀሳል፡፡ የCRDA አባላት የነበሩም ያልነበሩም ድርጅቶች

መረብ እየተዘረጋ ነበር፡፡ አቅም እየገነቡ፣ ከመንግሥት ጋር ከኮሙኒቲም ጋር ይሠራሉ፡፡ ሥልጠናም ነበር፡፡ እዚያ ገባሁ።

ሠፊ መረብ ተዘረጋ፡፡
ከእየሩሳሌም የህፃናትና ማህበረሰብ ልማት ድርጅት ጋር የተዋወቅነው ይሄኔ ነው! እዚህ ድሬዳዋ ላይ በተቋቋመው ፎረም

ውስጥ ካሉት ድርጅቶች አንዱ ጄክዶ ነው - እህማልድ። እኔ ፀሐፊ ነኝ የፎረሙ፡፡ (አፋር፣ ድሬዳዋ፣ ሐረሬ ነው) ጄክዶ

እዚህ አካባቢ በጣም ጥሩ ሥራዎች ነበር የሚሠራው! የአቅም ግንባታ ሥራ ይሠራል፡፡ አሳዳጊ የሌላቸው ህፃናት ላይ

ይሠራል። አረጋውያን ላይ ይሠራል - በድሬዳዋ፡፡ ድሬዳዋ  Drought – Prone (ለድርቅ ተጋላጭ)  ከሚባሉት

አካባቢዎች አንዷ ናት። ጐርፍ የሚያጠቃት አካባቢ መሆኗ በጣም የተረጋገጠ ነው፡፡ ይህንን ለመመከት ጄክዶ እጅግ

በጣም ሰፊ ሥራዎች ይሠራል፡፡
የአውሮፓ ህብረት/ የአውሮፓ ኮሚሽን  (EU/EC) ጥያቄ ያቀርባል ስለ Community Based Organizations at a

grass root level ማህበረሰብ -አቀፍ ድርጅቶችን በመሠረታዊ ወለል ደረጃ ማቋቋም፡፡ ማህበረሰብ አቀፍ ድርጅቶች

በጋራ ሆነው ችግራቸውን የሚፈቱበት መንገድ እንዲፈጠር ሃሳብ ይቀርባል ይረቀቃል፡፡ ቀጥታ ተጠቃሚ ራሱ ማህበረሰቡ

እንዲሆን ነው፡፡ ፈንዱ እዛ ላይ ይውላል፡፡ እንደምታውቀው የድሬዳዋ ህዝብ ተግባቢ ነው፣ አዲስ ነገር በቀላሉ

ይገባዋል፤ ምንም ዓይነት ሥራ ተባበር ሲባል ፈጣን ምላሽ ይሰጣል (Socializes, Understands, Cooperates)

በቀላሉ ማህበራዊ ትሥሥር ይፈጥራል፡፡ ይገባባል፡፡ ይተባበራል፡፡ ፓይለት pilot እናርግ የሚል ሃሳብ ተያዘ፡፡

ፕሮጀክቱን ቀርፆ እዚህ መጣና ተወዳድሮ ጄክዶ አሸነፈ፡፡ ይሄኔ እኔ ብቅ አልኩ!
መሠረቱ ራሱ ማህበረሰቡ ሲሆን ልባዊ ልማት ላይ ያተኮረ ይሆናል! አባት እናት አጥተው የተቀመጡ ህፃናትን የእገሌ

ልጅ ከእገሌ ልጅ ብሎ የባሰበትን ተቸጋሪ መርጦ ይረዳል፡፡ አቅፎ እንደእናት እንደአባት እያየ ያሳድጋል፡፡ እኛ አለን

ይላል፡፡
በህይወት ያለውን ማገዝ፣ ሽማግሌውን መጦር፣ ማሳከም፣ ማህበረሰብ - አቀፍ ድርጅት (CBO) እንግዲህ አስፈላጊ

የሆነው ይህንን ለመሥራት ነው፡፡ ይህንን ለማቋቋም ጄክዶ ያገር ሽማግሌዎችን ጥሪ አድርጐ ድሬዳዋ ላይ በዚህ

መጥቻለሁ፤ አለ፡፡ እንዳልኩህ የድሬዳዋ ህዝብ፤ ለውጥ ተቀባይ፣ የሚገባው፣ መደራጀት የሚችል ህዝብ ነው፤ ብለን

መጥተናልና ምን ትላላችሁ?” አለ፡፡ ጥሪ አደረገ፡፡
“እኛኮ የሚያስተባብረን አጥተን ነው!” ሲል ምላሽ ህዝቡ ሰጠ፡፡  አያያዝ ሳይችል ቀርቶ ልጆች አላሳደጊ፣ ሥራ ፈት

ወጣት፣ ወደአልባሌ ቦታና ማጅራት መቺነት እያመራ አደለም እንዴ? አንድ አርጐ እሚያሠራን፣ እሚያደራጀንና መንገድ

እሚያሳየንማ ካገኘን ምን ገዶን?” የሚል መነሳሳት ተገኘ! “እስቲ እናዋጣ፤ አንድ ሁለት ልጅ አሠልጥነን ሥራ

ብናስይዝ…አንዱ አሳዳጊ ጥሩ ሲሆን፣ ሌላው ደህና አሳዳጊ ስላላጋጠመው ከሚጐዳ፤ በጋራ ብናደርገውስ የሚል ነው

መሠረቱ አድልዎ - አልባ fair የሆነ distribution የሀብት - ክፍፍል፡፡ ሰው ተደሰተ፡፡ አመራሩን ተቀበለ፡፡ ጄክዶ

እዚህ ቢሮ ሰጠን እንድናደራጅ፡፡ ዕድሮች፣ ኮኦፕሬቲቭ፣ ቻሪቲም አሉ፡፡ 70፣ 80፣ የሚሆኑ አደራጅ ኮሚቴ መረጡ፡፡

በከተማው ዘጠኝ ቀበሌ ነው ያለው፡፡ ከዛ የተውጣጡ ናቸው፡፡ ቢያንስ በየቀበሌው ሁለት ሁለት ተወካይ 20 ሰዎች።

ህጋዊ የሆነ ያልሆነ፣ የተመዘገበ ያልተመዘገበ፣ አቅም ያለው የሌለው፡፡ በባህላዊ አሠራሩ ውስጥ ያለ ያመራር ችግር ነበር፡፡

መዝገብ የለም፣ ሂሳብ የሚሠራ ሰው የለም ወዘተ…ከዛ ሥልጠና ሰጠን፡፡ በመንግሥት ታወቁ፡፡ ታማኝነት ተፈጠረ፡፡

መዋቅር ተዋቀረ፡፡ ትልቅና ጠንካራ ሆኑ፡፡ ገና በሥልጠናው ሲታይ የልምድ ልውውጥ ከናዝሬት፣ ከደብረዘይት፣ ከአዲሳባ

ተደረገ፡፡
በነዛ ዓይነት ህብረት መፍጠር ተቻለ፡፡ 47 ዕድሮች አሁን 54 ደርሷል ተደራጁ፡፡ በዩኒቨርሲቲ በተጠኑ ጥናቶች

ከመንግሥት ጋርና በራሳቸው ውስጥ ምን ዓይነት መልክ ይኑራቸው? በሚል ተጠና፡፡ System Develop ማኑዋሎች

ተዘጋጁ፡፡ ሥርዓት ያለው መዋቅር ኖረ፡፡ ተመሳሳይ ሥራዎች ይሠራሉ፡፡
ዕድሮች ህፃናትን ያሳድጋሉ፡፡ በጤና ላይ ይሠራሉ፡፡ ጐርፍ ይከላከላሉ፡፡ ኮኦፕሬቲቭስ አሉ፡፡ በትምህርት ላይ ይሠራል።

በምን ደረጃ ላይ ናቸው? ሲባል፤ ይለያያሉ፡፡ Diversified ናቸው፡፡ ሲቪል ሶሳይቲ ናቸው Communication

Network ያስፈልጋል፡፡ በልዩ ልዩ ተግባራት ዙሪያ የተሰባሰቡ ቡድኖችን (Cluster of activities) ማቋቋም አስፈላጊ

መሆኑን አመን፡፡
ሲቪል ሶሳይቲ ናቸው ሁሉም የትምህርት፣ የጤና፣ አካባቢ ጥበቃ ወዘተ፡፡ Network ግን የለንም፡፡ ስለዚህ በይዘት ላይ

የተመሠረቱ ስብስቦች (thematic clusters) ደረጃ፣ partners (አጋር) እንዲሆኑ ማድረግ ዓይነተኛ መንገድ ሆነ፡፡

በመጀመሪያ እንግዲህ ጄክዶ ለዚህ ገንዘብ ሰጠን - ማስጀመሪያ ነው!
የሚያስፈልጋቸውን ነገር፣ ዐይነትና መጠን ዴንማርክ፣ አየርላንድ፣ እንግሊዝ፣ ሆላንድና ኖርዌይ ያሉበት የሲቪል

ማህበረሰብ ፕሮግራም አቋቋምን፡፡ አዲስ ተግባር አመንጪ  (Innovation Action) ተብሎ የተወሰደ ነው፡፡ ወደ

ህብረተሰቡ የሚወርድ ሆኖ፣ በስብስቦቹ መዋቅር የሚመራ ነው፡፡ ተጠንቶ ነው፡፡ 9 ቀበሌዎች ናቸው፡፡ በተግባር ሲታይ

ገጠር ለመሄድ አቅም የለም፡፡ ባጃጅ አለችን፡፡
ዘለቄታው አላቂ ማቴሪያሎች ላይ ነው ጉዳዩና ራሱን በራሱ እሚችልበትን መንገድ ሽተናል፡፡ ለዚች ፕሮግራም

የሚያስፈልገው ዳቦ ቤት ነው? ሽመና ነው? መክፈት ያለበት ወዘተ እያልን ቋሚ ነገር እያሰብን ነው፡፡ እንዳልኩህ ነው።

በልመና ከሆነ፣ ልብሷ ታልቃለች፣ ደብተሯም ታልቃለች፣ ስለዚህ እየለመንክ ዘላቂነት የለም፡፡ 2011 መጨረሻ ላይ

ጀምረን ነው የቀረጽነው፡፡ ስኬታማ ሆነናል በ2013!”
“ዕድሮችን ማግኛ መንገዳችሁ ምንድን ነው?”
“ቦርድ አባላት አሉ፡፡ በየ2 ዓመቱ የሚቀየሩ፡፡ በየቀበሌው ያሉ የኛ አባላት የራሳቸው ፕላት ፎርም አላቸው፡፡ ያላቸው

ችግር ካለ፣ ከመንግሥት ጋራም መወያያ፤ የራሳቸው መድረክ አላቸው። እዛ ሲሰሩ ከመንግሥት ጋር ነው፡፡ ማነው

መንግሥት? ቀበሌ ነው፡፡ ከመንግሥት ጋር በጋራ እንሠራለን፡፡ ስለዚህ በስብስብ  ኮሚቴዎች እንገናኛለን፡፡ ዕድር፣

ቀበሌ፣ cluster ኮሚቴ ያረጋግጡልናል፡፡ አሁን ባጃጅ የሚነዱ ስልጠና ላይ ነን
ምንም ሳይኖረን ሠርተናል! አሁን የተሻለ መሥራት እንችላለን፡፡ ቀስ በቀስ ነው እዚህ የደረስነው፡፡
“ስንት ዓመትዎ ነው” አልኳቸው ስለማንነታቸው ላውቅ፡፡
“68”
“በጣም ጠንካራ ነዎት ማለት ነው!”  
“የተፈጥሮ ችግር አያስቀምጥህም፡፡ ጋቢና ጭራ ይዘህ ቤትህ ከመቀመጥ ይልቅ፤ እዚህ መሥራት፤ ህይወትህን

ያድስልሃል፡፡ አንዳንድ ሰው ጡረታ ትወጣለህ ሲባል መንፈሱ ይወድቃል! እኔ አመመኝ ማለት አልወድም! ተጓዳኝ

ሥራዎች አሉን፡፡”
“ጄክዶ ያግዛችኋል አሁንም?”
“Phase – out አርጓል ግን አሁንም ኮንታክት አለን፣ አሁን የህብረተሰብ እግር ኳስ አለ፡፡ አለንበት፡፡ ፈንድ ተገኝቷል

ወጣቶችን ያገናኛል፡፡ የሶስት ሪጂኖች ነው - ሐራሪ፣ ሱማሌና አፋር፡፡ የሰላምና የአንድነት ፕሮጀክት ነው፡፡ ጄክዶ

ወሰደው። ለእኔ ሰጠኝ፡፡ ባገር ሽማግሌዎች ለነዚህ ወጣቶች ትምህርት ይሰጣል፡፡ ፓንፍሌት ይበተናል፡፡
ትምህርት  በእግር ኳሱ በእረፍት ጊዜ ይሰጣቸዋል ወዘተ የኦሮሞ፣ የአማራ፣ የደቡብ፣ የሱማሌ፣ የአፋር ከተለያዩ የብሔር

ብሔረሰቦች የተውጣጡ ናቸው፡፡ በየቋንቋው ነው የሚቀርብላቸው፡፡ ገና 3ኛና 4ኛ ዙር ይቀራል፡፡ ወንድማማቾች

መሆናቸውን ይማማሩበታል፡፡ ሌላ ደግሞ፤
Ethiopian. social accountability የሚባል ፕሮግራም አሁንም ከጄክዶ ጋር አለ፡፡ ለገጠር ፤ ውኃ፣ ፅዳት፣ ጤና፣

ትምህርት… የኢትዮጵያ መንግሥት ከዓለም ባንክ የሚያገኘው ፈንድ ነው ህዝቡ የራሱ ማድረጉን እናያለን፡፡ መንግሥት

እና ኮሙኒቲ መመዘን አለበት! ሸንጐl አቋቁመናል፡፡ ተጓዳኝ ሥራዎች ተቋቁመዋል፡፡ የአረጋውያንና የደካማ ሰዎች

ፌዴሬሽን በኢትዮጵያ ደረጃ ይቋቋማል! ወደፊት ወደ አገር አቀፍ ደረጃ እናሳድጋቸዋለን፡፡
“EDDC የብርሃነ ጐበና ታላቅ ፍሬ ነው፡፡ በ68 ዓመት እንዲህ ያለ ሥራ ከባድ ነው፡፡ ለመሆኑ እነዚህን ሁሉ ኮሚቴዎች

ለመምራት ጊዜ ይበቃዎታል?”
“አይ የፕላኒንግ ጉዳይ ነው እንደዚህ እንዳሁኔ ድንገተኛ ነገር ሲያጋጥም ነው እንጂ እስካሁን በእቅዴ ሐዲድ ላይ ነው

እየሄድኩ ያለሁት፡፡ በጥንቃቄ ነው የምይዘው፡፡ በሁለት ሣምንት ወይም በወር አረጋግተህ ትይዘዋለህ፡፡ የምክር ቤት

አባል ነኝ… የሰፈሬ ዕድር አባል ነኝ… አቀናጃቸዋለሁ… የራሳችን ከሆነ በአጀንዳችን ይሠራል!...”
“ስንት ልጆች አሉዎ?”
“አምስት አሉኝ ሁሉም ደህና ናቸው፡፡ ራሳቸውን ችለዋል፡፡ ሥራ ላይ ናቸው፡፡ አንዱ ጐረምሳ አለ… አሁን ነው

እሚጨርሰው፡፡ ባለቤቴም ሠራተኛ ነች፡፡ በሥራ ጉዳይ አዲሳባ ነች፡፡ እኔ እዚህ ነኝ፡፡ በፕሮሞሽን ነው የሄደችው፡፡ ያ

ደግሞ አይጠላም - የማኔጅመንት ሰው ነች እዛ”
“ማህበራዊ መስተጋብሩዋ  እንዴት ነው?”
“የሚገርም ነገር ነው፡፡ ባልና ሚስት ካንድ ውሃ ይቀዳል ነው…ፖስታ ቤት ስሄድ እትዬ ደህና ናት እያሉ ተጠምጥመው

ይስሙኛል”
“ኢትዮ - ውስጥ ያላዩት ቦታ አለ?”
“ባሌና ኤሊባቦር”
ሥራ አስኪያጁ  ይሄኔ መጣ፡፡
“ባሌን ኮፈሌን አላውቃትም አሉኝኮ አቶ ብርሃነ?” ስለው፤
“ኮሙኒቲ ዴቬሎፕመንት ምንጩ እዛ ነው፡፡ ሐረርጌ The moving Atlas ይባላል፡፡ ዋናው ነገር ሐረርጌ ነው፡፡”
“ጐሙጐፋን በብዙ ሠርቼበታለሁ” አሉ አቶ ብርሃነ፡፡
ደራሲው ፀጋዬ ገ/መድህን፤  “በከርሞ ሰው” ላይ፤ አብዬ ዘርፉ “እቺን ሠርቼባታለሁ” ይላሉ፤ ግድግዳ ላይ

ወደተሠቀለችው ጠመንጃ እያሳዩ፡፡ አቶ ብርሃነ “ሠርቼበታለሁ” ሲሉ የመጣብኝ ስሜት የዚህ አይነት ነው፡፡
“እዚህ አገር እርግጠኛ የማትሆንበት ነገር (Uncertainty ው) ብዙ ነው፡፡ ወዳጄ ለትራንስፖርት መኪና ላይኖር

ይችላል። መኪናው ሲገኝ ጐማው ተበላሽቷል - መቀየር አለበት፡፡ ጐርፉ ራሱ አንድ Uncertainty ነው” አለ፡፡
ፀጋዬ ገብረመድህን “እንኳን ለዓመት ጉድ አበቃን” የሚል ግጥም አለው፡፡ የፍልውሃን ዓመታዊ ጐርፍ መጥለቅለቅ

አስመልክቶ የፃፈው ነው፡፡ ምነው የድሬዳዋን ጐርፍ ባየና በፃፈ” አልኩ፡፡
እኔም የድሬዳዋውን አስመልክቼ አንድ ግጥም ጽፌአለሁ። ቆይ ሁለቱንም ግጥሞች ለአንባቢ አቀርባቸዋለሁ  አልኩኝ

በሆዴ!
(የድሬዳዋ  ጉዞዬ የመጨረሻው ክፍል ይቀጥላል)

Published in ባህል
Saturday, 30 November 2013 11:10

“ብቻዬን ነኝ ፈራሁ…”

እንዴት ሰነበታችሁሳ!
አዎን ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እሸሸግበት ጥግ አጣሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ
እማማ ኢትዮዽያን መንፈሴ ተፈቶ እንዳይፈታት ሰጋሁ
ብሎናል ሎሬት ጸጋዬ በአቡነ ዼጥሮስ አንደበት። ከብዙ ዘመናት በኋላም “እሸገግበት ጥግ አጣሁ…” የሚያሰኝ መከራ

ሲወርድብን ያሳዝናል፡፡ እንጀራ በየሰዉ አገር እያንከራተተን የየዕለቱ ግፋቸው አልበቃ ብሎ “መቅደስ እንደገባች ውሻ…”

መንገድ ለመንገድ ሲያሳድዱንና በነፍስ ደርሶ “አይዞህ የአገሬ ልጅ፣ አለሁልህ…” የሚል ስናጣ… አለ አይደል… ምነዋ

“እሸገግበት ጥግ አጣሁ... አንል!
የጠጣሁት ጠጅ ምን አላረገኝ
እንጀራው አዙሮ በሰዎች ፊት ጣለኝ
ይሉ ነበር አባቶቻችን፡፡ አዙሮ እየጣለን ያለው ‘እንጀራ’ ነው፡፡ ለበረሀ ወንበዴ፣ ለባህር አውሬ፣ ለከተማ ‘ባሪያ ፈንጋይ’

ሲሳይ ያደረገን በቁራጭ እንጀራ የአንጀታችንን ጩኸት እናስታግሳለን ብለን ነው፡፡ በኢምግሬሽን በር ላይ ቁርና ብርድ

እየተፈራረቀብን ተሰልፈን ውለን እንድናድር የሚያደርገን ‘እንጀራ’ ነው፡፡
አንድዬ አገር ለአገር የመንከራተት ዘመን ይብቃችሁ ይበለንማ!
በዕውቀት ሳይሆን በዘይት ትከሻቸውን ያሰፉ፣ ጎናቸውን ያደነደኑ፣ ከእኛ በላይ ለአሳር በሚሉ፣ በገንዘባቸው ኃይል

መንግሥታትንና ሚዲያዎችን ‘በኪሳቸው በከተቱ’ የሳውዲ ባለ ጊዜዎች ያ ሁሉ መከራ የደረሰባቸው ወገኖቻችን ዋነኛው

‘ወንጀላቸው’…እንጀራ መፈለጋቸው ነው፡፡
የእናት አገር ቀሚስ የአባት አገር ሸማ
ነጠላ አይደለም ወይ የሰው አገርማ
ይባላል፡፡ የሰው አገር ነጠላ ለሆነባቸው ወገኖቻችን አንድዬ ይብቃችሁ ይበላቸውማ!
ተባረው ወደ ሀገራቸው የተመለሱ 30 የፊሊፒንስ ሠራተኞች አገራቸው ሲገቡ የደረሰባቸውን ተናግረዋል፡፡ አንዷ “እንደ

እንስሳ ነው የሚቆጠሩን…” ነበር ያለችው፡፡ ለእኛ ዜጎችም ያላቸው አመለካከት ይኸው እንደሆነ ስንሰማ ኖረናል፡፡

በሰሞኑ ቪዲዮዎችም ላይ ስድቦቻቸውን ሁሉ ሰምተናል፡፡
እንዲህ ሁሉ ሲሆን ፈጥኖ … “አይ አሁንስ ወጥ ረገጣችሁ…” የሚል ‘ጋሻ’ ማጣታችን ያሳዝናል፡፡
እናላችሁ..እነኚሁኑ የፊሊፒንስ ዜጎች ለአራት ቀን አስረዋቸው ከቆዩ በኋላ ወደ አውሮፕላን ጣቢያ ሲወስዷቸው

እግሮቻቸውን በሰንሰለት አስረዋቸው ነበር፡፡ መካከለኛው ምሥራቅ ያሉ አንድ የእስልምና ኃይማኖት አባት “እነዚህ

ሙስሊሞች እስልምናን የተማሩት የት ነው? እስልምና በሠራተኞች ላይ እንዲህ አይነት ድርጊት አይቀበልም፡፡  

ሠራተኛውን  በሚደበድብ ላይ በፍርድ ቀን በቀል ይወሰድበታል፣” ብለዋል፡፡
ይሄኔ ነው “ነጠላ አይደለም ወይ የሰው አገርማ…” የሚያሰኘው፡፡ እና በርካታ ወገኖቻችን ‘እንጀራ’ እያንከራተታቸው

ይህንኑ እያሉ ነው፡፡
‘ኤዥያ ኒውስ’ የተባለ ዜና ምንጭ ባለፉት 12 ዓመታት ሳውዲ ዓረቢያ ውስጥ በአስቸጋሪ የሥራ ሁኔታዎችና የጉልበት

ብዝበዛ የተነሳ ከ3000 በላይ የኔፓል ዜጎች ህይወታቸውን አጥተዋል ይላል። አብዛኞቹ ህይወታቸው የሚያልፈው

በድብቅ በሚጠመቁ የአልኮል መጠጦች ነው ይላሉ፡፡ ወደ መጠጥ የሚገፉትም እጅግ አስቸጋሪ የሆነውን የሥራ ሁኔታ

መቋቋም እያቃታቸው በብስጭት ነው ተብሏል፡፡ በአልኮል የተነሳ በየወሩ ከ30 በላይ ሰዎች ይሞታሉ ተብሏል፡፡
እናላችሁ…ለመሆኑ ሳውዲ ዓረቢያም ሆነ ሌሎች የዓረብ ሀገራት ሄደው እንደወጡ የሚቀሩ ዜጎቻችንን ሁኔታ

የሚከታተለው ማን ነው? እዚህ እንደምንሰማው በተለያዩ ህገወጥና ተግባራትና ብልሹ ምግባሮች ውስጥ ይገባሉ

የሚባሉት ምክንያታቸውን ተከትሎ የሚጠይቃቸው ማን አለ?
ፊሊፕንሶቹ በየአገሩ በርካታ ኤጀንሲዎች ስላሏቸው የእያንዳንዱን ዜጋቸውን ዕጣ ፈንታ ይከታተላሉ፡፡ የምር ግን…መቼ

ነው እኛስ በየምንሄድበት የሰው አገር “በጎ አደርክ ወይ?” “የከፋሀ ነገር አለ ወይ?”  የሚሉን ‘የአገር ልጅ’ ተቋማት

የምናገኘው! መቼ ነው ገንዘብ ማግኛና ማስገኛ ብቻ መሆናችን ቀርቶ እኛ ራሳችን በምንም አይነት ዋጋ የማይተመን

ሰብአዊነት ያለን የአንዲት ታላቅ የነበረችና ከዕለታት አንድ ቀን ታላቅነቷን የምትመልስ አገር ዜጎች መሆናችንን የሚያምኑ

‘አድራጊ፣ ፈጣሪዎች’ የምናገኘው?
ሌላው የእኛ ችግር ‘ጉዳዩ እንዳይደለ’ ማወቁ አሪፍ ነው፡፡ በቀደም ቢቢሲ ‘Have Your Say’ ፕሮግራም ላይ ጋዜጠኛዋ

ስለእኛው ጉዳይ እያወያየች ነበር፡፡ እንግዶቿ ሁለት ኢትዮዽያውያንና አንዲት የሳውዲ ሴት ነበሩ፡ እናላችሁ…የቢቢሲዋ

ጋዜጠኛ በጣም ስትደጋግመው የነበረው ነገር የሚታዩት ቪዲዮና የፎቶ ምስሎች “ያልተረጋገጡ…” መሆናቸውን ነበር፡፡

“ያልተረጋገጡ…” መሆናቸውን መግለጹ በጋዜጠኝነት ስነ ምግባር ተገቢም ትክክልም ነው፡፡ ጨዋታዋ ያለው የቱ ላይ

መሰላችሁ… ተደጋግመው እዛው በዛው የሚታዩ  ምስሎችን ደጋግሞ “ያልተረጋገጡ…” ማለቱ ላይ ነው፡፡ (ድሮስ

እንግሊዝ! ቂ…ቂ…ቂ…)
አንደኛው ኢትዮዽያዊ በጉዳዩ ላይ በዝርዝር ሀሳቡን እየሰጠ እያለም ስለተካሄዱት የተቃውሞ ሰልፎች አንዳንዶቹ የኃይል

ተግባራተ የታዩባቸው  (‘ቫዮለንት’) ነበሩ አለች፡፡ እዚህ ቦታ ትልቁ ስዕል ያለው በሳውዲ በዓለም ህዝብ ፊት እየተፈጸመ

የነበረው የጭካኔ ተግባር ሆኖ ሳለ፣ ዓቢዩ ጉዳይ ለሌሎች ሲሆን በሚጢጢው ነገር ‘ያዙኝ ልቀቁኝ’ የሚሉት የዓለም

አቀፍ ሚዲያዎች ‘ጭምትነት’ ሆኖ ሳለ፣ የተቃውሞ ሰልፎቹ ቢሆኑም አብዛኞቹ ፍጹም ሰላማዊ የነበሩ መሆናቸው ሆኖ

ሳለ፣ አንዳንድ ቦታ ስሜታቸው ንሮ ራሳቸውን መቆጣጠር ያልቻሉ ግለሰቦችን ነቅሶ ማውጣቱ ‘ጨዋታ’ ይኖረዋል ብሎ

ማሰቡ ብልህነት ነው፡፡ (ድሮስ እንግሊዝ! ቂ…ቂ…ቂ…)
መጨረሻ ላይ ሀሳቡን ይገልጽ የነበረው ኢትዮዽያዊ ሌላ ጊዜ እንደሚደረገው የሁለትና ሦስት ደቂቃ ማሳሰቢያ

ሳይሰጠው፣ ሀሳቡን በአጭሩ እንዲያጠቃልል ሳይነገረው የጀመረውን ዓረፍተ ነገር እንኳን ሳይጨርስ መሀል ላይ

መቁረጡ ጨዋታ ሊኖረው ይችላል ብሎ ማሰቡ ክፋት የለውም፡፡
ስሙኝማ…ይሄ ከሁሉ ነገር ጀርባ ምስጢር የመፈለግ ‘ኮንስፒሬሲ ቲየሪ’ የሚሉት ነገር ብዙም አያስደስተኝም፡ ግን ዓለም

አቀፍ ሚዲያዎች ስለ እኛ በሚዘግቡበት ጊዜ ከ‘ሽፋኑ ስር’ (Between the lines… እንደሚሉት) ማንበብ፣ መስማትና

ማየት አሪፍ ነው፡፡
‘እውነት እውነት እላችኋለሁ’… ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችን በተመለከተ ብዙ ወዳጆች የሉንም፡፡
አንዱ የሰብአዊ ድርጅት ድረ ገጽ የኢምፔሪያሊስቱ መገናኛ ብዙኃን…የሳውዲው አገዛዝ ለሚፈጽመው ጭካኔ ዝምታን

መርጠዋል” ሲል ይከስና እነሱንም “ወንጀሎኞች” ይላቸዋል፡፡
ዝም ያለው ዘመዴ እኔ ሳጣጥር
ሞተ ቢሉት መጣ አልቅሶ ሊቀብር፡
…….
እንዲህ አልኩት ዘመድ የተባለውን
ታምሜ ነበረ ሳጣጥር ማዘን
“አሁን ክንዴ ቀኝ እጄ ቢሉኝ
“አሁን የእናቴ ልጅ ወንድሜ ቢሉኝ
“ከሞትኩኝ በኋላ ምንም አይገባኝ፡
“ይልቅ ልተኛበት አታደንቁረኝ”
ይህን ተናግሬ አንጀቴን አርሼ
ወደ መጣሁበት ሄድኩኝ ተመልሼ፡፡
ይላሉ መንግስቱ ለማ፣ ለማዳን ወደኋላ የመቅረት፣ ለመቅበር የመትጋት ልምዳችንን ሲኮንኑ፡፡ የሆነውን ምንም ማድረግ

አይቻል ይሆናል፡፡ ነገ፣ ከነገ ወዲያ ዜጎቻችን በባእድ ሀገራት መንገዶች ላይ ተደፍተው እንድናይ፣ የዘርአይ ደረስ ልጆች

በባእድ አገራት አደባባዮች እየተሳደድን አናት አናታችንን ስንባል እንዳናይ ምን ማድረግ እንዳለብን ብንመክር ብልህነት

ነው፡፡
እናላችሁ...ከሁሉም በላይ ግን በወገኖቻችን ስቃይ ‘ጩኸታቸውን ለመቀማት’ የሚደረጉ የሁሉም ወገኖች ‘ሂሳብ

ማወራረጃ’ አይነት  ‘ፖለቲካዊ እገታዎች’ የሚያሳዩት አገር ወዳድነት ሳይሆን ራስን ወዳድነት ነው፡፡
እሺ- በለኝ እሺ እሺ በለኝ
እንቅልፍ ይውሰደኝ፣ እንቅልፍ ይውሰደኝ
አሉ ብርሀኑ ድንቄ በ‘አልቦ ዘመድ’፡፡
የሰሞኑን አይነት ሰቆቃዎች የማናይበትና ሰላማዊ እንቅልፍ የምንተኛበትን… “እንቅልፍ ይውሰደኝ፣ እንቅልፍ ይውሰደኝ…”

የምንልበትን ዘመን ያፍጥልንማ!
አዎን ብቻዬን ነኝ ፈራሁ
እሸሸግበት ጥግ አጣሁ
እምፀናበት ልብ አጣሁ
እማማ ኢትዮዽያን መንፈሴ ተፈቶ እንዳይፈታት ሰጋሁ
እንጉርጉሮ የማንጎራጎሪያ ዘመናችንን አንድዬ በቃችሁ ይበለንማ!
ደህና ሰንብቱልኝማ!

Published in ባህል

(የአዲስ አበባ 22ተኛ ከንቲባ)

መጋቢት በቀድሞው ሐረርጌ ክፍለ ሀገር ኤጀርሳ ጐሮ በተባለ ገጠራማ መንደር ነው የተወለዱት - በ1928 ዓ.ም፡፡

አባታቸው በአርበኝነት ከሞቱ በኋላ፣ መንግሥት የባለውለታ ልጆችን ሰብስቦ ሲያስተምር፣ ሐረር ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ

ትምህርት ቤት ገብተው የመማር ዕድል አገኙ፡፡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁ፤ በ1945 ዓ.ም ተግባረ ዕድ

ኮሌጅ ገቡ፡፡ ሕንፃ ኮሌጅ ሲከፈት ከመጀመሪያዎቹ ተማሪዎች አንዱ ሆነው ለአራት ዓመት የሚሰጠውን ትምህርት

የተከታተሉ ሲሆን ለተጨማሪ ትምህርትም ወደ ዩጐዝላቪያ ሄደዋል፡፡ ከትምህርት በኋላ በበርካታ መንግሥታዊ መሥሪያ

ቤቶች አገልግለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ 22ተኛ ከንቲባ ሆነውም ሠርተዋል፡፡ “የፖለቲካ ፍላጐት የለኝም፤ ኖሮኝም

አያውቅም” የሚሉት ኢንጂነር ዘውዴ ተክሉ፤ አሁን የአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪዎች ፎረም ሰብሳቢ በመሆን ማህበራዊ

ተሳትፎ እያደረጉ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ ጋዜጠኛ ብርሃኑ ሰሙ ስላሳለፉት ህይወትና የሥራ ዘመን አነጋግሯቸዋል፡፡


ዩጐዝላቪያ የሄዱበትን የትምህርት ዕድል እንዴት አገኙ?
የሕንፃ ኮሌጅ ትምህርታችንን ስናጠናቅቅ የማዕረግ ሁለተኛ ተሸላሚ ነበርኩ፡፡ ለምረቃ እየተዘጋጀን እያለ የትምህርት ቤቱ

አስተዳዳሪ፤ “የውጭ አገር ትምህርት ዕድል መጥቷል፤ መሄድ ትፈልጋለህ ወይ?” ሲሉኝ ተስማማሁ፡፡ ከእኛ ኮሌጅ

ሁለት፤ ከሌሎች ቦታ የተመረጡ አራት ልጆች ተጨምረው ወደ ዩጐዝላቪያ ሄድን፡፡ በወቅቱ ዩጐዝላቪያ የኢትዮጵያ

ትልቋ ወዳጅ አገር ነበረች፡፡ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ቲቶም ብዙ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ይመጡ ነበር፡፡
በሕንፃ ኮሌጅ የተማርኩት ቢዩልዲንግ ቴክኖሎጂ ቢሆንም ተጨማሪ ትምህርትም ይሰጠን ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ታሪክ፣

ፖለቲካ ሳይንስና የኦርቶዶክስ ሃይማኖትን ተምረናል፡፡ በአገራችን ያለውን የሕንፃ አሰራር ጥበብን ለማየት የተለያዩ

አካባቢዎች እየሄድን እንጐብኝ ነበር፡፡ ጅማ፣ ሐረር፣ ጎንደር፣ ትግራይና ኤርትራ ወደመሳሰሉት ቦታዎች ሄደናል፡፡ እኔ

ለኪነ ህንፃ (አርክቴክቸር) ትምህርት ልዩ ፍላጎት ስለነበረኝ፣ ዩጐዝላቪያ ስሄድ አርክቴትር ፋኩልቲ ነው የገባሁት።

የትምህርት ጊዜ ለእረፍት ሲዘጋ የተለየዩ አገራትን እየዞርኩ እጎበኝ ነበር፡፡ ጀርመንን፣ ኦስትሪያን፣ ቡልጋሪያን፣ ሀንጋሪን

በዚያ አጋጣሚ ነበር ያየኋቸው። በ1961 ዓ.ም ትምህርቴን አጠናቅቄ መጣሁ፡፡
የት የት ሰርተዋል?
ከውጭ እንደመጣሁ ሥራ የጀመርኩት ሥራና ውሃ ሚኒስቴር በሚባል መሥርያ ቤት ነው - በሙያዩ ተመድቤ ምክትል

ዋና አርክቴክት ሆንኩ፡፡ በ1965 ዓ.ም ወደ አስመራ ተቀይሬ ሄድኩ፡፡ አብዮቱ የፈነዳው እዚያ እያለሁ ነበር፡፡ ከአብዮቱ

በኋላ ወደ አዲስ አበባ ተመልሼ ቀድሞ በነበረኝ ኃላፊነት ተመድቤ መሥራት ቀጠልኩ፡፡ ከዚያ በኋላ በተለያዩ መሥሪያ

ቤቶች እየተመደብኩ ሠርቻለሁ፡፡ የዚያ ዘመን አንዱ ችግር ሙያህም ባይሆን “ተመድበሀል። ገብተህ ሥራ፡፡ ሁላችንም

ተመድበን እየሰራን ነው ያለነው” ይባል ነበር፡፡ በዚህ ምክንያት በሙያዬ ብቻ ሳይሆን እየተመደብኩም በተለያዩ ቦታዎች

ሠርቻለሁ፡፡ በብሔራዊ ሀብት ልማት ሚኒስቴር በመምሪያ ኃላፊነት፤ በከተማ መሬት አስተዳደር በሥራ አስኪያጅነት፤

በኪራይ ቤቶች አስተዳደር ተጠባባቂ ሥራ አስኪያጅነት፤ በከተማ ፕላን በዋና ኃላፊነት፤ በምርት ዘመቻና ማዕከላዊ

ፕላን በቡድን መሪነት … በተለያዩ ቦታዎችና ኃላፊነቶች ሠርቻለሁ።
በከንቲባነት ሊመረጡ የቻሉት እንዴት ነበር?
ለከተማ ፕላንና አስተዳደር ጥናት ተሰርቶ አዋጅ እንዲወጣ ሲታሰብ የቴክኒክ ሪፖርቱን ያቀረብኩት እኔ ነበርኩ፡፡

ከተሞች እንዴት እንደሚለሙና እንደሚደራጁ ነበር ያጠናነው፡፡ በዚያ አጋጣሚ ለከንቲባነት እንድወዳደር መታሰቡን

ሰምቻለሁ፡፡ የከተማ አስተዳደር ምርጫ ሲደረግ ግባና ተወዳደር ተባልኩ፡፡ በሙያዬ ብሰራ ይሻለኛል ብዬ ተቃውሜ

የነበረ ቢሆንም “ያው ነው፤ ምርጫውን አሸንፈህ የምትገባ ከሆነ እዚያም የምትሰራው ተመሳሳይ ነው” ተባልኩ፡፡
የምርጫው ሂደት ምን ይመስል ነበር?
አዲስ አበባ ከጃንሆይ ጊዜ ጀምሮ በቻርተር ነው የምትተዳደረው፡፡ በዘመኑ የምርጫ ውድድሩ የሚጀምረው ከቀበሌ

ነው፡፡ ያንን ያሸነፉ በከፍተኛ ደረጃ ይወዳደራሉ፡፡ ከከፍተኞቹ ቀጥሎ ዞን ቢኖርም ዞኖቹ ምርጫውን የማስተባባር ሥራ

ነበር የሚሰሩት። በዚህ መልኩ ተወዳድሬ ነው ከንቲባ ለመሆን የቻልኩት፡፡  
የአዲስ አበባ ስንተኛው ከንቲባ ነዎት?
22ተኛው ነኝ፡፡ በዚህ ኃላፊነት ከ1973 እስከ 1981 ዓ.ም ድረስ ነው የሠራሁት፡፡ ሥራ ስንጀምር ቀደም ብሎ ታቅዶ፤

ጠረጴዛ ላይ ካገኘነው ሥራ አንዱ የሌኒን ሐውልት ግንባታን የሚመለከት ነበር፡፡ እቅዱ ሞዴል የተሰራለትና ብዙ ደረጃ

የተጓዘ ነበር፡፡ ሞዴሉ ሁለት ሐውልቶችን ይዟል፡፡ አንዱ የሌኒን ሐውልት ሲሆን ሁለተኛው 30 ሜትር ርዝመት

የሚኖረውና ከሌኒን ሐውልት በስተጀርባ የሚቆም የአክሱም ሐውልት አምሳያ እንደሚኖር ያሳያል፡፡ ለዚህ ሥራ ደግሞ

የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ሲመሠረት 30 የተለያዩ አገራት መሪዎች የተከሏቸው ባህር ዛፎች ሙሉ ለሙሉ ይመነጠራሉ

ይላል፡፡ በሐውልቶቹ ዙሪያ ፏፏቴ እንደሚኖርም ተመልክቷል፡፡
እኛ ሥራ ስንጀምር በእቅዱና በሞዴሉ ዙሪያ አስተያየችሁን አቅርቡ ተባልን፡፡ የአክሱም ሐውልት የአርክቴክት ሚስጢሩ

ያልታወቀ፤ የኢትዮጵያና የዓለምም ትልቅ ቅርስ ነው፡፡ ሌኒን የወዛደር መሪ ነው፡፡ ሁለቱን ነገሮች የሚያገናኝና

የሚያመሳስል ምንም ነገር የለም፡፡ ሐውልቶችን ማዳቀልም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት የሌለውና የተከለከለ ነው።

ከዚህም ባሻገር የ30 አገራት መሪዎችን ሥም የያዘ ዛፍ አጥፍቶ፣ ሌላ ታሪክ መሥራት አሳማኝ አይደለም ብለን

አስተያየታችንን አቀረብን፡፡
ሪፖርቱን ያቀረብነው ለከተማው ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ነበር፡፡ አስተያየታችንን ለሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለማርያም

እንድናቀርብ ታዘዝን፡፡ ቀጠሮ ተይዞልን ሄደን ሀሳባችንን ስንነግራቸው “እነዚህ ሰዎች የሚሉት ትክክል ነው፡፡ እኛ

በጊዜው እንደዚህ አላሰብንበትም ነበር፡፡ የሶቪየት መሪ ሲመጡ ለሌኒን ሐውልት መሥሪያ ቦታ አዘጋጁ ሲባል ነው

ቦታው ተመርጦ የመሠረት ድንጋይ የተቀመጠበት …” ስላሉ ሐውልቶቹን ማዳቀሉ ቀርቶ፤ ታሪካዊ ዛፎች ሳይቆረጡ

የሌኒን ሐውልት ተሰራ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ 100ኛ ዓመት ኢዮቤልዩ በዓልም የተከበረው በእናንተ የስልጣን ዘመን ነው፡፡ ዝግጅቱ ምን ይመስል

ነበር?  
የከተማዋን 100ኛ ዓመት የማክበር እቅድም እኛ ከመምጣታችን በፊት የታቀደ ነበር፡፡ ሊከበር የታሰበው ግን በ1976

ዓ.ም የነበረ ቢሆንም እኛ ከመጣን በኋላ ተክለፃዲቅ መኩሪያን የመሳሰሉ የታሪክ ምሁራንን በመጠየቅ ማስተካከያ

ተደርጐ በዓሉን በ1979 ዓ.ም አክብረናል፡፡ አዲስ አበባ ከአፄ ምኒልክና ከእቴጌ ጣይቱ ጋር የተያያዘው ታሪኳ የቅርብ

ቢሆንም ከአብርሐ አጽብሃና ከንጉሥ ዳዊት ጋር የሚያያዝ ጥንታዊ ታሪክ እንዳላትም ይታወቃል፡፡ ከተማዋ

የተመሠረተችበትን 25ተኛ፣ 50ኛና 75ተኛ ኢዮቤልዩ ስለማክበሯ የሚገልጽ መረጃ አላገኘንም ነበር፡፡ 100ኛው ኢዮቤልዮ

የመጀመሪያ ነበር፡፡
ለበዓሉ ምን አቀዳችሁ? ምን ተሳካ? ያልተሳካውስ?
ለበዓሉ ብሔራዊ ኮሚቴ እንዲዋቀር ስንጠይቅ፣ ከእናንተ ውጭ ማንም አይመጣም፤ ሥራችሁን ቀጥሉ ተባልን፡፡ የአዲስ

አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራው ባለቤት ሆኖ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትንና ባለሙያዎችን እያሳተፍን መሥራት

ጀመርን፡፡ እንጦጦ ማርያም ቤተክርስቲያንን ስንጐበኝ በዕቃ ማስቀመጫ ክፍል ውስጥ ብዙ ታሪካዊ ቅርሶችን ስላየን፣

ከባህል ሚኒስቴር ጋር በመተባበር እንጦጦ ላይ ሙዚየም አሰርተን ቅርሶቹ እዚያ እንዲቀመጡ አደረግን፡፡
መስቀል አደባባይ በራስ ብሩ ቤት ለተመሳሳይ አገልግሎት የሚውል ሙዚየም አደራጀን፡፡ ከቤተመንግሥት በውሰት

ያመጣናቸው ቅርሶችንና ከግለሰቦች የተበረከቱልንን ይዘን ነው ሙዚየሙን ያቋቋምነው፡፡ ከሽሮ ሜዳ እስከ እንጦጦ

ያለውን መንገድ በአፋልት ያሰራነው የመቶኛ ዓመቱን በዓል ምክንያት በማድረግ ነው፡፡ ከራጉኤል እስከ ጐጃም በር

ፍተሻ ጣቢያ ያለውን ጥርጊያ መንገድንም አስፋልት ለማድረግ አቅደን የነበረ ቢሆንም በገንዘብ እጥረት ምክንያት

አልተሳካም፡፡
ሌላው ያልተሳካልን እቅድ እንጦጦ ራጉኤል ቤተክርስቲያን አጠገብ፣ አዲስ አበባንና በዙሪያዋ ያሉ አካባቢዎችን

የሚያሳይ ማማ ሬስቶራንት መስራት አለመቻላችን ነው፡፡ 50 ሜትር ከፍታ ያለውን ሕንፃ ለመሥራት ከማሰብም በላይ

የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦለት ነበር፡፡ ቦታውን የመረጥንበት ምክንያት አፄ ምኒልክ ከባለስልጣኖቻቸውና ከአገር

ሽማግሌዎች ጋር ተቀምጠው የሚመክሩበት መስክ መሆኑን ስለተነገረን ነበር፡፡
ቦታው ላይ ለሕፃናት መዝናኛ አምባ የመሥራት ዕቅድም ነበረን፡፡ ይህም አልተሳካም፡፡ ከተሳኩልን ሥራዎች ሌላኛው

ለከተማዋ ስድስት አዳዲስ ፓርኮችን አዘጋጅተን ማስመረቅ መቻላችን ነው፡፡ ሐምሌ 19፣ ፒኮክ፣ የካ ማካኤል፣ መርካቶ

ራጉኤል፣ ጐላ ሚካኤል መናፈሻ ቦታዎች የዚያ ዘመን ውጤት ናቸው፡፡ አራቱ የመናፈ ቦታዎች አሁንም አገልግሎት

በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡ በአዲስ አበባ ታሪክ ዙሪያ ምሁራን የሚወያዩበት ሲምፖዚየምም ተካሂዷል፡፡ ታስበው

ያልተሳኩ ነገሮች ቢኖሩም የከተማዋ 100ኛ ዓመት ኢዮቤልዮ በደመቀና በተሳካ ሁኔታ ነበር የተከበረው፡፡
በ1981 ዓ.ም የከንቲባነት ዘመንዎ ሲያበቃ የት ገቡ?
ቀድሞ ወደነበርኩበት ማዕከላዊ ፕላን ተመልሼ፣ በኮሚሽነርነት የአንድ መምሪያ ኃላፊ ሆኜ መሥራት ቀጠልኩ፡፡ እዚያ

እያለሁ ነው የስርዓት ለውጥ የተካሄደው፡፡ ከደርግ ባለስልጣናት  አንዱ ስለነበርኩ ‘ትፈልጋላችሁ’ ተብለው ከታሰሩት

አንዱ ሆኜ በሰንደፋ ፖሊስ ማሰልጠኛ ለተወሰነ ጊዜ ታስሬያለሁ። በኋላ በነፃ ተሰናበትኩ፡፡ ከዚያ በኋላ በግልም በጋራም

የራሴን ሥራ ሞክሬያለሁ፡፡ በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ መሳተፍ ያስደስተኛል፡፡
አሁን የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ፎረም ሰብሳቢ ነዎት፡፡ እንዴት ወደዚህ ኃላፊነት መምጣት ቻሉ?
መንግሥት ወይም የአገር መሪ የሚኮነው በሦስት መንገድ ነው፡፡ አንዱ ከንጉሳዊያን ቤተሰብ መወለድ ነው፡፡ ሌላኛው

በምርጫ ተወዳድሮ መመረጥ ሲሆን ሦስተኛው አንዱ ሌላውን ታግሎ በማሸነፍ ነው፡፡ ኢሕአዴግም ከእነዚህ በአንዱ

መንግሥት ሆኗል፡፡ እኔ አንድ መሠረታዊ የሆነ የግል እምነት አለኝ፡፡ የአካባቢዬ የስልጣን አካል ሲጠራኝ መሄድ አለብኝ

ብዬ አምናለሁ፡፡ ቀበሌ ማለት መንግሥት ነው፡፡ ከቀበሌው ጋር ያልተገናኘ ከላይኛው አካል ጋር እንዴት ሊገናኝ

ይችላል? በዚህ እምነትና አቋሜ ምክንያት በተጠራሁባቸው መድረኮች እየተገኘሁ የተሰማኝን አስተያየት አቀርባለሁ፡፡ ይህ

ደግሞ የምጋበዝባቸውን መድረኮች ቁጥር አበራከተው፡፡
መሠረታዊ የሆነው የሕዝብ አደረጃጀት የሚፈጠረው በጉርብትና ነው፡፡ በጉርብትና ለመገናኘት ደግሞ መሠረታዊ የሆነ

የጋራ ነገር ያስፈልጋል፡፡ መሠረታዊው ነገር በቦታ፣ በጊዜና በአገልግሎት ይገለፃል፡፡ እያንዳንዳችን በየዕለቱ ሦስት

ተግባራትን በተደጋጋሚ እንፈጽማለን፡፡ 8 ሰዓት በሥራ፣ 8 ሰዓት በእንቅልፍና 8 ሰዓት ደግሞ በእረፍት ወይም

በመዝናናት እናሳልፋለን፡፡
በአንድ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ ሕዝቦች እርስ በእርስ ካልተገናኙ፣ ካልተወያዩና በጋራ ካልተዝናኑ ከተማ ነው አይባልም፡፡

የከተማ ሕዝብ አደረጃጀት ፍልስፍና መሠረቱም አብሮነትን የሚያጐላ ነው። ይህንን አመለካከትና ፍልስፍና

ስለማምንበት ባለፉት 12 ዓመታት ለሊዝ ፖሊስ የማሻሻያ ውይይት ሲደረግ፣ የአዲስ አበባ ተሐድሶ ኮንፈረንስ ሲጠራና

በመሳሰሉት መድረኮች እየተጋበዝኩ ተሳትፌያለሁ፡፡ በእነዚህ መድረኮች ተገኝቼ ሃሳቤን መግለጽ በመቻሌ ደስተኛ ነኝ፡፡
ይህንን ተሳትፎ የማደርገው በጡረታ ዕድሜዬ ነው፡፡ ልማት የጋራ ነው፡፡ ብንወድም ብንጠላም እየሰራን ነው

ልዩነታችንን ወደ አንድ ለማምጣት መጣር ያለብን፡፡ ሥራና ልማትን ትቶ መሟገትና መጨቃጨቁ የሚያስገኘው ጥቅም

የለም፡፡ በአሰራሮች ላይ ችግሮች እንዳሉ አያለሁ፡፡ ለምሳሌ ለልማት እንዲነሱ የሚደረጉ ሰዎች የሚከፈለው ካሳ

የገበያውን ዋጋ መሠረት ያደረገ አለመሆኑ ትክክል አይደለም፡፡
የከተማ መሬት በመንግሥት መያዙ ብዙ ጥቅም እንዳለው አምናለሁ፡፡ በደርግ ዘመንም መሬት የመንግስት ነበር፡፡

በከተሞች መሬት በነፃ እናድል ነበር፡፡ ኢሕአዴግ በሊዝ አለ፡፡ ይህ ደግሞ ገንዘብ በማስገኘት ብቻ ሳይሆን መንግሥት

ለከተማው ፕላን መሥራት እንዲችልም አድርጎታል፡፡ ነገር ግን ለሕዝብ አገልግሎት፡- ትምህርት ቤት፣ ገበያ፣ መዝናኛ፣

ጤና ጣቢያ ሊሰራባቸው የተከለሉ ቦታዎች ላይ ማስተር ፕላኑ ባስቀመጠው መሠረት ለምን እንዳልተሰሩ

የሚመለከታቸው አካላትን በሕግ መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ ለምን እንዳልተሰሩ ይህን መሰል ሀሳብና አስተያየቼን በየመድረኩ

እየተገኘሁ መግለፄ በሂደት የከተማ ነዋሪዎች ፎረም ሰብሳቢ ሆኜ እንድመረጥ ምክንያት ሆኗል፡፡
ተቃውሞ አልገጠመዎትም?
ከ1997 እስከ 1999 ዓ.ም መንግሥት ከአዲስ አበባ ሕዝብ ጋር ቅሬታ ላይ በነበረበት ጊዜ እንዴት አብረህ ትሰራለህ?

የሚሉኝ ነበሩ፡፡ አሁን ግን ይህንን መሰል ጥያቄ የሚያቀርብልኝ የለም፡፡ የሚጠይቀኝ ከመጣም ‘አገሬ አይደለም ወይ?

ለምንድነው በልማት ሥራ የማልሳተፈው?’ ብዬ መልሼ መጠየቄ አይቀርም፡፡ ይህንን ተሳትፎ በነፃና በፍላጐቴ ነው

የማከናውነው፡፡ የፖለቲካ ፍላጐት የለኝም፤ ኖርኝም አያውቅም፡፡
ቤተሰባዊ ሕይወትዎ ምን ይመስላል?
የማከብራት ባለቤትና ሦስት ሴት ልጆች አሉኝ፡፡ ቤተሰቤ የተባረከ ነው፡፡ እኔም ሰላምና እርጋታ ያለኝ ሰው ነኝ፡፡

በደስታና በሰላም ነው የምንኖረው፡፡  


Published in ህብረተሰብ

በአወዛጋቢው የ1997 ዓ.ም ምርጫ የታዛቢ ቡድን መሪ የነበሩት አና ጐሜዝን ጨምሮ “ለአፍሪካ ፣ ካሪቢያን፣ ፓስፊክና

የአውሮፓ ህብረት” የጋራ ስብሰባ ወደ አዲስ አበባ የመጡ የአውሮፓ ህብረት ፓርላማ አባላት ሰሞኑን ከተቃዋሚ ፓርቲ

መሪዎች ጋር  ተወያዩ፡፡
ፓርቲያቸውን ወክለው በውይይቱ እንደተካፈሉ የተናገሩት የኢዴፓ ማዕከላሚ ኮሚቴ አባል አቶ ልደቱ አያሌው፤

የአውሮፓ ህብረት ፓርላማ አባላት የኢትዮጵያ  የዲሞክራሲና የፖለቲካ ሁኔታ ላይ ምን አዲስ ነገር አለ? የወደፊቱ

አቅጣጫ ምን ይሆናል? በማለት ጥያቄ እንደሰነዘሩ ገልፀዋል፡፡ የፓለቲካ ምህዳሩ፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሊጠናከሩ

የሚችሉበት እድል ከጊዜ ወደ ጊዜ መጥበቡን ተናግሬያለሁ የሚሉት አቶ ልደቱ፣ የሀገሪቱ ዲሞክራሲያዊ ሂደት

እንደሚያሳስበንና የአውሮፓ ህብረት እርዳታ የፓለቲካ መጠቀሚያ እንዳይሆን ጥንቃቄ መውሰድ እንዳለባቸው

አስረድቻለሁ ብለዋል፡፡ የአውሮፓ ህብረት ለአገራችን እርዳታ መስጠቱን እንደማንቃወም፣ የእኛን ችግር እነሱ እንዲፈቱ

እንደማንጠብቅ ገልፀንላቸዋል ያሉት አቶ ልደቱ፤  ከዲሞክራሲያዊና ከሰብዓዊ መብት አያያዝ አኳያ ማድረግ

የሚገባችሁን ወደኋላ ትታችኋል፤ እርዳታ ሰጪ እንደመሆናችሁ ማድረግ ያለባችሁን ነገር ዘንግታችኋል የሚል አስተያየት

ሰጥቻለሁ ብለዋል፡፡
የአንድነት ፓርቲ ዋና ፀሃፊ አቶ አስራት ጣሴ በበኩላቸው፣ የፓለቲካ ምህዳሩ መጥበቡን፣ የሠላማዊ ትግል ተስፋ

መዳፈኑንና ህገ መንግስቱ እየተከበረ አለመሆኑን እንዳስረዱ ጠቅሰው፤ በነፃው ፕሬስ ህግ፣ ተሻሽሎ በወጣው የፓርቲ

ህግ፣ በፀረ ሽብርተኛ አዋጁ ዙሪያ እንደተወያዩበት ተናግረዋል። በ2002 ዓ.ም. ምርጫ በዝርፊያና በንጥቂያ ኢህአዴግ  

99.6 በመቶ ድምፅ አግኝቶ ማለፉን በመጥቀስ፤ 2007ዓ.ም. የሚደረገው አገር አቀፍ ምርጫ አጣብቂኝ እንደሆነብን

ለአውሮፓ ህብረት የፓርላማ አባላት አስረድቻለሁ ብለዋል - አቶ አስራት፡፡
ተቃዋሚ ፓርቲዎች ህዝቡን ሰብስበን ማነጋገር፣ ሠላማዊ ሰልፍ  ማድርግ እንዳልቻልንም፣ የመንግስትን ጫና በማሳየት

ገለፃ አድርጌያለሁ በማለት አቶ አስራት ተናግረዋል፡፡ የአውሮፓ ህብረት አባላት ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናትም

ጋር ቀደም ብለው ውይይት ማድረጋቸውን የተናገሩት አና ጎሜዝ፣ አገሪቱ በኢኮኖሚ ማደጓለ እንደሚገልፅና ልማቱ ግን  

ህዝቡን ከድህነት ያላወጣ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
በ2007 ዓ.ም. ለሚደረገው አገራዊ ምርጫም ተገቢውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ አና ጐሜዝ ገልፀው፤ ታዛቢዎችን ከመላክ

በተጨማሪ በየሁኔታው እና በየወቅቱ ድጋፋቸውን እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል፡፡
መኢአድ፣ ኢዴፓ፣ መድረክ፣ ሰማያዊ ፓርቲ በውይይቱ ላይ ተካፋይ እንደነበሩ ታውቋል፡፡

Published in ዜና

ከዕለታት አንድ ቀን ሶስት ትላልቅ ገበሬዎች በጣም አባያ ሆነው በየጫካው እየደነበሩ እፅዋቱን እየረመረሙ አገር-ምድሩን እያመሱ አስቸገሩ፡፡ የዱር አራዊቱ ሁሉ በግዙፍነታቸውና በጉልበተኝነታቸው ፈሯቸው፡፡ የደኑ አራዊት አንድ ቀን ተሰበሰቡና
“እነዚህን በሬዎች ምን ብናደርግ ነው በቀላሉ ልንበላቸው የምንችለው?” ይባባሉ ጀመር፡፡ ሆኖም ሁሉም ፈሩ፡፡ የበሬዎቹ ትላልቅ መሆን ከወኔያቸው በላይ ሆነ፡፡ ስለዚህም ምንም ሳያረጉዋቸው ቆዩ፡፡
አንድ ቀን አንድ ብልጥ ጅብ መጣና “ቆይ ግዴላችሁም፤ እኔ እነዚህን በሬዎች እነጣጥልላችኋለሁ” አለ፡፡ ከዚያም ወደ በሬዎቹ ሄደና እንዲህ አላቸው፡-
“እባካችሁ ተራ በተራ ላናግራችሁ እፈልግ ነበር፡፡ ትፈቅዱልኛላችሁ?”
በሬዎቹም፤
“እንደፈለክ ልታናግረን ትችላለህ” አሉት፡፡
አያ ጅቦም በመጀመሪያ ጥቁሩን በሬ ጠርቶ፤
“ከእናንተ መካከል የነጩ በሬ ነገር ያሳስበኛል”
“ለምን ያሳስብሃል?” አለና ጠየቀ ጥቁሩ በሬ፡፡
“ጠላቶች ከሩቁ በነጩ ቆዳው ምክንያት ይለዩታል፡፡ ስለዚህም በቀላሉ ስለሚለዩዋችሁ ያጠቋችኋል፡፡ የሚሻለው ገለል ብታደርጉት ነው-ተመካከሩበት” አለው፡፡
በሬዎቹ ተመካከሩና ነጩ በሬ ለብቻው ራቅ ብሎ እንዲኖር አደረጉ፡፡ የደኑ አውሬዎች፤ ብቻውን ያገኙትን በሬ አድነው፣ አሳድደው በሉት፡፡ አያ ጅቦ ቀጠለና ጥቁሩን በሬ እንደገና ጠራው፡፡
“የዚህ የጓደኛህ የቀዩ በሬ ነገር በጣም አሳሳቢ ሆኖብኛል” አለው፡፡
“ለምን አሳሳቢ ሆነብህ?” አለው፡፡
“ምክንያቱም፤ ደም የመሰለ ቀይ በመሆኑ፤ ሰዎች ከሩቅ ይለዩታል፡፡ ስለሆነም ባንድ አፍታ የት እንዳላችሁ ይለዩና ይከታተሉዋችኋል! ራቅ አርገህ ብትልከው አንተ እንደዛፍ ወይም እንደዛፍ ጥላ የጠቆርክ በመሆንህ አይለዩህም” አለው፡፡
ጥቁሩ በሬም ሄዶ ለቀዩ በሬ ስለተባለው አደጋ አዋየው፡፡ ቀዩ በሬ ተስማማና ራቅ ወዳለ ቦታ ሄደ፡፡
ቀዩ በሬ ብቻውን ሲሆንላቸው የዱር አውሬዎቹ አሳደው ሰፈሩበት፡፡
በመጨረሻም ወንድም የሌለው ጥቁሩ በሬ በግላጭ ተገኘና የዱር አውሬዎች ሁሉ ተቀራመቱት፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አያ ጅቦ “የአፍ-አጣፋጭ” የሚል ስም ወጣለት፡፡  
*   *   *
የባለተራ ደወል የሚለውን አለማሰብ የዋህነት ነው፡፡ አዳዲስ አካሄዳችንን አለማስተዋልም ጅልነት ነው! “እኔ እዚህ መሆኔ በቂ ነው” ከማለት ባሻገር፤ “እገሌ የት ደረሰ?” ማለት ያባት ነው፡፡ የኃይል ሚዛንን አውቆ ማን ምን እያደረገ ነው? ምን ዘዴ እየተጠቀመ ነው? ማለት ደግ ነው፡፡ “የከፋፍለህ ግዛውን መርህ የምንንቀውና የምንሳለቅበትን ያህል፤ ዕውነት ቢሆንስ? ማለት ከማኪያቬሊ ጀምሮ የኖረ ያለ፤ “ደባ” መሆኑን ማስተዋል ታላቅነት ነው፡፡
የሀገር፣ የህዝብ እና የተቋም ሚሥጥር ግራ ሊያጋባን አይገባም፡፡ የሚሥጥር ትርጉም ብዙዎችን ቢያወዛግብም፤ የግል - ሚሥጥርና የአገር ሚሥጥር ግን መለየት ይኖርበታል፡፡
ስልክ ወይም ኢሜይል ጠለፋ አዲስ ኃይላዊ ማረጋገጫ (Coerced confession) ነው ይባላል፡፡ አዲስ ሚሥጥር መያዣ ዘዴ ነው፡፡ ዱሮ፤ በጉልበት በማገት የምናደርገውን፤ ዛሬ በሽቦና በኤሌክትሪክ ኃይል ጠለፋ ላይ መፈፀም ማለት ነው፡፡ ይሄ እንግዲህ “ተመርማሪውን ከማስገደድ፣ ቢያስፈልግም በቶርቸት (በወፌ-ላላ)፤ ከማወጣጣት ዶክመንቶቹን ከመውረስ፣ የግል መረጃዎችን ከመውሰድ፣ ቤቱን ሰብሮ ከመግባት ይልቅ፤ ሌላ ዘዴ መተካት ማለት ነው፡፡ ይሄ በዘመናዊ መንገድ ሲታሰብ፣ የኢ-ሜይል መዛግብት መውረስ ማለት ነው፡፡
ይሄ ደሞ፤ የኤሌክትሮኒክ መገናኛ ዘዴዎችን የፈጠሩት ሰዎች ራሳቸው፤ የማያውቁት ዘዴ የለም ብለን እንመን እንደማለት ነው፡፡
“ፖስታህ ከተከፈተ አለቀልህ፡፡ ገበናህ ተቀደደ፡፡ ፈረሱ ከጋጣው ወጥቷል”
 “ዱሮ ሚሥጥር የቤተ ክህነት ነበር፡፡ ዛሬ ቴክኖሎጂ ወርሶታል፡፡ ነገር ከካህን ወደ ልዑል ካለፈ - ነገር ጠፋ” ይላል - ዘ ኒውዮርከር፡፡ ገዢ የማያቀው ሚሥጥር የለም ነው ቁም ነገሩ፡፡
ከግልጽነት ይልቅ ሚሥጥራዊነትን የሚፈልግ ወገን - ባሁኑ ዘመን ቀልጧል፤ የሚል እሳቤ ቢኖረን ይሻላል፡፡ “ሚሥጥር ከኮተኮታችሁ ሁሉ ነገር ተጀመረ፡፡ ጐበዝ! ሚሥጥራዊነት የሤራ መሣሪያ ናት (ጄሬሚ ቤንታም)” በድብቅነትና በሚሥጥራዊነት መኖር አይቻልም፡፡ ከህዝብ የምትደብቀው ሚሥጥር በተለይ፤ ውሎ አድሮ መሸማቀቂያህ ነው!
ድብቅነት ነገ ከነግ - ወዲያ ይገለጣል፡፡ ሚሥጥራዊነት ግን የጥብቅነቱን ያህል ይቆይ እንጂ የሚታወቅ አደጋ ይሆናል፡፡ ሚሥጥራዊነት ብዙ ሽፋን አለው:- የሉዓላዊነት ሽፋን፣ የመንግሥት ደህንነት ሽፋን፣ የተቋም ህልውና ሽፋን፣ ያለመከሰስ መብት ሽፋን…ምኑ ቅጡ! ዜጋ የግል - ሚሥጥሬ ነው ቢል ግን፤ በብዳቤ፣ በኢ-ሜይል፣ በሞባይል፣ በአካል ሊያስጠይቅህ ይችላል የሚባለው ሚሥጥር የመብቱን መገፈፍ አያመላክትም፡፡
“መንግሥት ዜጐቹን ላለመሰለል መጠንቀቅ ይገባዋል” ይላሉ ፀሐፍት፡፡ “እኛ ብቻ ነን መሪዎች” የሚሉ ህዝቡን እንዲህ ይላሉ:- “ለማመዛዘንና ለመፍረድ አትችሉም፡፡ ደንቆሮ ናችሁና፡፡ ያም ሆኖ፤ ደንቆሮ ሆናችሁ መቀጠል ይኖርባችኋል - ምነው ቢሉ ማመዛዘንና መፍረድ እንዳትችሉ ይፈለጋልና፡፡” ይላል /ቤንታም/፡፡
ፖስታ እየገለጡ ሚሥጥር ስለሚያዩ ፖስታ ቤቶች፣ ዲዝሬኤሊ እንዲህ ይላል፤ “ደብዳቤዬን ክፈቱ ግን መልስ መስጠት ቻሉ!”
ዋናው ጥያቄ ግን በግል - ሚሥጥር (Privacy)፣ በግልጽነት  (Publicity) መካከል ልዩነት እንዳለ ልብ - ማለት ያሻል የሚለው ነው፡፡
ሆኖም እንደ ኤድጋር አላን ፖ - አመለካከት፤ “ሁሉም ድብቅ ነገር (mystery) ነገ ተገላጭ ነው፡፡ ምንም ነገር ተሸሽጐ አይቀርም፡፡ ወንጀሎች መፈታት አለባቸው፡፡ ግርግዳዎች መፍረስ አለባቸው፡፡ መቃብሮች ይፈነቀላሉ፡፡ ፖስታዎችም ተቀደው ይታያሉ” ይላል፡፡
ሙሰኛን፣ ኢፍትሐዊን፣ ሃሳዊ - መሲህን፣ ደካማ - ፖለቲከኛን፣ አድርባይን፣ አሻጥረኛን፣ አስመሳይ ተራማጅን የሚያውቅና የሚከስ፤ በዚህም ሆነ በዚያ ዕውቀቱ ያለው ነው፡፡ “ሰርቆ የሚያውቅ፣ በምልክት ያሰራል” የሚለው የወላይትኛው ተረት ይሄው ነው፡፡   

Published in ርዕሰ አንቀፅ

መንግስት ከሣውዲ የሚመለሱ ዜጐች ቁጥር አስቀድሞ ከተገመተው በላይ መሆኑን ገልጿል። ቀድሞ የተመላሾቹ ቁጥር  

28 ሺህ እንደሚሆን ቢገመትም አሁን ወደ 80ሺህ እንደሚደርስ ተነግሯል፡፡ በስደተኞቹ ላይ እየደረሰ ያለውን እንግልት

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም፤ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ከማውገዝ አልተቆጠቡም፡፡ ጉዳዩ በሰከነና

የዲፕሎማሲ መርሁ በሚፈቅደው መንገድ መያዙንም ገልፀዋል፡፡ መንግስት ከዚህ በላይ በዲፕሎማሲው ርቆ ሊሄድባቸው

የሚችልበት አማራጮች  እንደሌሉ የሠሞኑ መግለጫዎቹ ያመለክታሉ፡፡ ይሁን እንጂ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ

ሣይንስ ምሁሩ ዶ/ር መረራ ጉዲና፣ መንግስት የዜጐቹን መብት በማስከበርም ሆነ የሃገርን ክብር በማስጠበቅ ረገድ ምንም

አልተራመደም ይላሉ - ተመላሾቹን ከመቀበል የዘለለ ዲፕሎማሲያዊ እርምጃዎች መውሰድ አለመቻሉን በመግለፅ፡፡ ዶ/ር

መረራ ጉዲና በጉዳዩ ዙሪያ የሰጡንን አጭር ማብራሪያ እነሆ:-


በሣውዲ አረቢያ በዜጐቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ተከትሎ መንግስት ጉዳዩን የያዘበትን መንገድ እንዴት

ገመገሙት?
ሁለት ሶስት ነገሮች አሉ፡፡ አንደኛው አሜሪካ፣ ጀርመን፣ ስዊድን በመሳሰሉት ሃገሮች ያሉ ኢትዮጵያውያን በሣውዲ

አረቢያ ላይ ተቃውሞ ሲያሰሙ እየፈቀዱላቸው፣ እዚህ መከልከሉ በዜጐች ላይ ተጨማሪ ወንጀል መስራት ነው፡፡

ሁለተኛው በተለያየ መንገድ እየሰማን እንዳለው አሁንም ቢሆን በ40ሺህ የሚቆጠሩ ዜጐች እየተንገላቱ ነው፡፡ እሪታና

የይድረሱልን ጥሪ እያሰሙ ነው። የኢትዮጵያ መንግስት ደግሞ የሚያወራው ሌላ ነው፡፡ መደብኩ እንኳን ያለው 50

ሚሊየን ብር አንድ እነሱ “የመንግስት ሌባ” የሚሉት የሚሠርቀው እኮ ነው። 50 ሚሊየን ብር ለ70ሺህ ሰው ነው

የመደቡት። ነገር ግን በሙስና የተከሰሱት ሰዎቻቸው እኮ የዚያን ሶስት እጥፍ ሰርቀዋል ተብሏል፡፡ በእውነቱ የተመደበው

ገንዘብ በጣም ትንሽ ነው፡፡ ሌላው ደጋግመው የሚያሰሙት፤ የሣውዲ አረቢያ መንግስትን ድርጊት የሚኮንን ሳይሆን

ወዳጅነት እንዳይበላሽ ትልቅ ስጋት ያላቸው የሚያስመስላቸው ነው፡፡ ከዜጐች ድብደባ፣ ግድያና እንግልት ይልቅ

የሣውዲ መንግስት ፍቅር የያዛቸው ነው የሚመስለው፡፡ ስለዚህ በሚፈለገው መንገድ ለጉዳዩ ምላሽ እየሰጡ አይደለም

የሚል መደምደሚያ ላይ መድረስ ይቻላል፡፡ ድሮውንም ቢሆን እነዚህ ዜጐች የተሰደዱት የኢትዮጵያ መንግስት የስራ

እድል መፍጠር ባለመቻሉ ነው፡፡ ሃገሪቷን የስደት ሃገር ያደረገው ራሱ መንግስት ነው፡፡
በሃላፊነትም ያስጠይቀዋል፡፡ ስለዚህ መንግስት በቀን ይሄን ያህል ሰው መለስኩ ከሚል፣ በመሠረታዊነት ዜጐች

የማይሰደዱባት ሃገር መፍጠር አለበት፡፡ የስራ እድል ሊኖርና የሰብአዊ መብት ሊከበር ይገባል፡፡
መንግስት በዜጐቹ ላይ ለተፈፀመው ግፍ፣ በአለማቀፍ ፖለቲካዊ ዲፕሎማሲው ምን ድረስ ነው ሊሟገት የሚችለው?
መንግስት እኮ ደጋግሞ የሚነግረን በህገወጥ መንገድ ከሃገር የወጡ ናቸው እያለ ነው፡፡ እንኳን በዚህ ዘመን ቀርቶ በጥንት

ዘመንም ስደተኞች ክብር አላቸው፡፡ ዝም ብሎ ይገደሉ፣ ይፈለጡ፣ ይቆረጡ አይባልም፡፡ ስለዚህ ሣውዲ አረቢያ ኋላቀር

በሆነ መንገድ ዜጐቻችንን ስታንገላታ በህግ መክሰስም ይቻላል፡፡ ሌላ አማራጭ ከተፈለገም እንደወዳጅ መንግስትና

የንግድ ሸሪክ ብዙ ተጽእኖ ማድረግ ይቻላል፡፡ ይልቁንስ የኢትዮጵያ መንግስት እያየ ያለው፣ እዚህ ያሉ ተቃዋሚዎች ምን

አሉ የሚለውን ብቻ ነው፡፡ ተቃዋሚዎች ከሰሱን፣ አጣጣሉን የሚለው ላይ ነው ያተኮረው፡፡
ከዚያም ሲያልፍ ሌት ተቀን እንደ መጽሐፍ ቅዱስ የሚነግረን ዜጐቹ በህገወጥ መንገድ መሄዳቸውን ነው፡፡ ዋናው ጉዳይ

መጀመሪያ የዜጐችን ነፍስ ማዳን ነው፤ ሌላው ደግሞ ለስደት የዳረገንን የኢኮኖሚ ችግር በመፍታት፣ ኢትዮጵያን ከስደት

ሀገርነት ዝርዝር ለማውጣት መንቀሳቀስ አለበት፡፡ ግን አሁን ባለው ሁኔታ የዚህ አዝማሚያ እምብዛም እየታየ አይደለም፡፡
መንግስት በሣውዲ አረቢያ ላይ ይከተል የነበረውን የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ለመፈተሽና ለመቀየር የእነዚህ ዜጐች እንግልት

ምክንያት ሊሆን ይችላል ብለው ያስባሉ?
አሁን እኮ መንግስት ጠንከር ያለ መግለጫ እንኳ አላወጣም፡፡ በመኮነን ደረጃ እንኳ ደፍሮ መግለጫ ማውጣት

አልቻለም፡፡ ሌሎች ሀገሮች እኮ ቢያንስ በዜጐቻቸው ላይ በደል ሲፈፀም በመንግስት ደረጃ የመረረ ጩኸት ያሰማሉ፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ግን ከህዝቡ ጋር አብሮ ሊጮህ ቀርቶ፣ የህዝቡንም ድምጽ እያፈነ ነው፡፡ ለዚህ ነው በተለይ

በፖለቲካ ዲፕሎማሲው በኩል እየተወሰደ ያለው እርምጃ በቂ አይደለም የምለው፡፡
መንግስት ዜጐቹን ከሃገሪቱ ከማስወጣት ባለፈ እርምጃ ያልወሰደው የኢኮኖሚ ጥገኝነት ጉዳይ ስላለ ነው፤ የኢትዮጵያ

ዋነኛዋ የውጪ ንግድ ሸሪክ ሣውዲ በመሆኗ ነው የሚሉ አስተያየቶችንስ እንዴት ያዩዋቸዋል?
በእርግጥ የኢኮኖሚ ጥገኝነቱ አለ፡፡ እናውቃለን። ታላላቅ የሣውዲ አረቢያ ከበርቴዎች በዚህች አገር ኢንቨስት ያደርጋሉ፡፡

ነገር ግን ለኢኮኖሚ ሲባል የዜጐችን መብትና ብሔራዊ ጥቅምን አሣልፎ መስጠት በየትኛውም የፖለቲካ አማራጭ ፈጽሞ

አይመከርም፡፡ ከምንም በላይ የዜጐች መብትና የሃገር ክብር ይቀድማል፡፡ በመቶ ሺህ የሚቆጠር ሰው እየተንገላታ

ለኢኮኖሚ ጥገኝነቱ ሲባል ዝምታን መምረጥ እንዲሁም የዜጐችን ጩኸት ወደማፈኑ መሄድ ተገቢ አይደለም፡፡
አንድ መንግስት በሌላ ሀገር የሚኖሩ ዜጐቹን መብት ለማስከበር ከአለማቀፍ ህግና ፖለቲካ ተመክሮ አንፃር ምን ያህል

ርቀት ነው ሊጓዝ የሚችለው?
ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ጨርሶ እስከማቋረጥ ይደርሳል፡፡ ከዲፕሎማሲ ግንኙነት ማቋረጥ ባለፈም ችግሩን ለአለማቀፉ

ህብረተሰብ በጩኸት ማሰማትም ይገባል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ግን አፉን ሞልቶ ‘በዜጐቻችን ላይ እየተሰራ ያለውን

ግፍ እንኮንናለን’ ለማለት እንኳ እየጨነቀው ነው፡፡ እዚህ ያለውን ኤምባሲ እንኳ ሲያነጋግሩ፣ ዋናውን አምባሳደር

አይደለም፡፡ በሰለጠኑትን ሃገሮች ደረጃ ቢሆን በ30ሺህ፣ 60ሺህ የሚቆጠሩ ዜጐች እንዲህ ያለ እንግልት ሲደርስባቸው

ቀላል ጉዳይ አድርገው አይመለከቱትም፡፡ የህንድ፣ የፊሊፒንስ እና የሌሎች ሃገሮች ዜጐች ከኢትዮጵያውያኑ በተለየ

ክብራቸው ተጠብቆ ነው ከሃገር የወጡት፡፡ ይሄ ለምን ሆነ ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡
የስደተኞቹ ስቃይ ለፖለቲካ መጠቀሚያነት እንዳይውል መንግስት ጠይቋል፡፡ በእርግጥ ለፖለቲካ መጠቀሚያነት ውሏል?
የኢትዮጵያ ዜጐች በያሉበት ብሶት እያሰሙ ነው። በተለያዩ መንገዶች በየሃገራቱ በኢትዮጵያውያኑ ላይ የሚፈፀሙት

በደሎች ሲሰሙ ይዘገንናሉ፡፡ እኛ እኮ እየጠየቅን ያለነው የእነዚህ ኢትዮጵያውያንን መብት ነው፡፡ ነገር ግን መንግስት

ጉዳዩን በሌላ እየተረጐመው እኮ ነው የተቸገረው፡፡ 

ጀግኖችን ብናከብር፣ ለስደት ባልተዳረግን!
መንግስትንና እርዳታን ማምለካችን ይቁም

በሳዑዲ አረቢያ የተሰቃዩ ስደተኞች፣ እንደ እንስሳ እየታደኑና እየታጐሩ ሲባረሩ፣ ብዙዎቻችን በንዴት እርር ብለናል፣

በቁጭት ተንጨርጭረናል፡፡ ነገር ግን የንዴታችንና የቁጭታችን ያህል፤ በሰከነ አእምሮ የሚያዛልቅ ነገር ለማሰብ

የምንፈልግ አይመስልም፡፡ እንደ አያያዛችን ከሆነማ፤ የዛሬው አሳዛኝ ትዕይንት፣ (አዲስ ካለመሆኑም በተጨማሪ) ነገ ከነገ

ወዲያም መደገሙ አይቀርም፡፡
ካሁን በፊትምኮ በሶማሊያና በየመን በኩል ወደ ሳዑዲ አረቢያ የተሰደዱ  ብዙ ሺ ወጣቶች በተደጋጋሚ ከሪያድ እና

ከጂዳ እየታፈሱ ተባረዋል። ይሄውና ዛሬም እየተባረሩ ነው፡፡ እንዲህም ሆኖ፣ ሳዑዲ ለመግባት በየመን በኩል የሚደረገው

የስደት ጉዞ አልተቋረጠም፡፡ ምን አለፋችሁ! አንዳችም አዲስ ነገር አልተፈጠረም፡፡ አንዲት መላ ካልተዘየደ፣ አዙሪቱ

አይቆምም፡፡ ሰሞኑን ያየነው የሰዶ ማሳደድ ግርግር ሲረግብ፣ ቁጭታችንና ንዴታችን ሲበርድ፤ ወደ ድሮው እንመለሳለን፡፡
በእርግጥ፣ በደላሎችና በኤጀንሲዎች ላይ የጀመርነውን ከንቱ የውግዘት ዘመቻ ለማቆም ፍቃደኞች አንሆንም፡፡ የኩነኔ

መዓት እናወርድባቸዋለን፡፡ በስደት ላይ የሚደርሱ መከራዎችንና ስቃዮችን እየዘረዘርን እለት በእለት መለፈፋችንንም

እንቀጥልበታለን፡፡ የመንቀሳቀስ መብትን የሚጥሱ የጉዞ እገዳዎችንም በሰበብ አስባቡ ማራዘም እንችላለን፡፡ “እኔ

አውቅልሃለሁ” በሚል ስሜት አዛዥ ናዛዥ የመሆን አባዜያችንን በቀላሉ አንለቀውም፡፡ አዛኝ ተቆርቋሪ መምሰልም

እንችልበታለን፡፡
ከስደት ተባርረው ለሚመለሱ ወገኖች፣ የትራንስፖርት ወጪ መሸፈንና ህክምና መስጠት፣ የእለት ረሃብ ማስታገሻ ምግብ

ማቅረብና የእርዳታ ማሰባሰቢያ የባንክ ሂሳብ መክፈት የመሳሰሉ ልግስናዎችንም በሆይ ሆይታ ለተወሰነ ጊዜ ማቆየት

አያቅተንም፡፡ ግን ምን ዋጋ አለው?
ይሄ ሁሉ ቅንጣት መፍትሔ አይሆንም፡፡ ለምን በሉ፡፡ እስካሁን መች መፍትሔ ሲያመጣ አየን? አላመጣም፡፡

“ብንተባበርና ብንረዳዳ ይሄ ሁሉ ስቃይ አይፈጠርም ነበር” የሚሉ ሰዎች መኖራቸውን አጥቼው አይደለም፡፡ “በአገር

ውስጥ ሰርቶ መኖር ይቻላል” የሚለውን መፈክር ሳልሰማ የቀረሁም አይምሰላችሁ፡፡ ነገር ግን ሰሞኑን የተሰራጨ ሌላ

ዜናም ሰምቻለሁ፡፡ እናቱን የገደለ አንድ የገጠር ወጣት በፍርድ ቤት የእስር ቅጣት እንደተወሰነበት የሚገልጽ ዜና ነው፡፡

ወጣቱ እናቱን የገደላቸው የእርሻ መሬት አላወረሰችንም በሚል ምክንያት እንደሆነ በዜናው ተጠቅሷል፡፡ ደግነቱ

አብዛኛው ወጣት የዚህን ያህል ክፉ ጭካኔ የተጠናወተው አይደለም፡፡ ታዲያ፣ ጭቃኔ ያልተጠናወተው፣ ሳይቸገር ቀርቶ

አይደለም፡፡
አብዛኛው የገጠር ቤተሰብ የሚተዳደርበት የእርሻ ቦታ፣ ከግማሽ ሄክታር ያነሰ ነው፡፡ የየቤተሰቡ የእርሻ ማሳ የእግር ኳስ

ሜዳ እንኳ አታክልም ማለት ነው፡፡  ይህችው ማሳ ለአምስት ልጆች ስትከፋፈል ይታያችሁ፡፡ ከእርሻ በስተቀር ሌላ

ምንም የመተዳደሪያ ስራ የሌላቸው ወደ ሚሊዮን የሚጠጉ መሬት አልባ ወጣቶች በየአመቱ እንደሚፈጠሩ አስቡት፡፡
ብዙዎቹ የገጠር ወጣቶች መሄጃ መድረሻ የላቸውም፡፡ መሬትን ጠፍጥፈው መስራት አይችሉም፡፡ ከተማ ሄደው

እንዳይሰሩ፤ የሚያወላዳ የስራ እድል አያገኙም፡፡ በየከተማው በስራ አጥነት የሚሰቃይ ወጣት ሞልቷል  - ለዚያውም

የተማረ ወጣት፡፡ ለነገሩ ተሻምተው ስራ ቢያገኙ እንኳ፣ በዛሬ ደሞዝ እህል በልቶ ማደር አይታሰብም፡፡ የዛሬ ብር ምን

እርባና አለውና! ባለፉት 6 አመታት በመንግስት ቅጥ የለሽ የገንዘብ ህትመት ሳቢያ  የዋጋ ንረት ሲግለበለብ፣ የአገራችን

ብር ክብር አጥቶ  ረክሷል። ከ6 አመት በፊት አራት ኩንታል ጤፍ ለመግዛት የሚያስችል ሁለት ሺ ብር፣ ዛሬ የአንድ

ኩንታል ዋጋ ሆኗል፡፡
ታዲያ መሬት ያጣ የገጠር ወጣትና፣ በልቶ ለማደር የሚበቃ ደሞዝ የሩቅ ህልም የሆነበት የከተማ ተመራቂ ምን

ይዋጠው?
በየወሩ 15ሺ ያህል ወጣቶች በሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እየተመዘገቡ፣ 10ሺ ያህል ደግሞ በየአቅጣጫው

ድንበር እየጣሱ ሲሰደዱ የቆዩት፣ ወደው አይደለም፡፡ መሄጃ መድረሻ ጠፍቷቸው፣ አማራጭ መላ አጥተው ነው ብዙዎቹ

ወጣቶች የሚሰደዱት፡፡ እንደ ድሮው ልምድ፣ ድህነትን ታቅፈው በተስፋ ቢስነት ተኮራምተው መቀመጥን ትተዋል፡፡
ታዲያ፣ ደላሎችንና ኤጀንሲዎችን ስናወግዝ ብንከርም፣ ለእነዚህ ችግረኛ ወጣቶች መፍትሔ ይሆናቸዋል? “ስደት

በአመለካከት መጓደል ሳቢያ የሚከሰት ነው” እያልን ስለ አገር ልማት ስንደሰኩል ብንውል፤ የኛ መፈክር ለገጠሩ ወጣት

የእርሻ ማሳ አይሆንለትም፡፡ ወይም ለከተማው ወጣት መተዳደሪያ ደሞዝ አያስገኝለትም፡፡ “እንተባበር፣ እንረዳዳ” ብለን

የዛሬን ምሳ ብናበላቸው፣ ለጊዜው መልካም የልግስና ተግባር ቢሆንም፤ የኛ አዘኔታና ልግስና የነገን ረሃብ

አያስታግስላቸውም፤ ለከርሞ የኑሮ ጣጣቸውን አይሸፍንላቸውም፡፡
“መንግስትስ?” ብላችሁ ትጠይቁ ይሆናል። በእርግጥም፣ የመንግስት አፍ አያርፍም፡፡ “የኑሮ ማቋቋሚያ እሰጣለሁ”፤

“የስራ ዕድል እፈጥራለሁ” እያለ ያላወራበት ጊዜ የለም፡፡
ተስፋችንን በመንግስት ላይ ጥለን ስንት አመታት ተቆጠሩ? እውነትም፣ መንግስት “ለስራ ፈጠራ” እና “ለማቋቋሚያ” ብዙ

ገንዘብ ማፍሰሱ አልቀረም። ለዚህም በተለይ በከተሞች አካባቢ ግማሽ ያህሉን የዜጐች ገቢ በመንግስት ይወሰዳል፡፡ ነገር

ግን፣ ጠብ ያለ ነገር የለም፡፡ “አነስተኛና ጥቃቅን አምራቾችን አበራክታለሁ” እያለ ለበርካታ አመታት “ስትራቴጂና

ፓኬጅ” ከመደርደር ባያርፍም፣ ከድሮው የተለየ ስንዝር ያህል የመሻሻል ምልክት አለመታየቱ መንግስት ራሱ አምኗል፡፡

ደግሞስ መንግስት ራሱ የፈጠረውን የዋጋ ንረት በቢዝነስ ሰዎች ላይ እያላከከ፣ በአጭበርባሪትና በስግብግብት

ሲወነጅላቸው እየታየ፣ ለስራ ፈጠራ የሚነሳሱ ወጣቶች እንዲበራከቱ መጠበቁ አይገርምም?
ምን ለማለት ፈልጌ ነው? የመሬት አልባና የስራ አጥ ወጣቶችን ዋነኛ ችግር ምን እንደሆነ እንገንዘብ። ያኔ፤ ደላሎችንና

ኤጀንሲዎችን በመኮነን፣ ወይም የስደት አስከፊነትን በመስከበክ መፍትሔ እንደማናገኝ እንረዳለን እያልኩ ነው፡፡ እንደ

ወትሮው መንግስትን እያመለክን ተስፋችንን ብንጥልበት፤ ወይም እንደለመድነው ከሁሉም በላይ የእለት ምጽዋትንና

እርዳታን ብናሞግስ ቅንጣት ታክል ለውጥ አናመጣም፡፡ ከጥንት እስከዛሬ ሽራፊ ለውጥ ያላመጡልንን ነገሮች የሙጢኝ

ይዘን የምንቀጥል ከሆነም፤ የእስከዛሬው የኑሮ ችግር፣ ስደትና ስቃይ ወደፊትም መደገማቸው አይቀርም፡፡
እንዲህ ስባል ግን፣ ለውጥ ማምጣትና መሻሻል አይቻልም ማለቴ አይደለም፡፡ እስከዛሬ የዘነጋነውን፣ የሳትነውንና ችላ

ያልነውን ነገር አናጢን፡፡ ሌሎች አገሮች ከችጋር ተላቅቀለው የበለፀጉበትንም መንገድ እንመልከት፡፡ ከአሜሪካ እስከ

ጃፓን፣ ከእንግሊዝ እስከ ደቡብ ኮሪያ… ገና ወደ ብልጽግና እየተራመደች የምትገኘው ቻይና ሳትቀር፣ የስኬታቸው ዋና

ምንጭ ተመሳሳይ ነው - የስራ ፈጠራ ቢዝነስ!
የአገራችን ሰው ደግሞ በተቃራኒው ቢዝነስን ከቁም ነገር አይቆጥረውም፤ እንዲያውም በጠላትነት እስከማየት ይደርሳል፡፡

መንግስትንና ራሽንን፣ እርዳታንና ምጽዋትን ነው የሚያመልከው፡፡
ኢትዮጵያን ጨምሮ፣ በርካታ የአፍሪካ አገራት፣ ምስራቅ ጀርመንና ሰሜን ኮሪያ፣ እነ ራሺያና ቬትናም፣…በአጠቃላይ

ተስፋቸውን በመንግስት ላይ የጣሉ የቀድሞ ሶሻሊስት አገራት ሁሉ፣ በኢኮኖሚ የቱን ያህል ተንኮታኩተው እንደነበር

አታስታውሱም? ከሃያ አመታት ወዲህ በተሰወነ ደረጃ የስራ ፈጠራ ቢዝነስ ሲፈቀድ ነው ብዙዎቹ ያንሰራሩት፡፡

በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች በረሃብ ያለቁባት ቻይና እንኳ፣ ለግል ኢንቨስትመንትና ለቢዝነስ በሯን ስትከፍት ነው ወደ

ብልጽግና ግስጋሴ የተሸጋገረችው፡፡
ጉዳዩ ያን ያህልም ውስብስብ አይደለም። የመንግስት እጅ ውስጥ የገባ ገንዘብ ለተለያዩ ፕሮጀክቶች ሲመደብ፣ በሙስና፣

በዝርክርክነትና በተንዛዛ ቢሮክራሲ ይባክናል፡፡ እንዲያ በከንቱ ሃብታቸውን የሚያባክኑ የቢዝነስ ሰዎች ብዙ አይደሉም፡፡
ለነገሩ እዚሁ አገራችን ውስጥ በአንድ በኩል፣ እንደ ጣና በለስ በግል ኩባንያዎች አማካኝነት የተገነቡ የኤሌክትሪክ

ማመንጫ ግድቦችን፣ በሌላ በኩል ደግሞ እንደ ተንዳሆ፣ ከሰም እና ርብ የመሳሰሉ በመንግስት ድርጅቶች አማካኝነት

የተጀመሩና ለበርካታ አመታት የተጓተቱ የግድብ ግንባታዎችን ማነፃፀር ይቻላል፡፡ በመንግስት ድርጅቶች የተያዙ

ግድቦች፣ ግንባታቸው እየተጓተተ የመጠናቀቂያ ጊዜያቸው ከ6 አመት በላይ ተራዝሟል፡፡ እውነታውን የዚህን ያህል

ያፈጠጠ ቢሆንም፣ እንደወትሮው ተስፋችንን ሁሉ በስራ ፈጠራ ቢዝነስ ላይ ሳይሆን በመንግስት ፕሮጀክቶች ላይ

መጣላችንን አላቆምንም፡፡
ይህ ብቻ አይደለም ችግሩ፡፡ ከግል ኢንቨስትመንትና ከትርፋማ ቢዝነስ ይልቅ፣ ለምጽዋት ተግባራትና ለእርዳታ ጥሪዎች

የላቀ ክብር እንሰጣለን፡፡ በእርግጥ፣ አመልማል አባተ እንዳደረገችው፣ 5ሺ ለሚሆኑ የስደት ተመላሾች ምሳ ማቅረብ

ትልቅ የልግስና ተግባር ነው፡፡ ሊመሰገንም ይገባዋል፡፡ ለ5ሺ ወጣቶች የስራ እድል የሚፈጥር ቢዝነስ ግን፣ ሺ ጊዜ እጥፍ

ድርብ ምስጋናና አድናቆት ይገባዋል፡፡ የአንድ ቀን የምሳ ግብዣ ማግኘት የእለቱን ረሃብ ያስታግሳል፡፡ የስራ እድል

ማግኘት ግን፣ ለዘለቄታው ከተመጽዋችነት ያላቅቃል፡፡ ብዙ ሺ ሰዎች ራሳቸውን ችለው ሰው የመሆን ክብር የሚቀዳጁት፣

የቢዝነስ ሰዎች በሚፈጥሩት የስራ እድል ነው፡፡ የዛሬ ረሃባቸውን ማስታገስ ብቻ ሳይሆን፣ ብዙ ሺ ሰዎች የብዙ ሺ ቀናት

ኑሯቸውን የሚያደላድሉበት ትልቅ ፀጋ ነው - የስራ ፈጠራ ቢዝነስ፡፡
እናም ተስፋችንን በመንግስት ላይ መጣላችንን ትተን፣ ለምፅዋትና ለእርዳታ የላቀ ክብር መስጠታችንን አርመን፤ ለስራ

ፈጠራ ቢዝነስ ቅድሚያ በመስጠት፣ የቅዱስነቱ ያህል ታላቅ ክብር እንደሚገባው ስንገነዘብ ነው እንደሌሎች አገራት

መበልፀግ የምንችለው፤ ያኔም ነው ከስደት ስቃይ የምንገላገለው፡፡   

  • የአገሩን ከፍተኛ ሙቀት መቋቋም አቅቷቸው ይሰቃያሉ
  • የመንገድ አጠቃቀም ባለማወቅ ለመኪና አደጋ ይዳረጋሉ
  • ድብደባና የሰሩበትን ደሞዝ መከልከል የተለመደ ነው  


በቤት ሰራተኝነት ተቀጥረው ወደ ኩዌት የሚሄዱ ኢትዮጵያውያን ሴቶች  በሁለቱ መንግስታት መካከል የስራ ስምምነት

በመኖሩ የሚገጥማቸው ፈተና ከሌሎች የአረብ አገራት በንፅፅር የተሻለ ነው ሊባል ይችላል። ሆኖም ችግርና መከራው

አይቀርላቸውም። በመጀመርያ ደረጃ ከዚህ ሲሄዱ ስለኩዌት  አጠቃላይ ሁኔታ ምንም መረጃ ሳይኖራቸው ነው፡፡ በስራ

ላይ ስለሚያጋጥሙ አለመግባባቶች፣ አደጋ ቢደርስ ስለሚከፈል ካሳ፣ ኮንትራት ስለሚፈርስበት ሁኔታ ወዘተ … ምንም

የሚያውቁት ነገር የለም፡፡ ወደ ሌሎች የአረብ አገራት እንደሚጓዙት ሁሉ እነዚህም በቂ የሙያ ስልጠና እንዲሁም

የስነልቦና ዝግጅትም የላቸውም፡፡  ከዚህ የሚልኳቸው ኤጀንሲዎች ደግሞ ጥቅማቸውን ብቻ ነው የሚያስቡት፡፡ በመሃል

እነዚህ ለአገሩ ባዳ ለህዝቡ እንግዳ የሆኑ ኢትዮጵያውያን መከራቸውን ይበላሉ፡፡
ባለፈው ሰሞን በኩዌት የተዘጋጀውን ሶስተኛውን የአፍሪካ አረብ ጉባኤ ለመዘገብ ወደዚያው አምርቼ በነበረ ጊዜ እዚያ

ስላሉ ኢትዮጵያውያን በመጠኑ ለማወቅ ችያለሁ፡፡ አንዳንድ የሚያሳዝኑና የሚያስገርሙ ነገሮችም ሰምቻለሁ፡፡ አንዲት

በቤት ሰራተኝነት የተቀጠረች ኢትዮጵያዊት፣ ገና አገሩን ሳትላመድ በፊት አሰሪዎቿ ሲወጡ እየጠበቀች ግቢ ውስጥ

ትፀዳዳ ነበር፡፡ በሁኔታው ግራ የተጋቡት አሰሪዎቿ፤ ነገሩን ተከታትለው ይደርሱበትና ለምን  መፀዳጃ ቤት

እንደማትጠቀም ሲጠይቋት “እንዴት እዚህ ንፁህ ነገር ላይ እፀዳዳለሁ” ብላ እንደመለሰችላቸው ተነግሮኛል፡፡ ከኢትዮጵያ

ቀዝቃዛ አካባቢዎች በተለይ ከባሌ የሚሄዱ ሴቶች ደግሞ ስለኩዌት ከፍተኛ የአየር ሙቀት ምንም አይነት መረጃ ሳያገኙ

እየሄዱ፣ አየሩን መቋቋም አቅቷቸው ይሰቃያሉ፡፡ በመንገድ አጠቃቀም ችግር የተነሳም በመኪና አደጋ አካላቸው

ይጐድላል፡፡ ህይወታቸውን የሚያጡም አሉ፡፡
 በህጋዊ መንገድ ወደ ኩዌት ከሄዱ በኋላ የተለያዩ ችግሮች የገጠማቸው ኢትዮጵያውያን ያሉበት  መጠለያ የሚገኘው

ጃብሪያ በተባለ ሰፈር ውስጥ ነው፡፡ መጠለያው በኩዌት መንግስት እና በኢትዮጵያ ኤምባሲ ትብብር የተከፈተ ሲሆን

በአሁኑ ሰአት መጠለያውን የሚያስተዳድሩት ግለሰብ በትውልድ ፍልስጤማዊ በዜግነት ዮርዳኖስ ናቸው፡፡ በመጠለያው

ውስጥ ከአስራ አምስት የማያንሱ ኢትዮጵያውያን ሴቶችን አግኝቻለሁ። የመጠለያው ሃላፊ እንደሚሉት ቁጥራቸው

በየጊዜው ይለዋወጣል፡፡ አዲስ ገቢዎች ይመጣሉ። የገቡት ደግሞ ወይ ወደ አገራቸው ይመለሳሉ አሊያም  እዚያው ስራ

ይጀምራሉ፡፡ በመጠለያው ውስጥ ካገኘኋቸው ሴቶች መካከል ጥቂቶቹን ያነጋገርኳቸው ሲሆን ስማቸውና ምስላቸው

እንዲወጣ ስላልፈቀዱ ለቀረበላቸው ጥያቄ የሰጡትን ምላሽ ብቻ እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ፡፡

“አሰሪዬ ትደበድበኝ ነበር”
የመጣሁት ከደቡብ ወሎ ደሴ ካራጉቱ አካባቢ ነው፡፡ ከአገሬ ከመጣሁ ስምንት ወሬ ነው፡፡ እድሜዬ ሀያ  ነው፡፡ እዚህ

መጠለያ የመጣሁት ከአሰሪዎች ጋር ስላልተስማማሁ ነው፡፡ መጀመሪያ የገባሁበት ቤት አሰሪዬ ትደበድበኝ ስለነበር

ቀየርኩ። ተመልሼ የገባሁበትም ቤት ተመሳሳይ ችግር አጋጠመኝ። ታስፈራራኛለች፡፡ “ስራ አትስሪ ከኔ ጋር ቁጭ በይ፤

ሌሎች ሰራተኞች ይሰራሉ” ትለኝና መልሳ ለምን አልሰራሽም ብላ ትመታኛለች። አንድ ቀን ስትመታኝ ጆሮዬን በጣም

ስላመመኝ ወጥቼ ጠፋሁ። ተመልሼ ሁለት ወር ሰራሁ እና ደሞዜን አልሰጠኝ አለች፡፡ ለምን አትሰጭኝም ስላት  

አስወጥታ በር ዘጋችብኝ። ሌላ ቦታ አስራ አምስት ቀን ሰራሁና “ከኤምባሲ ትፈለጊያለሽ” ተብዬ እዚህ መጣሁ፡፡ አሁን

የምፈልገው የቀረብኝ የአራት ወር ደሞዜ ተሰጥቶኝ ሌላ ስራ መግባት ነው፡፡
         
“ልጄ ሳይሞትብኝ ልድረስ ብዬ ወጣሁ”
አገሬ ወግዲ ወረዳ ጫቃታ ቀበሌ ነው፡፡ ባለትዳር እና የሁለት ወንድ ልጆች እናት ነኝ፡፡ እዚህ ከመጣሁ ሁለት አመት

ጨርሻለሁ፡፡ ከአገሬ በሴትየዋ ስልክ ደውለው “አባቴ ሞተ” ብለው ነገሩኝ፡፡ “ልሂድ” ስላቸው “ቆይ ትሄጃለሽ” ብለው

አሰነበቱኝ፡፡ ከዛ ደግሞ “ልጅሽ ታሟል ድረሽ” ተባለና ተደወለ፡፡ “እባካችሁ ለስምንት ቀን ፍቀዱልኝ፤ ሄጄ ልምጣ፤

አባቴ እዚህ ሆኜ ሳላየው ሞተ፡፡ ልጄም ሳይሞትብኝ ልሂድ” ብላቸው፤ አሁን አትሄጂም አሉኝ፡፡ እኔ እሄዳለሁ አልኩ፡፡

በመሀል መስራት ስላልቻልኩ የሰውየው እናት እዚህ አመጣችኝ፡፡ እኔ መሳፈርና መሄድ ነው የምፈልገው፡፡ አባቴም

ሞተብኝ፡፡ መልሶ ልጄ ሳይሞትብኝ ልድረስ ብዬ ወጣሁ፡፡ እኔ ፍላጎቴ ለመሳፈር ብቻ ነው፡፡ አሰሪዎቼ በጣም ደህና

ሰዎች ናቸው፡፡ ሰላመኛ ናቸው፡፡ እኔ ልጄን አይቼ ነው የምመለሰው፡፡ አባቴ ሞቶ ልጄ ቢደገም እንዴት ብዬ እቆማለሁ፡፡
“ልሂድ ስላቸው የኛስ ኪሳራ ይሉኛል”         
አገሬ ከገፈርሳ በላይ ያለ ገጠር ነው፡፡ የሶስት ልጆች እናት ነኝ፡፡ ከአገሬ  ከመጣሁ አንድ አመት ጨርሻለሁ፡፡ እዚህ ጤና

አላገኘሁም፡፡ ሀኪም ቤት ስወሰድ ሀኪሞቹ “የማህፀን ችግር አለብሽ፤ ኦፕራሲዮን ትሆኛለሽ” ይሉኛል፡፡ እኔ ደግሞ የሰው

አገር ሰው ነኝ፡፡ ማንም አጠገቤ የለም፡፡ አባቴ የለ፤ እህትና ወንድሜ የሉ፤ እናቴ የለች፡፡ ፈራሁ። “መሄድ እፈልጋለሁ፤

አገሬ ላይ የምሆነውን እሆናለሁ” ስል የኛስ ኪሳራ ይሉኛል፡፡ ኮንትራትሽ ሁለት አመት ስለሆነ ሁለት አመቱን ጨርሰሽ

መሄድ አለብሽ አሉ፡፡ እኔ ደግሞ እዚህ በበሽታ እሰቃያለሁ፤ ቆሞ መስራት አቃተኝ፡፡ በሽታ አስቸገረኝ እንጂ ስራ

እወዳለሁ፡፡ ሁሉም ነገር ከአቅሜ በላይ ሆነ፡፡ እዚህ መጠለያ ከገባሁ አንድ ወሬ ነው፡፡ እኔ ከታመምኩ በኋላ ብር

አይሰጡኝም፡፡ እዚህ መጠለያ ከገባሁ በኋላ “አስተዳዳሪው እዚህ ከምትቀመጪ ስራ ብትገቢ” ብሎኝ ሞከርኩ፤ ግን

ምንም አልቻልኩም። አሁን ራሱ ሆስፒታል አድሬ ውዬ መምጣቴ ነው። ለቤተሰቦቼም እስከአሁን ይሄ ገጠመኝ

አላልኩም። እዚህም አገር እህት አለችኝ፤ ስልክ ቁጥሯን የምሰራበት ቤት ጥዬ ስለወጣሁ እስከአሁን አልሰማችም፡፡
 
“ወይ ደህና ህክምና አላገኘሁ ወይ አገሬ አልገባሁ”
የመጣሁት ከአዲስ አበባ ነው፡፡ ስምንት ወሬን እየጨረስኩ ቢሆንም የሰራሁት አራት ወር ብቻ ነው፡፡ ስራ እየሰራሁ ሳለ

በእሳት ተቃጠልኩና ያመጣኝን ኤጀንሲ ስነግረው፣ ምንም ለማድረግ ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ ሁለቱም እግሬ ተቃጥሏል። ቀኝ

እግሬ በጣም ተጎድቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤምባሲ “ካሳ ይገባታል” ሲል እነሱ “በራሷ ጊዜ ነው የተቃጠለችው” አሉ፡፡ “ስራ

ላይ እያለች ስለተቃጠለች ካሳ ያስፈልጋታል” ብሎ ነበር ግን  ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ የሰራሁበት ገንዘብ፣ ፓስፖርቴ እና

ልብሴ ያለው አሰሪዎቼ ቤት ነው። ይህን ማስመጣት የሚችለው ኤጀንሲው ነው፡፡ ግን አከሰርሽኝ በሚል ሊተባበረኝ

አልቻለም፡፡ ወይ ደህና ህክምና አላገኘሁ ወይ አገሬ አልገባሁ፡፡ ክርክር ላይ ነኝ፡፡ እኔ አገሬ መግባት እፈልጋለሁ፡፡

“ባዶ እጄን ወደ አገሬ እመለሳለሁ”
ሰፈሬ ኮተቤ ነው፡፡ ከመጣሁ ሰባት ወር ሆኖኛል። መጀመሪያ የገባሁበት ቤት በጣም ችግር ነበር፡፡ ስራ በጣም ይበዛል፡፡

ምግብ አልተስማማኝም፡፡ ቤት ለመቀየር ስጠይቅ፣ ኤጀንሲው ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ አልሰራም ብዬ ቁጭ ስል፣ አሰሪዬ

ዘመዷ ቤት ወስዳ ዘጠነኛ ፎቅ ላይ ለስምንት ቀን በረሀብ እያሰቃየች አቆየችኝ፡፡ ካስወጣችኝ በኋላ ኤጀንሲዬ ጋር

ስደውል “ህግ ያለበት አገር ነው፤ ምንም ላደርግልሽ አልችልም፣ ያለሽ አማራጭ መጥፋት ብቻ ነው” አለችኝ፡፡ ታምሜ

ሆስፒታል ስወሰድ ጠፋሁ፡፡ ኤጀንሲዬ ኤምባሲ አመጣችኝ፡፡ ሴትዮዋ በማግስቱ ዘመዷን ይዛ መጥታ “እነሱ ጋር ስሪ”

ስትለኝ፤ አልፈልግም አልኩ፡፡ “ያከሰረችኝን ትክፈልና ትሂድ” አለች፡፡ “እኔ ምንም የለኝም፤ ንብረቴ ሁሉ አንቺ ጋ ነው”

አልኳት፡፡ ሁለት ጊዜ ተመላልሳ ልውሰድሽ አለችኝ፤ አልፈልግም ስላት ፓስፖርቴንና ትኬቴን ይዛ መጣች፤ ስለዚህ ነገ  

ባዶ እጄን ወደ አገሬ እመለሳለሁ፡፡

የደፈረኝ ኢራናዊ አልተገኘም
የመጣሁ ከሀረር ነው፡፡  አንደ አመት ከስድስት ወሬ ነው፡፡ አንድ የማውቃት ኢትዮጵያዊት የተሻለ ስራ አግኝቼልሻለሁ

ብላ ደወለችልኝና ታክሲ ይዛ መጣች፡፡ ቤተሰብ ያለው ሰው ነበር ያናገረችው፤ ሄድኩኝ፡፡ አምስት ልጆችና ሚስት

አለው፡፡ ቅዳሜ፤ ልጆቹ የእረፍት ቀናቸው ነበር፡፡ ቤተሰቡን እንዳለ ሌላ ቦታ ወስዶ ማታ አንድ ሰአት ላይ ለብቻው

ሰክሮ መጣና አስገድዶ ደፈረኝ፡፡ ሴትዮዋ ስታየኝ “ምን ሆነሽ ነው?” ብላ ጠየቀችኝ፤ እንዳልነግራት ፈርቼ “ወድቄ ነው”

አልኳት፡፡ ጠዋት ወጣሁና  ኤጀንቷ ጋር ሄድኩ፡፡ “ለምን እንደዚህ ታደርጊኛለሽ?” ብዬ ስንደባደብ “መቶ ዲናር ከፍሎኝ

ነው” አለችኝ። ፖሊስ ጋ ሄጄ ነገርኩ፡፡ ሁለታችንንም እስር ቤት አስገቡን፡፡ አንድ ወር ቆየን፡፡ እሷ ድርጊቷን ስላመነች

ወደ ኢትዮጵያ አሳፍረዋታል፡፡  እኔን ወደ ኤምባሲ ሂጂ አሉኝ፡፡ ኤምባሲ ሄድኩ፤ ከዛ የማውቃቸው ልጆች ስራ

አስገቡኝ፡፡ እሰከ አራት ወር ደሜ ሳይመጣ ሲቀር፣ እቃዬን ይዤ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሄድኩኝ፡፡ እዛው ቆይቼ ወለድኩ፡፡

አሁን ሶስት ሳምንት ሆኖኛል ከመጣሁ፡፡ የወለድኩት ከኩዌት ዜጋ አለመሆኑ ስለታወቀ “ልጅሽን ይዘሽ አገርሽ

ትሳፈሪያለሽ” ተብዬ እየተጠባባቅሁ ነው። የደፈረኝ ኢራናዊም አልተገኘም፡፡ የወለድኩትን ልጅ እናሳድግልሽ የሚሉ ሰዎች

በተደጋጋሚ ይመጣሉ። እንዴት አድርጌ ልስጣቸው፡፡ አገሬ ላይ ድንጋይ ተሸክሜም ቢሆን አሳድገዋለሁ፡፡ ከመደፈር

አንስቶ እስከዛሬ ስንት የተሰቃየሁበት ልጄ ነው፡፡ አሁን ሶስት ወር ከአስራ አምስት ቀኑ ነው፡፡
እዚያው መጠለያ ውስጥ ያገኘኋት ሌላ ኢትዮጵያዊት ደግሞ ምንም አትናገርም፡፡ የመጠለያው አስተዳዳሪ “ይቺን

የማትናገር ልጅ እንዴት ለስራ ከኢትዮጵያ ላኳት?” ሲል እኔኑ ጠየቀኝ፡፡ እውነት የማትናገር መስሎኝ በመገረም “ከየት

ነው የመጣሽው?” ብዬ ብጠይቃት እንባዋን ዘረገፈችው፡፡ መጠለያው ውስጥ ከገባች ጀምሮ ከማንም ጋር ተነጋግራ

እንደማታውቅና ምን እንደሆነች ስትጠየቅ ማልቀስ እንደምትጀምር ነገሩኝ፡፡ እኔም ስለያት እያለቀሰች ነበር፡፡ የትም ሆነ

የትም የስደት ነገር ትርፉ ሰቆቃና ለቅሶ ነው - በተለይ ለኢትዮጵያውያን፡፡

የዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እና የኢ/ር ሃይሉ ሻውል ቲተርና የፓርቲያቸው ማህተም
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ጨምሮ የበርካታ ሚኒስቴር መ/ቤቶች ማህተም
የኦነግና የኢሜሬት ኢምባሲ ማህተሞች ተገኝተዋል


የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጨምሮ የ132 መንግስታዊና የግል ድርጅቶችን ማህተም እንዲሁም የፖሊስ ኮሚሽነሮችን

እና  የተለያዩ ግለሠቦችን ቲተር በህገወጥ መንገድ በመያዝ ለግለሠቦች ሃሠተኛ ማስረጃዎችን ሲሠራ ነበር የተባለው

ተጠርጣሪ ላይ በፀረ ሙስና ኮሚሽን አቃቤ ህግ የቀረበው ክስ እንዲሻሻል ፍ/ቤት ብይን ሰጠ፡፡
አቃቤ ህግ በተጠርጣሪው አቶ ኮከብ ጥላሁን አማረ ላይ ሁለት ክሶችን ያቀረበ ሲሆን በመጀመሪያው ክስ ላይ የውጭ

ጉዳይ ሚኒስቴርን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች፣ የኤምባሲዎች፣ የግልና የመንግስት

ዩኒቨርስቲዎች፣ የትምህርት ሚኒስቴርና የሃገር አቀፍ ፈተናዎች ድርጅት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የአስተዳደሩን

የተለያዩ ቢሮዎች የክልል መንግስታት የተለያዩ መስሪያ ቤቶች የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን እና የአዲስ አበባ ፖሊስ

ኮሚሽን  የቦሌ ኢምግሬሽን የኢትዮ ቴሌኮም እና የንግድ ሚኒስቴር የተለያዩ ቢሮዎችና ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ማህተም

እንዲሁም የፖሊስ ኮሚሽነሮችና ኢንስፔክተሮችን ጨምሮ የተለያዩ ግለሠቦችን ቲተር በተጨማሪም የኢትዮጵያ ነፃ ፕሬስ

ጋዜጠኞች ማህበርንና የተለያዩ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎችን ማህተምና የሊቀመንበሮቻቸውን ቲተር ይዞ መገኘቱን

አመልክቷል፡፡
ተከሳሹ ከመንግስት ሚኒስቴር መስርያ ቤቶችና ከተለያዩ የመንግስት ተቋማት ባሻገር እንዲሁም አሜሪካ እና የግብፅ

ኤምባሲዎችን ማህተም፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ደግሞ የኦሮሞ ነፃ አውጪ ግንባር (ኦነግ)፣ የአንድነት

ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ማህተሞች እና የሌሎች የተቃዋሚ የፖለቲካ

ድርጅቶች ማህተም ይዞ መገኘቱ ተገልጿል፡፡ የኢ/ር ኃይሉ ሻውል እና የዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳን ቲተሮችም ይዞ ተገኝቷል

ይላል የክስ ዝርዝሩ፡፡
ከግል ተቋማት መካከልም የእንይ ሪል ስቴት ማህተም፣ ብዛት ያላቸው የግል ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆችን ማህተም፣

የተለያዩ ባንኮችን ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ማህተም እንዲሁም መንግስት ወደ ግል ይዞታነት እንዲዞር በማሠብ ተደጋጋሚ

ጨረታ የሚያወጣበት የግዮን ሆቴሎች ድርጅት ማህተም ይገኙበታል፡፡
በአቃቤ ህግ የክስ ዝርዝር ላይ ተከሣሹ በድምሩ 132 ከሆኑት የተለያዩ መስሪያ ቤቶች ማህተምና ቲተር እንዲሁም ህጋዊ

ሠነዶች በተጨማሪም ኮምፒውተሮች፣ ስካነር፣ ልዩ ልዩ የሃሠት ሠነዶች ተዘጋጅተው የሚገኙባቸው ሲዲዎችን ይዞ

በመገኘቱ፣ በፈፀመው የመንግስትን ወይም የመንግስት ባለስልጣናት ማህተሞችንና የህዝብ ጥቅምን የሚመለከቱ ነገሮችን

ሃሠተኛ አድርጐ ወይም አስመስሎ ለመስራት የሚያገለግሉ መሣሪያዎችን ይዞ መገኘት ወንጀል ተከሷል፡፡
በኮሚሽኑ አቃቤ ህግ በሁለተኛ ክስነት የቀረበውም ግለሠቡ እነዚህን ማህተሞች፣ ቲተሮችና ሠነዶች በመጠቀም ለተለያዩ

ግለሠቦች ህገ ወጥ የትምህርት ማስረጃ፣ የልደት ሠርተፊኬት፣ የተለያዩ ድጋፍ ሠጪ ደብዳቤዎች፣ የመንጃ ፈቃድ፣ የስራ

ልምድ፣ የንግድ ፈቃድ፣ የመኪና ሊብሬ፣ የኤምባሲ ደብዳቤዎች እንዲሁም ፓስፖርቶች እና ሌሎች ብዛት ያላቸውን

ህገወጥ ሠነዶች እጁ እስከተያዘበት ሐምሌ 2005 ዓ.ም ድረስ አስመስሎ በማዘጋጀት፣ ተከሣሹ በፈፀመው መንግስታዊ

እና የህዝብ ጥቅምን የሚመለከቱ ሠነዶችን አስመስሎ ማዘጋጀት የሙስና ወንጀል ተከሷል ይላል፡፡
የመንግስት እና የግል ተቋማት ሠነዶች መስለው በተከሣሹ የተዘጋጁ ሃሠተኛ ሠነዶች በተከሣሹ መኖሪያ ቤት በተደረገው

ብርበራ መገኘታቸውም በክሱ ተመልክቷል፡፡
ከትናንት በስቲያ ሃሙስ እለት የዋለውና የሙስና ጉዳዮችን የሚመለከተው የከፍተኛው ፍ/ቤት  1ኛ ወንጀል ችሎትም

ቀደም ባለው ቀጠሮ ከተከሣሽ የቀረበውን የክስ መቃወሚያ እና ከአቃቤ ህግ የተሠጠውን የመቃወሚያ መልስ ከመረመረ

በኋላ በሠጠው ብይን፤ ተከሣሹ ኮሚሽኑ ክሡን የማቅረብ ስልጣን የለውም በማለት ያቀረበውን ተቃውሞ

እንዳልተቀበለው አስታውቆ፤ ከሣሽም ሊያሻሽላቸው ይገባል ያላቸውን ጉዳዮች አስታውቋል፡፡ በዚህ መሠረት ብርበራ

የተካሄደበትን ቤት አድራሻ በተመለከተ አቃቤ ህግ በተገቢው መንገድ አሟልቶ እንዲያቀርብ፣ “ሌሎች በርካታ ሃሠተኛ

ሠነዶች” ተብለው የተመለከቱ በዝርዝርና በቁጥር እንዲጠቀሱ እንዲሁም የመንግስት እና የግል ሠነዶች ተለይተው

እንዲቀርቡ ሲል ፍ/ቤቱ ብይን የሠጠ ሲሆን በአጠቃላይ አቃቤ ህግም ክሡን አሻሽሎ እንዲያቀርብ ብሏል፡፡
ቀጣዩን ሂደት ለመመልከትም መዝገቡን ለታህሣስ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጥሯል፡፡  

Published in ዜና

          በትግራይ ክልል ፖሊስ ክስ የቀረበበት የ“ሎሚ” መፅሄት ዋና አዘጋጅ ሰናይ አባተ የክሱ መነሻ በግንቦት ወር 2005 ዓ.ም “የትግራይ እስር ቤትና ጓንታናሞ” በሚል ርዕስ የታተመ የአቶ አስገደ ገብረስላሴ ፅሁፍ እንደሆነ ገለፀ። በትግራይ ክልል ሁለት ልጆቻቸው መታሰራቸውን በመጥቀስ አቶ አስገደ ባቀረቡት ጽሑፍ፣ እስር ቤቱ በተራራ የተከበበ አስጨናቂ ሸለቆ በማተት አሸባሪዎች ከሚታሰሩበት፣ ከጓንታናም ጋር አመሳስለውታል፡፡ የትግራይ ፖሊስ በበኩሉ፣ የአቶ አሰገደ ጽሑፍ የእስረኞች አያያዛችንን ለማጠልሸት እና የፖሊስን ተአማኒነት ጥርጣሬ ላይ ለመጣል ያለመ ነው ሲል ክስ ማቅረቡን የሎሚ መጽሔት ዋና አዘጋጅ ተናግሯል፡፡ ሐሙስ ረፋድ ላይ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ተገኝቶ ቃሉን የሰጠው ዋና አዘጋጁ፤ “ፅሁፉ በሎሚ መፅሄት ከመታተሙ በፊት በኢትዮ ምህዳር ጋዜጣም ላይ ተስተናግዷል” ብሏል፡፡ ታተመ የመጣ ጽሑፍ በህግ ሊያስጠይቅ የሚችለው ከስድስት ወር ላልበለጠ ጊዜ እንደሆነ በመገናኛ ብዙሃን አዋጅ ላይ የተገለፀ ሲሆን፤ ፅሁፉ ከተስተናገደ ከሰባት ወራት በኋላ ክስ የቀረበበት ምክንያት አልገባኝም ብሏል - ሲሳይ አባተ፡፡ “አቶ አሰገደ ትግራይ ውስጥ እየበጠበጠ ያለ ሰው ነው፤ ፅሁፉን እንዴት አግኝታችሁ አስተናገዳችሁ” በሚል በመርማሪዎች ጥያቄ እንደቀረበበት የገለፀው ዋና አዘጋጁ ሲሳይ አባተ፤ በተለያዩ ጋዜጦችና መፅሄቶች ላይ በመፃፍ የሚታወቁት አቶ አሰገደ ፅሁፉን ልከውልን እንዳስተናገድን ተናግሬያለሁ ብሏል፡፡

Published in ዜና
Page 3 of 19