Monday, 29 April 2024 07:45

ዘመን ባንክ ከሊንክድኢን ለርኒንግ ጋር በአጋርነት ለመሥራት ተስማሙ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ዘመን ባንክ፤ የሠራተኞቹን ዕውቀትና ክህሎት ለማሳደግ፣ በዓለም  ትልቁ የኢንተርኔት የመማሪያ መድረክ ከሆነው ሊንክድኢን ለርኒንግ ጋር የአጋርነት ስምምነት ተፈራረመ፡፡
የዘመን ባንክ የሰው ሀብት ምክትል ዋና ኦፊሰር አቶ ታከለ ዲበኩሉ ስምምነቱን አስመልክቶ ባደረጉት ንግግር፤ “ዘመን ባንክ ለሰራተኞቹ ቀጣይነት ያለው የመማርና የሙያ እድገት ባህልን ለማሳደግ ቁርጠኛ ነው። ከሊንክድኢን ለርኒንግ ጋር ያደረግነው ስምምነት፣ ይህንን ቁርጠኝነት የሚያጎላ ከመሆኑም ባሻገር ሠራተኞቻችን የፋይናንስ ዘርፉ  የሚጠይቀውን ችሎታ፣ እውቀትና ክህሎት እንዲያዳብሩ  የሚረዳ ነው፡፡” ብለዋል፡፡
የሊንክድኢን ታለንት ሶሉዩሽን ዋና ኃላፊ ማቲው ግሬይ በበኩላቸው፤ ”ከዘመን ባንክ ጋር ያደረግነው ስምምነት የሰራተኞቹን የክህሎትና የእውቀት ክፍተቶች ለማሟላት እድሉን የሚሰጠን ከመሆኑም በላይ ሊንክድኢን ለርኒንግ በአፍሪካ ተመራጭ የክህሎት ልማት መድረክ ሆኖ  መቀጠሉን ስለሚያሳይ እጅግ ተደስተናል።“ ብለዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም፤“ የዘመን ባንክ የሰው ሃብት ስትራቴጂ በቀጣይ አመታት ይበልጥ እንዲጎለብትና ውጤታማ እንዲሆን አብረን እንሰራለን።” ሲሉ ተናግረዋል፡፡


Read 165 times