Friday, 05 April 2024 20:15

የደራሲ እያዩ ደባስ ሦስተኛ መጽሐፍ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የደራሲ እያዩ ደባስ ሦስተኛ መጽሐፍ “ፓርታ” ለንባብ የበቃ ሲሆን፤ ደራሲው በመግቢያው ላይ እንዳሰፈረው፤ “ፓርታ ላልተጻፈው የሐሳብ ዕዳ ክፍያ ይሆን ዘንድ ነው። እነርሱን የመሆን የሐሳብ ዕዳ ውስጥ ለገባ አንድ አሳቢ፣ ሰውን ነጻ የማውጣት የቀናነት ትግል ነው።

መጽሐፉ የትችት፣ የመወቃቀስ፣ የሐሜትና የጥላቻ ግብ የለውም። ከሐሳብነት የተረፈ የመቆሚያ ሥፍራም የለው፤ ብሏል ደራሲው።

የዚህ መጽሐፍ ዋና ገጸ-ባሕርይ “ሐሳብ” መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን፤ደራሲው የእድሜ ዘመን ንባብ ያላቸውን ታዋቂ ግለሰቦችን ገጸ ባህሪ አድርጎ በማምጣት፣ለሃሳብ የበረታ ድርሰት ከትቧል፡፡
 
“ፓርታ” በ273 ገጾችና 68 ምዕራፎች የተቀነበበ መጽሐፍ ሲሆን አሳታሚና አከፋፋዩ ጃዕፈር መጻሕፍት መደብር ነው ተብሏል፡፡ መጽሐፉ  በ400 ብር ለአንባቢያን ቀርቧል።

Read 541 times