Thursday, 15 February 2024 20:28

ጀምበሩ ደመቀ “እሳቱ ሰ” የተሰኘ ሁለተኛ አልበሙን በቅርቡ ይለቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በራሱ ስም በተሰየመው የመጀመሪያ አልበሙ የአፍሪካ ጃዝ አባት ከሆኑት  ከአንጋፋው ዶ/ር ሙላቱ አስታጥቄ ጋር በመጣመር “ዓይፈራም ጋሜ”ን ያስኮመኮመን አርቲስት ጀምበሩ ደመቀ፤ በቅርቡ “እሳቱ ሰ” የተሰኘ ሁለተኛ አልበሙን ለአድማጭ እንደሚያደርስ ተገለጸ፡፡

 ጀምበሩ በቅርቡ ከኡኖ ጋር ባቀነቀነው “ተፍ ተፍ” በተሰኘው ነጠላ ዜማው፣ ከፍተኛ ተቀባይነትን ማግኘቱ የሚታወቅ ነው፡፡  

በ21 አመቱ የመጀመርያውን አልበም በ2014 ዓ.ም ያወጣው ጀምበሩ ደመቀ፤ ወጣት የሂፕሆፕ አድናቂዎችን ልብ ለመግዛት ጊዜ አልፈጀበትም።
 
አርቲስቱ በሁለተኛው አዲስ አልበሙ  ከወጣት አቀንቃኞች ጋር የተጣመረባቸው ስራዎች የተካተቱ ሲሆን፤ ከባህር ማዶ ከኬንያው እውቅ አርቲስት ሬገን ዳንዲ እና ከትውልደ ብሩዎንዲ በዜግነት እንግሊዛዊው ሙቲ  እንዲሁም ከሀገር ውስጥ ከሌሎች ወጣት አርቲስቶች ጋር በአንድነት መሥራቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 633 times