Sunday, 11 February 2024 00:00

ኮትዲቯር የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ምሽት 5:00 ሰዓት ላይ በተካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ አስተናጋጇ ኮትዲቯር ናይጄሪያን 2 ለ 1 በማሸነፍ ዋንጫውን አንስታለች።

የኮትዲቯርን የማሸነፊያ ግቦች ፍራንክ ኬሲ እና ሴባስቲያን ሀለር  አስቆጥረዋል።ናይጄሪያን ከሽንፈት ያላዳነችውን ብቸኛ ግብ ደግሞ ዊሊያም ትሩስት ኢኮንግ አስቆጥሯል።
በዚህም ዝሆኖቹ የአፍሪካ ዋንጫን ለሶስተኛ ጊዜ ማንሳት ችለዋል።

Read 772 times