Saturday, 27 January 2024 00:00

ብሬክስሩ ትሬዲንግ ለ41 ሺህ ዜጎች የሰብዕና ለውጥ ስልጠና መስጠቱን አስታወቀ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ካፒታሉን ወደ 1 ቢሊዮን ብር አሳድጓል

ብሬክስሩ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ባለፉት አራት ዓመታት ከ41 ሺህ በላይ ለሆኑ ዜጎች የሰብዕና ለውጥ ሥልጠና መስጠቱንና በስልጠናው በርካታ በኢኮኖሚ ራሳቸውን የለወጡ ዜጎች ማብቃቱን አስታወቀ፡፡ ድርጅቱ ይህንን የገለፀው ባለፈው ረቡዕ ጥር 15 ከሰዓት በኋላ በሸራተን አዲስ ሆቴል ላሊበላ አዳራሽ የተመሰረተበትን 4ኛ ዓመት በዓል  ባከበረበት ወቅት ነው፡፡ብሬክ ስሩ ትሬዲንግ በ2012 ዓ.ም “ቅን” (Genuine) በተሰኘ 17 ባለ ራእይ ሰዎች ጥምረት የተቋቋመ ሲሆን፣ አላማውም ባለ ራዕይ፣ ቅን፣ ጤናማና ባለፀጋ ትውልድን መፍጠር እንደሆነ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አብዱል ፈታህ ሁሴን ተናግረዋል፡፡ ድርጅቱ በአራት ዓመት ጉዞው ዜጎች በአዎንታዊ መልኩ ሰብዕናቸውን በመገንባት በኢኮኖሚ ያደጉና ሀገራቸውን የሚጠቅሙ እንዲሆኑ እየተጋ እንደሚገኙ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጨምረው ገልፀዋል፡፡ ብሬክስሩ በ2.4 ሚ ብር ካፒታል ተነስቶ በአራት ዓመታት ውስጥ ካፒታልን ወደ 1 ቢሊዮን ማሳደጉንና አሁንም አክሲዮን በመሸጥ ላይ መሆኑን የገለፁት ዋና ስራ አስፈፃሚው፣ ከሰብዕና ግንባታ በተጨማሪም ወደ ተለያዩ ቢዝነሶች እየተሰማራ መሆኑንና በቅርቡ አንድ ት/ቤት መክፈቱን እንዲሁም “የኔ” የተሰኘ የሰብዕና ግንባታ ስልጠና ፕሮጀክት ማቅረቡንና በትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ እንደሚሰማራም ተናግረዋል፡፡
በብሬክስሩ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር አራተኛ ዓመት የምስረታ ክብረ በዓል ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት፣ የድርጅቱ ከፍተኛ ሀላፊዎችና አባላትን እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል፡፡

Read 705 times