Thursday, 25 January 2024 19:54

ሮፍናን ሁለት የሙዚቃ አልበሞችን በአንድ ቀን ሊለቅ ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

"ህልም ነበረኝ፤ ሁለት አልበም በአንድ ቀን ማውጣት"

ሙዚቀኛ ሮፍናን ኑሪ፤ በአንድ ቀን "ሀራንቤ" እና "ኖር" የተሰኙ ሁለት አልበሞችን፣ "ዘጠኝ" በሚል አብይ ርዕስ ውስጥ ለአድማጮች እንደሚያደርስ ተጠቆመ፡፡

"ይህ አልበም ማሳረጊያ ፕሮጀክቴ ነው። በጣም ደክሜበታለሁ። ቴክኒካል ጉዳዮችን ጨምሮ ብዙ የተለፋበት ነው። የኔን እድገት የምታዩበት አልበም  ነው" ብሏል፤ድምጻዊው።

አክሎም ሲናገር፤ "ህልም ነበረኝ፤ ሁለት አልበም በአንድ ቀን ማውጣት" ብሏል፡፡

በ"ዘጠኝ" አብይ ርዕስ ውስጥ ያሉት ሁለቱ አልበሞች፣ በአጠቃላይ ሃያ አንድ ሙዚቃዎችን ይዘዋል ተብሏል።

በአልበሞቹ ላይ ሀይሌ ሩት፣ ሸዊት መዝገቡ፣ የልጅ ተመስገን ልጆችን ጨምሮ የሀገር ውስጥና የውጪ የሙዚቃ ባለሞያዎች ተሳትፈዋል።

"ሀራንቤ" እና "ኖር" አልበሞች ከሦስት ሳምንት በኋላ ለሙዚቃ አድማጮች እንደሚደርሱ ታውቋል፡፡

አልበሞቹ በሮፍናን ዩቲዩብ ቻናልና በሁሉም የሙዚቃ ማሰራጫ መተግበሪያዎች በኩል ይለቀቃሉ።

ከአልበሙ ውስጥ ለሁለቱ Yሙዚቃ ቪዲዮዎች የተሰራ ሲሆን፤ ከአልበሙ የተወሰደ አንድ የሙዚቃ ቪዲዮ ዛሬ ማታ ለአድማጮች ይደርሳል ተብሏል።

Read 515 times