Saturday, 06 January 2024 21:18

የድምጻዊ ቴዲ ዮ ሦስተኛ አልበም ትናንት ተለቀቀ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ድምጻዊ ቴዎድሮስ አሰፋ (ቴዲ ዮ) ከዞጃክ ወርልድ ዋይድ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን  “ይለያል” የተሰኘ ሦስተኛ አልበሙን በትላንትናው ዕለት ለገበያ ማቅረቡ ታውቋል፡፡ ሦስተኛ አልበሙ መውጣቱን አስመልክቶ ድምጻዊው ከትላንት በስቲያ በማሪዮት ሆቴል ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ፤አልበሙ በአይቲውስ እና በአማዞን ከፊታችን ረቡዕ ጀምሮ በይፋ እንደሚለቀቅ ጠቁሞ፣ አዲሱ አልበም  10 ሙዚቃዎችን ማካተቱንና ሦስቱ የቪዲዮ ክሊፕ እንዳላቸው አመልክቷል፡፡ በዚህ አለም አቀፍ ጥራቱን የጠበቀ ነው በተባለለት የሙዚቃ አልበም ላይ በአጃቢነት ከተሳተፉ ታዋቂ ድምፃዊያን መካከል ሱራፌል ፣ ካስማሰ ፣ ቃል ኪዳን ፣ ኩል ሱሬ እና እዮቤድ ይገኙበታል ተብሏል፡፡ በቅንብርና በሚክሲንግ ቢግ ባድ ሳውንድ እንደተሳተፉበት ታውቋል፡፡


Read 808 times