Saturday, 23 December 2023 20:56

”ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ እንደ ስሙ ጥራት ያለው ስራ የሚያከናውን ነው” -የሲዳማ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር-

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞና  ሌሎች ከፍተኛ የክልሉ የሥራ ሀላፊዎች ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በዛሬው ዕለት በመሐል ሐዋሳ ፒያሳ ላይ አስገንብቶ ያስመረቀውን ሁለገብ ሕንጻ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

 የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር አቶ  ደስታ ሌዳሞ ከጉብኙቱ በኋላ ባደረጉት ንግግር፤ ''ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በሲዳማ ክልልም ሆነ በሃዋሳ ከተማ አስተዳደር ተጨማሪ ኢንቨስትመንት ማስፋፋት ለሚያቅዱ ሌሎች አካላት ምሳሌ መሆን የሚችል ተግባር እያከናወነ ነው'' ብለዋል።

''ባንካችሁ ለከተማችን ተጨማሪ ውበት ያጎናፀፈ ዘመናዊ ሕንጻ አስገንብቶ ለምረቃ በማብቃቱ እንኳን ደስ አላችሁ” ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ''ንብ ባንክ እንደ ስሙ ጥራት ያለው ስራ የሚያከናውን ባንክ ነውም'' ሲሉ አክለው ተናግረዋል፡፡



በሐዋሳ ከተማ የተሟላ የባንክ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ 20 ዓመታትን ያስቆጠረው ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ፤ በከተማዋ የዲስትሪክት ፅ/ቤት ያለው ሲሆን  የቅርንጫፎቹንም ቁጥር 8 አድርሷል።

 ባንኩ በሐዋሳ ፒያሳ ያስገነባውን ባለ 12 እና ባለ 14 ወለል መንትያ ሕንጻ በዛሬው ዕለት የተለያዩ የመንግሥት የሥራ ሀላፊዎች፣ የባንኩ የቦርድ ከፍተኛ የስራ አመራር፣ ማኔጅመንትና የከተማዋ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ማስመረቁን ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 1430 times