Saturday, 16 December 2023 19:42

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለሠራተኞቹ የብቃት ምዘና ፈተና ሊሰጥ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ፈተናውን ማለፍ ያልቻሉ መቋቋሚያ ተሰጥቷቸው ከስራ ይሰናበታሉ ተብሏል

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስሩ ለሚገኙትና አዲስ የመዋቅራዊ ማሻሻያ አደረጃጀት ጥናት ባደረጉ ተቋማት ውስጥ ለሚገኙ ሁሉም ሠራተኞችና የስራ ኃላፊዎች የብቃት መመዘኛ ፈተና ሊሰጥ ነው ተባለ። ፈተናውን ያላለፉ ሰራተኞች መቋቋሚያ ተሰጥቷቸው ከስራ ይሰናበታሉ ተብሏል።
ከተማ አስተዳደሩ በተለያዩ ዘርፎች ለሰራኞቹ የብቃት ምዘና ፈተናውን የሚሰጥ ሲሆን በመጀመሪያው ዙር የብቃት ምዘና ፈተናውን የሚወስዱት የቤቶች ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት፣ የስራ ኢንተርፕራይዝ ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት፣ የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ጽ/ቤት፣ ህብረት ስራ ጽቤት የመሬት ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት መሆናቸውም ታውቋል። የብቃት ምዘና ፈተናው የሚሰጠው በክፍለ ከተሞቹና በከተማ አስተዳደሩ ስር ባሉ መዋቅሮች እንደሆነም ታውቋል።
የብቃት ምዘና ፈተናውን የወሰዱ ሠራተኞች ፈተናውን ማለፍ ካልቻሉ ሁለት የውሳኔ አማራጮች የቀረቡ ሲሆን፤ አንደኛው አማራጭ ሰራተኛ ድልድሉ ከመደረጉ በፊት አጭር ስልጠና ተሰጥቷቸው ፈተናውን በድጋሚ እንዲወስዱ የሚደረግ ሲሆን ሌላኛው አማራጭ ደግሞ ወደ ሌላ ተቋም ተዛውረው ባላቸው የትምህርት ዝግጅትና በነበራቸው ደመወዝ እንዲመደቡ ይደርጋል ተብሏል። ከእነዚህ ውጪ የሆኑት ደግሞ የማቋቋሚያ ድጋፍ ተደርጎላቸው ከሥራ እንደሚሰናበቱ ተነግሯል። ከስራ እንዲሰናበቱ ያደርጋል ተብሏል። በሃላፊነት ደረጃ ላይ ተመድበው ሲሰሩ የነበሩና የብቃት ምዘና ፈተናውን ማለፍ ያልቻሉ ሠራተኞች ደግሞ ከነበሩበት የስራ መደብና ደመወዝ ዝቅ እንደሚሉ ተገልጿል።የብቃት ምዘና ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ሜያቸው ለጡረታ የደረሱና ጡረታ መውጣት የሚፈልጉ ሠራተኞች በፍቃደኝነት የጡረታ መብታቸውን ማስከበር እንደሚችሉም ታውቋል።
የአስተዳደሩ ሰራተኞች በከተማ አስተዳደሩ ተግባራዊ ሊደረግ ስለተዘጋጀው የብቃት ምዘና ፈተና የሚያውቁት ነገር እንደሌለና ዱብዕዳ እደሆነባቸው ምንጮች ጠቁመዋል። ፈተናው በቀጣዮቹ ሳምንታት ውስጥ እንደሚደረግና መጪው ጥር ወር በፊት እንደሚጠናቀቅ ታውቋል። የኢትዮጵያ ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ መርሻል ብርሃኑ ጁላ ሰሞኑን ለፋና ቴሌቪዥን በሰጡት ቃለ-መጠይቅ የድሮን ጥቃቱን አስመልክተው
ሲናገሩ “ድሮን እኮ የተሰራው ለጦርነት ነው፣ለውጊያ ነው የገዛነው ልንዋጋበት ነው እንጂ ድሮን አለን እያልን በሚዲያ ልንገልጸው አይደለም የጦር መሳሪያ ነው ልክ እንደክላሹ ክላሽ የአቅሙን ይሰራል ሌላውም የአቅሙን ይሰራል፣ ድሮንም የራሱን ስራ ይሰራል፡፡ ድሮን እኛ የምንጠቀመው ለስብስብ ዓላማ ነው፡፡ ለወታደራዊ ስብብ ኢላማ የሚባል ነገር አለ፡፡ ስብስብ ኢላማ ማለት የጠላት ጠንካራ ቋጠሮ ማለት ነው፡፡ የጽንፈኛ
ስብስብ ስናገኝ በድሮን እንመታለን”ብለዋል፡፡

Read 1698 times