Friday, 10 November 2023 09:11

"ወደ ፍቅር ጉዞ" ዛሬ ምሽት በወመዘክር አዳራሽ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በቢኒያም አቡራ የተዘጋጀውና "ወደ ፍቅር ጉዞ" የተሰኘው፣ የአንጋፋውን ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሣሁን የዘፈን ግጥሞች የሚዳስሰው መጽሐፍ ዛሬ ከ11፡30 ጀምሮ በወመዘክር አዳራሽ እንደሚመረቅ ደራሲው ለአዲስ አድማስ አስታውቋል፡፡

መጽሐፉ በስድስት ምዕራፎች ተከፋፍሎ በ206 ገጾች የተቀነበበ ሲሆን፤ በ320 ብር  ለገበያ ቀርቧል ተብሏል።

ቢኒያም አቡራ፤ ከዚህ ቀደም የተወዳጇን ድምጻዊት እጅጋየሁ ሽባባው የዘፈን  ግጥሞች የሚዳስስ “ባለቅኔዋ ሶሪት” የተሰኘ  መጽሐፍ ማሳተሙ  አይዘነጋም።     

 የቴሌግራም ቻናልችንን  በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas                                  

Read 869 times