Saturday, 24 June 2023 20:50

“የሊስትሮው ማስታዎሻ” መፅሐፍ ሰኞ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  የጋዜጠኛ ታምሩ ከፈለኝ የመጀመሪያ ሥራ የሆነው “የሊስትሮው ማስታዎሻ” ልብ ወለድ መፅሐፍ የፊታችን ሰኞ ሰኔ 19 ቀን 2015 ከቀኑ 10፡00 ጀምሮ አራት ኪሎ ኢክላስ ህንፃ ላይ በሚገኘው ዋልያ መፃህፍት ቤት ይመረቃል። መፅሐፉ በዋናነት አንድ ጫማ በማስዋብ ስራ ላይ የሚተዳደር ሊስትሮን ህይወት የሚዳስስና የሚያስቃኝ ልብ-ወለድ ታሪክ ስለመሆኑ የመፅሐፉ ደራሲ ጋዜጠኛ ታምሩ ከፈለኝ ገልጿል። በ135 ገፅ ተቀንብቦ በ300 ብር ለገበያ በቀረበው በዚህ መፅሐፍ ምረቃ ላይ የመፅሀፍ ዳሰሳ፣ ከመፅሐፉ የተመረጡ ታሪኮች ንባብና የተለያዩ ኪነ-ጥበባዊ መሰናዶዎች ለታዳሚ ይቀርባሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ወጣትና አንጋፋ ደራሲያን፣ የስነ-ፅሁፍ አፍቃሪያን፣ የሚዲያ ባለሙያዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በምረቃው ላይ ይታደማሉም ተብሏል።

Read 1603 times