Saturday, 24 June 2023 20:52

“ከአቧሬ ካዛንቺስ እስከ ኮለምበስ ኦሃዮ“ መጽሐፍ ሰኞ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 በዳንኤል ተፈራ ማሞ የተጻፈው “ከአቧሬ ካዛንቺስ እስከ ኮለምበስ ኦሃዮ“ የተሰኘ መጽሐፍ፣ የፊታችን ሰኞ ሰኔ 19፣ ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ በሃገር ፍቅር ትንሹ አዳራሽ እንደሚመረቅ ተገለጸ፡፡
ጸሃፊው፤ በስደት ህይወቱ ያሳለፋቸውን ውጣውረዶች፣ አስተማሪና አዝናኝ ገጠመኞች  እንዲሁም በጀብዱ የተሞላ እውነተኛ ታሪኩን ነው ለአንባብያን ያበረከተው ተብሏል፡፡
የሥነጽሁፍ ባለሙያው ደሳለኝ ሥዩም በመጽሐፉ ጀርባ ላይ ባሰፈረው አስተያየት፤ “በዳንኤል ተፈራ ማሞ ህይወት ውስጥ ዕውቂያ ያልነበራቸው ወይም የሌላቸው የኪነጥበብ ሰዎች፣ የፖለቲካ ሰዎች፣ ወይም ባለሃብቶች የሉም ማለት ይቻላል፤ ከብርሃኑ ነጋ እስከ ዲማ ነገዎ፣ ከጎሹ ወልዴ እስከ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ ከአዲሱ ለገሰ እስከ መለስ ዜናዊ፣ ከአሃዱ ሳቡሬ እስከ ማናህሎሽ ጎላ (የአዜብ መስፍን እናት)፣ ከሰጠኝ መርቆ እስከ አስቴር አወቀ፣ ከሙለር ሪል እስቴት እስከ ቀበሪቾ ሬስቶራንት ዳንኤል የማያውቃቸው ምስጢሮች ወይም መረጃዎች የሉም፤ ስለሁሉም ተሰምተው የማያውቁ መረጃዎች ይነግረናል፡፡ በሌላ ጥበብ ውስጥ ላሉ ሰዎች አንድ ብቻ ጥያቄ ጣል ላድርግ፤ ይሄ ታሪክ ፊልም ካልሆነ የትኛው ታሪክ ፊልም መሆን ይችላል?” ሲል ጠይቋል፡፡
በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ ጥናታዊ ጽሁፍና ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች እንደሚቀርቡ የተጠቆመ ሲሆን፤ በመርሃግብሩ ላይ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የሥነጽሁፍ ባለሙያዎችና የክብር እንግዶች እንደሚታደሙም ታውቋል፡፡   


Read 1668 times