በመላው አለም በአሁኑ ወቅት በስራ ላይ ከሚገኙት ተጨማሪ 1 ሚሊዮን ያህል አዋላጆች እንደሚያስፈልጉና አዋላጆችን በበቂ መጠን አሰልጥኖ ማሰማራት በአለማችን ከሚከሰቱት የእናቶችና ጨቅላዎች ሞት 60 በመቶ ያህሉን ማስቀረት እንደሚቻል አንድ ጥናት አመለከተ፡፡
በአለማችን ከፍተኛ የአዋላጆች እጥረት ከሚታይባቸው አካባቢዎች መካከል አፍሪካ ቀዳሚነቱን እንደምትይዝ የጠቆመውና በ194 የአለማችን አገራት ላይ በአለም የጤና ድርጅትና በአጋር ተቋማት የተሰራው ጥናት፣ ከ1 ሚሊዮን ያህሉ ተጨማሪ አዋላጆች መካከል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ለአፍሪካ እንደሚያስፈልጉም አክሎ ገልጧል፡፡
በአሁኑ ወቅት በማለው አለም 1.9 ሚሊዮን ያህል አዋላጆች በስራ ላይ ይገኛሉ ያለው ጥናቱ፣ ከእነዚህ መካከልም 90 በመቶ ያህሉ ሴቶች መሆናቸውንና ባለፉት አመታት ተጨማሪ አዋላጆችን አሰልጥኖ በማሰማራት ረገድ በቂ ስራ አለመሰራቱንና የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝም የአዋላጆችን እጥረት እንዳባባሰው አመልክቷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ